ወደ ዋና ይዘት ዘለው ይሂዱ

ክርስቶስን ጥሎ የህልውና ትግል ድል ሳይሆን ሞትን መጥራት ነው!!

"መድኀኒታችንን አምላካችንን ኢየሱስ ክርስቶስን እርሱት" የሚል የህልውና ታጋይ የአማራ ብቻ ሳይሆን የሰው ልጆችን ሁሉ የዘላለም ሕይወት የሚቃወም የዲያብሎስ ዋና ሠራተኛ ብቻ ነው ‼️

===============

የምንሞትለትን አገር እንደ እንግዳ ሳይሆን እንደ ባለቤት ልንኖርበት ይገባል!!!
አባት እናቶቻችን አገር ያስረከቡን የውጭ ጠላት ውክልና ወስደን እንድንጠፋፋና እንድንገፋፋ ሳይሆን በእነርሱ የተቀደሱ እሤቶች በነፃነትና በእኩልነት፣ በአንድነትና በእምነት ኖረን የሁለት ሀገር ባለቤቶች እንድንሆን ነበር።
==============
 ኦዶክሳውያን የጥምቀት ልጆች ለሁለንተናዊ  መብቶቻችን እንቁም!!! ጥምቀታችን ከቋንቋና ሥጋ ወገንተኝነት የላቀ ክርስቶስን መሆኑን አንዘንጋ!!

ይህ ኢትዮጵያ የሚባለው አገር በአባት እናቶቻችን ሁለንተናዊ መስዋእትነት እና በእግዚአብሔር ቸርነት ያገኘነውን የተጠበቀ ርስታችን እንጂ ዘረኛ ፖለቱከኞች የሚያድሉን ድርጎ፣  ሲሻቸው የሚነሱን ንብረታቸው እንዳልሆነም ታሳቢ እናድርግ!!

እንነሳ!!
===≠====================  እኔ እንደዚህ ከታች እንደጻፍኩት አምናለሁ፣ ለማምንበት እታገላለሁ። እናንተስ?
========= በውስጥ መስመር ስለምንሠራው ተግባር ተመካከሩ።

ይህ መንግሥት ሲወድቅ የወደቀችዋን አገር በኦርቶዶክሳውያእ እልቂት እንዲደመደም የዘር ነጻ አውጭዎች ነን ባዮች የኢትዮጵያና የነባርነታችን ጠላቶችን አጀንዳ ለማስፈጸም በስሑት የባዕዳን ርእዮትና በሐሰት ትርክት ያሳሳቱትን  የሕወሃት እናንየኦነጋውያን፣ የወሀብያውያን፣ የናዚያዊ ፕሮቴስታንት ጥምረት ያሳሳቱትንና ያስታጠቁትን ነፍሰ ገዳይ ታጣቂ ያሰማራሉ።

ተሰልፎ ከመጨፍጨፍ አሁኑኑ መነጋገርና መዘጋጀት፣ ሰብአዉነትናንህሊና ያተለያቸውን ለይቶ መተባበር ወቅቱ አሁን ነው።።

ባለማወቅ ወይንም በሤራ ተጠልፈው ባልተብራራ የባዕዳን  አጥፊ ፍልስፍና ታውረው "ሴኩላር ንጹሕ" ትግልና ፖለቱካ አለ በሚል ኦርቶዶክሳውያን መሰባሰቦችን የሚያወግዙ የፋኖ የውስጥ ጠላቶችን መቃወም ያስፈልጋል። ዘጠናዘጠኝ በመቶ የፋኖ ሠራዊትን ጠልፈው ከላይ ጉብ በማለት ለጸረ ኦርቶዶክስ ግብ ደሙን የሚያባክኑትን አንዳንድ ተላላኪ ሤሩኞች ሠራዊቱ አውቆ እኒጠነቀቅባቸው በእጃችሁ ያለውን መረጃ ሁሉ ይፋ አድርጉ። 
 ==========

