ምን ነክቶን ነው በማኅበራዊ ሚዱያ ጀግናና እፕዋቂ የሆንን እኛ ግብዜቹ ከማሰብ ወደ መከተል ሰውነት የወረድነው? አሁንስ ፈራሁ። በፓስታና ኮካ ውስጥ ሊቀበሩ በሚችሉ ማይክሮ ሺፕስ እናንተን/ዘረ-መል ለውጭ ቅንጣት ሮቦት ሆነን ይሆን?
ምነው ሰው ከመሬት ተነስቶ ፕሮግራምድ ሆኖ እንደተለቀቀ ድሬንንየተጫነውን ሁሉ የሚተኩሰው? ባለህሊና ሰው መሆናችን ሊቀር እንዳይሆን?
በእምነታችን ደረጃ ክርስቲያን ክልሆኑት በጋራ የምናመልከው አምላክብየለንም።
የእኛ አምላክ ራሱን በባሎን ግንብ፣ በአብርሃም ቤት እንግድነት፣ በዳዊት ትንቢት፣ ኋላም በዮርዳኖስ በልጁ ጥምቀት፣ በታቦር በነብያትናን ሐዋሪያት ጉባዔ ምስክርነት የነገረን ያለመቀላቀል አንድም ያለመለያየት ሶስትም መሆኑን ነው። አንድ አምላክ ቅድስት የሆነች ሦስትነቱን (አብ ወልድ መንፈስ ቅደስ አንድ አምላክ) መሆኑን ነው።
ሌሎች አንድ ቢሉ ምን እንድሆነ ሊገልጹት የማይችሉት ወይ በፍልስፍና ወይ ወግ እንጠብቃለን ብለው የመገለጥ ትምህርትን በመቃወም፣ ወይንም ነብያት ያስተማሩትን፣ ወንጌላውያን በእግዚአብሔር በሥጋ በመገለጥ ያስተማራቸውን ትምህርት ሲያስተላልፉ ባለመቀበል አዳዲስ አማልክት ለራሳቸው ፈጥረዋል። ስለዚህ የጋራ አምላክ የለንም።
ነገር ግን በማመንና ባለማመን ደረጃ የጋራ አምላክ ባይኖረንም የጋራ ሰውነት፣ የጋራ ምድራዊ አገር ፣ የጋራ ምድራዊ መንግስት፣ የጋራ ዜጋዊ ክብር ግን አለን።
የጋራ ሰማያዊ ርስት ያለን በጋራ ቅርንጭፍ የሆንበትን ሕያው የወይን ግንድ የክርስቶስን የእግዚአብሔር ልጅነት የተቀብልን ከተጠመቅነው ጋር ሁሉ ብቻና ብቻ ነው። ሌሎች ከተቀበሉት ርስቱን አሁንም ቢሆን ይወርሳሉ።
ለክርስቲያን ማስመሰል ኃጢአት ነው። ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እግዚአብሔር ነው ብሎ አምኖ፣ በአፍ መስክሮ መዳን ራሱ ያስተማረን እንደሆነ በእውደምህረት ጆሮአችን እስኪግል ይነግሩንና ከቤተ ክርስቲያን ውጭ ከአሕዛቡም፣ ከመናፍቁም፣ ከፀረ ክርስቶስም ጋር ይጸልያሉ። አንድ ክርስቲያን የሊብራል ኢአማንያን መንፈስ ተጋሪ ካልሆነ በስተቀር እውነትን ደብቆ ውሸትን ዲፕሎማሲና አብሮነት ነው በሚል ግብዝነት ትውልድን ክህደት አያወርስም።
"ችግር የሚፈታው፣ ፖለቲካ የሚሠራው፣ ጦርነት የሚካሄደው፣ እውቀት የሚፈለገው እምነትን ጥሎ ነው" የሚል ክርስቲያን ክህነትን ከንግሥናብያስተባበሩትን ቅዱሳን ነገሥታት ከምልከ ጸዴቅ እስከ ዛሬ ያሉትን ሁሉ፣ በተለይ በቅርብ ዘመናት የተገለጡትን ቅዱስ ይምርሃነ ክርስቶስን፣ ቅዱስ ላሊበላን፣ ቅዱስ ነአኲቶ ለአብን ቅዱስ አጼ ካሌብን ወዘተ ያሚያነውር ከሀዲ ነው። ታቦት ተሸክመው አድዋ ዘምተው ከሴኩላሪስቶቹ አራዊት የታደጉንን ማውገዝና መሳደብ ነው። የቅዱሳን ሰማዕታት ጳጳሳትን የአቡነ ጴጥሮስን፣ የእቡነ ሚካኤን፣ ፰ሺ ከሀዲውን ሱሲንዮስ ተዋግተው የተሰዉትን የጎንደር ሰማዕታትን መሳደብ ነው።