በግልጽ ጠላትነታችሁን በአዋጅም ይሁን በነጻነት ትግል ሽፋን የምታካሄዱ ምሁራን፣ ታጣቂዎች፣ የአገርናንየክልል መንግሥታት ሁላችሁ፣ የዘረኝነት መንፈስ ልክፍት ለጥፋት ካሰለፋቸው እስከ ህልውና ታጋዮች ድረስ በተዘረጋው የፖለቲካና የትጥቅ ትግል ውስጥ የምትገኙ ኢትዮጵያውያን ሁሉ፣ በሀገር ውስጥና በውጭ ለአገራችን  መፍትሄ እንፈልጋለን የምትሉንሁሉ -------
------- አቋማችሁን ለእኛ መግገፋትና እልቂት ለሰለቸን ኦርቶዶክሳውያን ክርስቲያኖች  በግልጽ አሳውቁን -⁉️--- እኛን

ደማችሁን፣ ሀብታችሁን፣ ዕቀታችሁን  ስጡን ነገር ግን መብታችሁን አትጥቀሱ በሚል የሴኩላሪስቶች  የሃምሳ ዘመን ሤራ  ውስጥ መቀጠል አንችልም።  

ይህ እንዲያበቃ እምፈልጋለን ። ይህ ደግሞ የሚያበቃው እውነትን በፍቅር ስነነጋገር ብቻ ነው።

እንደተለመደው ፖለቲካና ሃይማኖትንይለያያል በሚል ያልተብራራ ማጭበርበሪያ በማያቋርጥ ሁለገብ ጥቃት ለመቀጠል ከማንችልበት የህልውና አደጋ ላይ እንገኛለን። ጎጠኝነትና ሤረኝነት ይበታትነናል።

ፖለቲካዊ ትክክለኝነት (political correctእንግባባ። 
(የፖለቱካዊ ትክክለኝነት አደገኝነት ለማንበብ ይህን ይጫኑ  https://ethiopiaorthodoxchristian.blogspot.com/2024/07/blog-post.html )  በኑፋቄ ጀምሮ በክህደት የሚጠናቀቅ የሰይጣን ማታለያ በመሆኑ ኦርቶዶክሳውያን በአገራችን የሚገባንን መብት ሁሉ ሳናመነታና በሌሎች አጀንዳዎች ሥር ሳንወሸቅ መጠየቅና ማስከበር ይኖርብናል።
================================

"ሃይማኖት ከፖለቲካ ሲደባለቅ አደጋ አለው"  የሚለው ስብከት ሳይንሳዊም፣ አመክንዮአዊም፣ ተግባራዊ ምስክርነት የለዉም። እንዳውም ተቃራኒው እውነት ነው።  እኛ የተሰቃየነው ከፈሪሃንእግዚአብሔር  ወጥተን በሴኩላሪዝም ወይንም በማርክሲዝም ስም ኢአማንያንናን የሚጠሉን ሥልጣኑን ጠቅልለው እንዲይዙት በመፍቀዳችን ነው። ኢአማንያንና መጤዎችን እንግዶች ለጠላቶቻችን ተወክለው ጨፈጨፉን ነው።

ምንም እንኳ በሐሰት ተራኪዎችና የውጭ ጠላቶች ስብከት ቢጠለሽም የእኛ የኦርቶዶክሳውያንናንሌሎች ነባር እሤቶችን የሚያከብሩ ወገኖች በሥልጣን መገኘት እንደሚተረከው ስንኳንስ ሌሎች እምነቶችን ሊጎዳ ቀርቶ ለዛፎችና አራዊቶች የተረፈ ነበር።

"እጄንና ጡቴንተቆርጦ ነበር" ከሚለው "እምነቴ ተጨቁኗል" ከሚለው ሐስተኛ  ቡድን ጀምሮ ዛሬ ላይ ነፍሰጡር ማኅፀን ከፍቶ ፅንስ እየሸለቀቀ  የሚገኘው ሥልጣን ላይንየሚገኘው ቡድን የሚመራው መንፈስ ነው።  ጥፋቱንም ውስክንጠፋ ለመቀጠል ሊያመቻቸን ወደንዛዥ የሆነውን የተለመደ "ስለሃይማኖታችሁ ትሟገቱ"  ሲሉን  መቀበል "አጥፉን" ብሎ ፈቃድ መስጠት ነው። 

የሚያስደንቀው ይህ አጥፊ መንፈስ በአንዳንድ ሰርጎ ገብ የፋኖ የውስጥ ሠራተኞች ሲቀነቀን መስማት መጀመራችን  ነው።  ⁉️
===============================
ኦርቶዶክሳዊ  መንፈሳዊነት በዓለም ውስጥ በተጎታችነት ብቻ እየኖሩ የሚደበቁበት ሕይወት ሳይሆን   ከግበበ ምድር እስከ ሮም ቤተ መንግሥት  አሕዛባዊነትን ተዋግቶ የመቀደስ የንቃት ጉዞ ነው!!
================================
ይህን ማንነታችንን በመዘንጋታችን አሳዳጅ የፖለቲካ ባህል አድጎ ቤተ መንግሥታችን ውስጥ እና በየትውልዱ የፖለቲካ ንቅናቄ ደረጃ ጎልቶ ይታያል።
=====≠===========================
ዛሬን ስናስብ:- 
ክርስቲያኖች ሁሉ ምናልባት በፕሮፓጋንዳ ብዛት ግራ ተጋብተው ፖለቲካን ለኢአማንያንና ለመናፍቃን ብቻ የተገባ የአገልግሎት ዘርፍ አድርጎ በማየት ራስን ማግለል ወይንም  በማመንታት  ወይንም በተጎታችነት በመሳተፍ በቤተ ክርስቲያን እና በልጆቿ ላይ ከውጭም ከውስጥም የተቃጣውን ጥቃት እንዲቀጥል ፈቅደናል።

እየተገፋን ነው፣  እየተጨፈጨፍን ነው፣ እየተከፋፈልን ነው፣ እየተሰደድን ነው።

ይህ ማብቃት አለበት።  

የሚያበቃውም በአገራችን ጉዳይ ሳንሽኮረመም እኩል ከሌሎች ወገኖቻችን ጋር ግልጽ በሆነ ዓላማ ያለ ድብብቆሽ ስንሳተፍና ስንተማመን ብቻ ነው። ዝም በሉ! ማንሾካሾክ ይበቃችኋል አልሠራም። 
የምንሞትለትን እገር እንደ እንግዳ ሳይሆን እንደ ባለቤት ልንኖርበት ይገባል።
========================
ንቅናቃዎች ሁሉ እየተነሱ የጥምቀት ልጆችን ዕውቀት፣ ሀለንተናዊ አቅም ፣ ላብ እና ደም እየተጠቀሙ በእኛ መስዋእትነት ለእምነታችንንተፃራሪ የፖለቲካ፣ የአስተዳደር፣ የፖሊሲና የአጠቃላይ አኗኗር አውድ ሲፈጥሩ ኖረዋል። 

የጥምቀት ልጆች መስዋእትነትና ደም ለክርስቲያኖች ተፃራሪን ለሆኑ ግቦች መዋል እንዳይችሉ በግልጽ አቅማችን የማንኛውም ትግል አካል ሆኖ መገለጽ አለበት። በሴኩላሪዝምና ገለልተኝነት ስም በሚጠሉን ወይንም እውቅና በሚነሱን ቡድኖችን ግለሰቦች መመራትን እምቢኝ ማለት ክርስቲያናዊ ግዴታችን ነው።።
==================
መታወቅ ያለበት