የሚገርመኝ የፍቅር ትርጉም ጠፍቷቸው "፣መቻቻል፣ መብት ማስከበር፣ ጨቋኝ ተጨቋኝ፣ ነፃነት፣ ወዘተ" በተሰኙና ትርጉማቸው በአገሩ የባህል፣ የእምነትና የታሪክ አውድ ውስጥ ያልተነገሩ ፅንሰ ዐሳቦችን በማንገብ ስለ ሰማይ ርስት የክርስቶስ ሰማዕታት በሚያስመስላቸው ትጋት በማኅበራዊ ሚዲያ ድንቁርናቸውን መተኪያንየሌለው ዕውቀት አስመስለው የሚወናጨፉ ወገኖቼን በታላቅ ትህትና ተረጋጉ ለማለት እወዳለሁ።
የፍቅር ሃይማኖት ውስጥ እየኖርን፣ ሰውን በእምነትና በሰው ሠራሽ ማንነቱ የእግዚአብሔር ክቡር ፍጡርነቱን እንደማንነሳ የውጭ ተላላኪ ያልሆነ ህሊና ያለው ሁሉ የሌላ እምነት ሰውብያውቃል። ይህ እየታወቀና የ፫ ሺ ዘመን ታሪካችን እየመሰከረልን እንዴት ፍቅርን የማያውቁ መንገደኞች "በመቻቻል" ስም እውነትን እንዳንመሰክር፣ ሃይማኖታችንን በሁሉም የሕይወት ዘርፎቻችን ማለትም በፖለቲካ፣ በጦርነት፣ በሰላም፣ በምጣኔ ሀብት በአስተዳደር፣ በትምህርት በሕግ፣ በፖሊሲ ውስት እታካቱት የሚሉን ለዚያውም ተጠመቅን የሚሉ ሰዎች ተፈጠሩ? ነው ጥምቀቱ አልገባቸውም? የእግዚአብሔር ልጅ የመሆን ሥልጣን የሚያስከትለውን በሕይወት የመመስከር ኃላፊነት ችላ ለማለት አዲሲ ሃይማኖት-አከሉ የብሔር ፖለቲካ ነጠቃቸውን? እላለኩ።
እኔ ሰውንንየምወደው፣ የማከብረው፣ የምታገልለት በሃይማኖት አይደለም። በመጀምሪያ በመሆኑ ነው። ሁለትኛ በመገፋቱና ዒላማ በመደረጉ ድምጽና ድጋፍ እንደሚያስፈልገው ሳምን ነው።
ከዚህ ውጭ ብየ ማንም ጭፍን አገልጋይ፣ መገልገያና ማደሪያ አልሆንም።
" ስለ ኦርቶዶክስ መገፋት የማንናገረው አጠገባችን እነ እንትና ስላሉ ነው" የሚለው መከራከሪያ ራስን ትኩሶ እንደማቁሰል ያለ ጅልነት ብቻ ሳይሆን የጠላት ሤራ ሰለባ መሆን ነው። ፍቅር የማያውቁና በእምነት ካልመሰልከኝ በዚህ ዓለም በምድር መኖር አይገባህም የሚሉ የሰው ሰራሽ እምነቶችን ባህል አምጥቶ "ኦርቶዶክሳዊት ክርስትናን" በዚያው ልክ መመልከት ምን ለራስህ ብል ስምህ ፈራሃለሁ ማለት ስህተት ብቻ ሳይሆን የማይገባ የክፋት ብልጠት ነው።
ይህችም ቪዲዮ ታስተምራለች https://youtu.be/lNcskbugmLY?si=5rX8L_P7ngP64RUe
ምነው ሰው ከመሬት ተነስቶ ፕሮግራምድ ሆኖ እንደተለቀቀ ድሬንንየተጫነውን ሁሉ የሚተኩሰው? ባለህሊና ሰው መሆናችን ሊቀር እንዳይሆን?
በእምነታችን ደረጃ ክርስቲያን ክልሆኑት በጋራ የምናመልከው አምላክብየለንም።
የእኛ አምላክ ራሱን በባሎን ግንብ፣ በአብርሃም ቤት እንግድነት፣ በዳዊት ትንቢት፣ ኋላም በዮርዳኖስ በልጁ ጥምቀት፣ በታቦር በነብያትናን ሐዋሪያት ጉባዔ ምስክርነት የነገረን ያለመቀላቀል አንድም ያለመለያየት ሶስትም መሆኑን ነው። አንድ አምላክ ቅድስት የሆነች ሦስትነቱን (አብ ወልድ መንፈስ ቅደስ አንድ አምላክ) መሆኑን ነው።
ሌሎች አንድ ቢሉ ምን እንድሆነ ሊገልጹት የማይችሉት ወይ በፍልስፍና ወይ ወግ እንጠብቃለን ብለው የመገለጥ ትምህርትን በመቃወም፣ ወይንም ነብያት ያስተማሩትን፣ ወንጌላውያን በእግዚአብሔር በሥጋ በመገለጥ ያስተማራቸውን ትምህርት ሲያስተላልፉ ባለመቀበል አዳዲስ አማልክት ለራሳቸው ፈጥረዋል። ስለዚህ የጋራ አምላክ የለንም።
ነገር ግን በማመንና ባለማመን ደረጃ የጋራ አምላክ ባይኖረንም የጋራ ሰውነት፣ የጋራ ምድራዊ አገር ፣ የጋራ ምድራዊ መንግስት፣ የጋራ ዜጋዊ ክብር ግን አለን።
የጋራ ሰማያዊ ርስት ያለን በጋራ ቅርንጭፍ የሆንበትን ሕያው የወይን ግንድ የክርስቶስን የእግዚአብሔር ልጅነት የተቀብልን ከተጠመቅነው ጋር ሁሉ ብቻና ብቻ ነው። ሌሎች ከተቀበሉት ርስቱን አሁንም ቢሆን ይወርሳሉ።
ለክርስቲያን ማስመሰል ኃጢአት ነው። ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እግዚአብሔር ነው ብሎ አምኖ፣ በአፍ መስክሮ መዳን ራሱ ያስተማረን እንደሆነ በእውደምህረት ጆሮአችን እስኪግል ይነግሩንና ከቤተ ክርስቲያን ውጭ ከአሕዛቡም፣ ከመናፍቁም፣ ከፀረ ክርስቶስም ጋር ይጸልያሉ። አንድ ክርስቲያን የሊብራል ኢአማንያን መንፈስ ተጋሪ ካልሆነ በስተቀር እውነትን ደብቆ ውሸትን ዲፕሎማሲና አብሮነት ነው በሚል ግብዝነት ትውልድን ክህደት አያወርስም።
"ችግር የሚፈታው፣ ፖለቲካ የሚሠራው፣ ጦርነት የሚካሄደው፣ እውቀት የሚፈለገው እምነትን ጥሎ ነው" የሚል ክርስቲያን ክህነትን ከንግሥናብያስተባበሩትን ቅዱሳን ነገሥታት ከምልከ ጸዴቅ እስከ ዛሬ ያሉትን ሁሉ፣ በተለይ በቅርብ ዘመናት የተገለጡትን ቅዱስ ይምርሃነ ክርስቶስን፣ ቅዱስ ላሊበላን፣ ቅዱስ ነአኲቶ ለአብን ቅዱስ አጼ ካሌብን ወዘተ ያሚያነውር ከሀዲ ነው። ታቦት ተሸክመው አድዋ ዘምተው ከሴኩላሪስቶቹ አራዊት የታደጉንን ማውገዝና መሳደብ ነው። የቅዱሳን ሰማዕታት ጳጳሳትን የአቡነ ጴጥሮስን፣ የእቡነ ሚካኤን፣ ፰ሺ ከሀዲውን ሱሲንዮስ ተዋግተው የተሰዉትን የጎንደር ሰማዕታትን መሳደብ ነው።