የዘላለም ሕይወታችን ብቸኛ መንገድ የሆነችዋን ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያናችንን የሚያሳንስ፣ በሕዝብ ሕይወት ውስጥ ሚና እንዳይኖራት የሚያስተምር፣ ታሪኳ እንዲጠለሽ የሚያደርግ ወይንም አይቶ የማይከላከል፣ አስተምሮዋ በአደባባይ ሳይሞገት ሰፈር ለሰፈርና በየካድሬ ማሠልጠኛው ሲጣጣል ዝምታን ይየሚመርጥ፣ "በአረጀና ባፈጀ" ስም የማናውቀውን አዲስነት የሚሰብክን አይቶ የማይቃወም ሁሉ  ለክርስቶሳዊ አስተምህሮና ሕይወት የመመስከር ግዴታውን ያልተረዳ ብቻ ሳይሆን የጠላቶቻችን ሠራተኛ ነው።

የሕይወት ብቸኛ መሰላላችንን ኦርቶዶክስን  ዒላማ የሚያደርግ አስተሳሰብ  ብቻ ሳይሆን ክርስቲያኖችን ከእምነታቸው ለይቶ ለማይጠቅመን ሴኩላር ፖለቲካ ግብ ግብአትነት ብቻ የሚፈልገን፣  ነገር ግን ሁለንተናዊ ህልውና (መንፈሳዊና ሥጋዊውን አስተካክሎ) የማያረጋግጥ፣  ጀግንነታችንን ብቻ ለድብቅ  ግቡ ብቻ ለማዋል የሚሞክር  ማንኛውንም ቡድን  አንቀበልም። 

እአንድ አካል ምንም አይነት መስዋእትነት  ቢከፍል  የክርስቶስን የመስቀል  ክፍያ ማሳነስም ሆነ መተካት አይችልም።  መተካት ብቻ ሳይሆን ለማሳነስ መሞከር  ከዘዓለም ሕይወት ህልውናችን የሚያስወጣን ነውና  ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ሁሉ አይቀበሉትም።
=============================

በዚህ ስሑት መንገድ የሄዱ የ፷ዎቹ ትውልድ እንዳደረጉት ሃይማኖታችንን ከሕዝብ ሕይወት                  
ለማስወገድ የሚሞክር:-  
👉  ከወጣት ተማሪ እስከ ፕሮፌሰር አስተማሪ፣
👉ከምንደኛ ቄስ እስከ ኢአማኒና ጎሠኛ ጳጳስ፣
👉 ከንዑስ ምንነት ፖለቲካ ታጋይ እስከ ምእራቡ ስግብግብ ተቋማት  እና እስከ ሀገራችን ሤረኛ ተላላኪ ድርጅቶች
👉 ከእልቃይዳ እስከ ቦኩሃራም መፈልፈያ ዉሀብያ
👉 ከደርግ እስክ ብልጽግና
👉ከዑስታዝ እስከ ዑላማ ----  ማንም ይሁን ማን ፣ በምንም ቋንቋ ይናገር፣ ምንም አብረቅራቂ ግብ አለኝ ይበል -----
------- የዘላለም ሕይወታችን እንቅፋት መሆኑ ከታወቀ "የመስቀሉ" ጠላቶች ተብለው እስከ ሰማዕትነት ተቃውሞ ይገጥማቸዋል።
እንግባባ።
በሃይማኖት ፖለቲካዊ ትክክለኝነትና ቁማርተኝነት ሳይሆን እውነትን በፍቅር መናገር ሕይወትን ይሰጣል። በእርግጥ ጊዜአዊ ድሎችን ሊያመክን ይችላል እንጂ ለዘለቄታው ፍሬው ጣፋጭ፣ ዘለቄታዊነቱ አስተማማኝ ነው።

https://photos.app.goo.gl/Awmsiui1VyqwGUPX6

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ገድሎና አስገድሎ ብፁዕ እየተባሉ መኖር የተፈቀደላቸው ጳጳሳትና ቆሞሳት እንዳይረሱ

ከጥር 27 ጀምሮ በተለያዩ የኦሮምያ ከተሞች በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቀኖና ውጭ የተሾሞና በቅዱስ ሲኖዶስ ተወግዘው የተለዩ አካላትን ወደ ቤተ ክርስቲያን እናስገባለን ባሉ የመንግስት የጽጥታ አካላት በተትኮሰ ጥይትና ሕገ ወጡ ቡድን ባደራጃቸው ወጣቶች ተደብድበው የተገደሉና የቆሰሉ  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ካህናትና ምእመናን።።   1)  ሻሸመኔ ከተማ   I.   የተገደሉ 1.  አያሌው ተረፈ ●   በሻሸመኔ የደብረ አስቦ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ማህደረ ፃድቃን ሰንበት ትምህርት ቤት አባል ●  ጥር 27 ዓ/ም በሻሸመኔ ከተማ በጸጥታ ሃይሉ በሚመራ የጨፍጫፊ ቡድን በደረሰበት ከፍተኛ ደብደባ ወደ ሆስፒታል ገባ ●  በአላቲዮን ሆስፒታል ሕክምና እየተደረገለት ሕይወቱን ማትረፍ አልተቻለም ●  በ ጥር 30 2015 ዓ/ም  ሰማዕትነትን ተቀብሏል       2.  ሊቀ ኅሩያን ቀሲስ ሐረገወይን ●  የሻሸመኔ ደብረ ስብሐት ቅዱስ ሚካኤል አገልጋይ የነበሩት ●  በሻሸመኔ በሕገወጦች በጸጥታ አካላት  በበግፍ በዱላ ተቀጥቅጠው በጭንቅላታቸው በእጅና በእግራቸው ላይ በደረሰባቸው ድብደባ በሀዋሳ ሕክምና እያሉ አርፈዋል። ●  ከመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች በተተኮሰ ጥይት ተመትተው  በያኔት ሆስፒታል ሕክምና ሲደረግላቸው ቢቆዩም ሕይወታቸውን ማትረፍ አልተቻለም። ●  በዛሬው ዕለት ጥር 30 2015 ዓ/ም  ሰማዕትነትን ተቀብለዋል።     3.  ዘማሪ ፍቃዱ ደጉ ●  የቅዱስ ሚካኤል ከሣቴ ብርሃን ሰ/ትቤት አገል...

ኢትዮጵያ የተገዳደሯትን ሁሉ ቅኝ ገዥወች የተከላከለችባቸው፣ የተዋጋችባቸውና ነጽነቷን ያስከበረችባቸው እሴቶች; በቀሲስ አስተርአየ ጽጌ

የጽዋዕ ማህበራትና ሰንበቴ ከቅድስት ድንግል ማርያም ጋራ የተሳሰሩት የጽዋ ማሕበራትና ሰንበቴወች ናቸው፡፡  ኢትዮጵያ የተገዳደሯትን ሁሉ ቅኝ ገዥወች የተከላከለችባቸው፣ የተዋጋችባቸውና ነጽነቷን ያስከበረችባቸው እሴቶች  ቀሲስ አስተርአየ ጽጌ  nigatuasteraye@gmail.com  ሚያዚያ ፳፩ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም.  (April 28, 2025)  መግቢያ  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያናችን ኩለንታዊት ቀዳማዊት ደኀራዊት፡ ዘመናዊት ናት ስትባል እም ኀበ አልቦ አይደለም፡፡ በብዙ እሴቶቿ ነው፡፡ ኩለንታዊት ከምታደርጋት ከብዙ እሴቶቿ መካከል የጽሑፌ መነሻ የሆኑት ከቅድስት ድንግል  ማርያም ጋራ የተሳሰሩት የጽዋ ማሕበራትና ሰንበቴወች ናቸው፡፡ ስንበቴ በቀጥታ ከእግዚአብሔር የታዘዘች ናት፡፡ የጽዋ ማኅበርም እንደ ሰንበቴው ቀጥታ ከግዚአብሔር ባይሆንም፡ በዮቶር በኩል ለሙሴ የደረሰው የግዚአብሔር ምሪት ናት፡፡ የጽዋ ማሕበርና ሰንበቴ የትርጉማቸው መነሻ፡ መድረሻና የመጨረሻ ዋና ዓላማቸው ሰባዊ ክብርና ነጻነት ነው፡፡   ኢትዮጵያ የተፈታተኗትን ሁሉ ቅኝ ገዥወች ከተከላከለችባቸው ከተዋጋችባቸውና ነጽነቷን ካስከበረችባቸው ዋናወቹ እሴቶቿ ውስጥ የጽዋ ማሕበራትና ሰንበቴወች ናቸው፡፡ በቅኝ ገዥወች ሲቀጠቀጡ ከኖሩት ካጎራባች አገሮች ልዩና የነጻነት ምሳሌ ያደርጓትም የጽዋ ማህበርና ሰንበቴ ናቸው፡፡ የጽዋ ማኅበራትና የሰንበቴ ድርጅቶች እንዴት ተመሰረቱ? ለኢትዮጵያ ምን ጠቀሙ? ትሩፋታቸው ምንድነው? የደርግንና የወያኔን ዘመናት እንዴት ተሻገሩ? በብልጽግና ዘመንስ እንዴት ናቸው? እንዴት ይቀጥሉ ? የሚሉትን ጥያቄወች ለመመለስ ከጽዋ ማኅበር እንጀምር፡፡   የጽዋ ማኅበር መነሻ...

ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን እና ቋንቋና ማንነት ተኮር እንቅስቃሴዎች

  ኦ ርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን እና ቋንቋና ማንነት ተኮር እንቅስቃሴዎች   ፩ . ቋንቋን በተመለከተ ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮና ትውፊት ከሰው ልጅ መበደል በፊት ፍጥረት ሁሉ የሚግባባው በአንድ ቋንቋ ነበር፡፡ “ ምድርም ሁሉ በአንድ ቋንቋና በአንድ ንግግር ነበረች” እንዲል፡፡ ዘፍ. 11፡1 በኃጢአት ምክንያት ግን ሰውና መላው ፍጥረት በአንድ ቋንቋ መግባባታቸው ቀረ፡፡ ኃጢአት እየበዛ ሲሄድ የሰው ልጅ ቋንቋም በባቢሎን ተደበላለቀ፣ አንዳቸው ከሌላቸው ጋር የማይግባቡ ብዙ ዓይነት ቋንቋዎችም ተፈጠሩ፡፡ በበደል የመጣውን ሁሉ ሊያስተካክልና ሊያድን በመጣው በአምላካችንና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አዳኝነት ያ የቀደመው ጸጋ ስለ ተመለሰልን በበዐለ ሃምሳ ሰዎች በልዩ ልዩ ቋንቋ አንድ ዐይነት የእግዚአብሔርን መልእክት ሰሙ፡፡ በዚህ ጸጋ የተጠቀሙና የበቁ ቅዱሳን የእንስሳትን ቋንቋ እስከ ማወቅ ደረጃ ይደርሳሉ፡፡   የክርስትና ጉዞ ወደ ቀደመው በአንድ ቋንቋ መግባባት መመለስ ነው፡፡ ወደዚያ ለመድረስ ደግሞ ሰው የእግዚአብሔርን ቃል በሚሰማው ቋንቋ መማር አለበት፡፡ በበዐለ ሃምሳ ጊዜ ለቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስ ብዙ ቋንቋ የገለጠላቸው ሰውን ሁሉ የእግዚአብሔርን የማዳን ጸጋ በሚሰማው ቋንቋ እንዲያስተምሩት ነው፡፡ ሆኖም ቋንቋ መልእክት ማድረሻና መግባቢያ እንጂ ከዚያ ያለፈ ሰዎችን በሆነ መደብ ለመመደብና የልዩነት አጥር ለመሥራት እንደ መሳሪያ ሊሆን አይገባውም፡፡ ይህ ከክርስትና ዐላማ ጋር ተቃራኒ ነው፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያት ወደ ዐለም ሁሉ ሲልካቸው ሰዎች የሚቀበሏቸው በሚያስተምሩት ትምህርት መሠረት ነበር እንጂ በትውልድ፣ በብሔርና በመሳሰለው መስፈርት የእኛ ናቸው/አይደሉም በሚል አልነበረም፡፡ የቤተ ክርስቲያ...