የሚገርመኝ የፍቅር ትርጉም ጠፍቷቸው "፣መቻቻል፣ መብት ማስከበር፣ ጨቋኝ ተጨቋኝ፣ ነፃነት፣ ወዘተ" በተሰኙና ትርጉማቸው በአገሩ የባህል፣ የእምነትና የታሪክ አውድ ውስጥ ያልተነገሩ ፅንሰ ዐሳቦችን በማንገብ ስለ ሰማይ ርስት የክርስቶስ ሰማዕታት በሚያስመስላቸው ትጋት በማኅበራዊ ሚዲያ ድንቁርናቸውን መተኪያንየሌለው ዕውቀት አስመስለው የሚወናጨፉ ወገኖቼን በታላቅ ትህትና ተረጋጉ ለማለት እወዳለሁ።
የፍቅር ሃይማኖት ውስጥ እየኖርን፣ ሰውን በእምነትና በሰው ሠራሽ ማንነቱ የእግዚአብሔር ክቡር ፍጡርነቱን እንደማንነሳ የውጭ ተላላኪ ያልሆነ ህሊና ያለው ሁሉ የሌላ እምነት ሰውብያውቃል። ይህ እየታወቀና የ፫ ሺ ዘመን ታሪካችን እየመሰከረልን እንዴት ፍቅርን የማያውቁ መንገደኞች "በመቻቻል" ስም እውነትን እንዳንመሰክር፣ ሃይማኖታችንን በሁሉም የሕይወት ዘርፎቻችን ማለትም በፖለቲካ፣ በጦርነት፣ በሰላም፣ በምጣኔ ሀብት በአስተዳደር፣ በትምህርት በሕግ፣ በፖሊሲ ውስት እታካቱት የሚሉን ለዚያውም ተጠመቅን የሚሉ ሰዎች ተፈጠሩ? ነው ጥምቀቱ አልገባቸውም? የእግዚአብሔር ልጅ የመሆን ሥልጣን የሚያስከትለውን በሕይወት የመመስከር ኃላፊነት ችላ ለማለት አዲሲ ሃይማኖት-አከሉ የብሔር ፖለቲካ ነጠቃቸውን? እላለኩ።
እኔ ሰውንንየምወደው፣ የማከብረው፣ የምታገልለት በሃይማኖት አይደለም። በመጀምሪያ በመሆኑ ነው። ሁለትኛ በመገፋቱና ዒላማ በመደረጉ ድምጽና ድጋፍ እንደሚያስፈልገው ሳምን ነው።
ከዚህ ውጭ ብየ ማንም ጭፍን አገልጋይ፣ መገልገያና ማደሪያ አልሆንም።
" ስለ ኦርቶዶክስ መገፋት የማንናገረው አጠገባችን እነ እንትና ስላሉ ነው" የሚለው መከራከሪያ ራስን ትኩሶ እንደማቁሰል ያለ ጅልነት ብቻ ሳይሆን የጠላት ሤራ ሰለባ መሆን ነው። ፍቅር የማያውቁና በእምነት ካልመሰልከኝ በዚህ ዓለም በምድር መኖር አይገባህም የሚሉ የሰው ሰራሽ እምነቶችን ባህል አምጥቶ "ኦርቶዶክሳዊት ክርስትናን" በዚያው ልክ መመልከት ምን ለራስህ ብል ስምህ ፈራሃለሁ ማለት ስህተት ብቻ ሳይሆን የማይገባ የክፋት ብልጠት ነው።
ይህችም ቪዲዮ ታስተምራለች https://youtu.be/lNcskbugmLY?si=5rX8L_P7ngP64RUe
አስተያየቶች