ወደ ዋና ይዘት ዘለው ይሂዱ

በእኔ አማራ እና በዘረኞች ቡድን የአማራ አይነት መካከል ያሉ ልዩነቶች

 እንደማንኛውም ማኅበረስብ ስለ አማራ ማኅበረሰበ ያገባኛል!!

ነገር ግን ስሞኑን የምትንጫጩ  ጥቂት የሤራ ቡድኖች የግል እቃችሁ ስለሆነው አማራ በእርግጥ አያገባኝምና አልናገርም። ስለ ነጻ ሕዝብ አማራ ግን ያገባኛል።

በዚህ ጽሑፌ አቋሜን ግልጽ ላድርግላችሁ እና በግምት ከምትፈጥሩት የሀሰት ትርክት ላሳርፋችሁ።

አማራ በእግዚአእብሔር የሚያምን ሕዝብ ነው፤ ነጻ የሚወጣውም እግዚአብሔርን ይዞና መከታው አድርጎ እንጂ እናንተ እንደምትሉት  እምነቱን እንደ ትርፍ ነገር ወዲቅያ በል ብሎ ትቶት አይደልም‼️
===========================================
መታወቅ ያለበት ፦ 
አማራ ሕዝብ እንጂ  ከሕወሃትና ኦነጋውያን እንደቀሰማችሁት ጥቂት ግለሰቦች በአምሳላቸው የሚፈጥሯቸው ቡድኖች የፈቀዱትን የሚፈጽሙበት የእጅ  መሣሪያቸው እና ባሪያቸው አይደለም። 

 በሌላ አነጋገር ፦
👉አማራ በእግዚአብሔር የሚያምን እግዚአብሔር በነጻ ፍቃድና በግዕዛን የፈጠራቸው ሰዎች አንድነት ያስገኘው ታሪካዊ ሕዝብ ነው እንጂ ዛሬ የሚነሱ ልሂቃን በአእምሮአቸው ስፋትና አመለካከት ለክተው የሚፈጥሩት ፖለቲካዊ ማንነት አይደለም! 

👉 አማራ ለሰው ልጅ ሁሉ በሀገሩ የሚገባው ማኅበራዊ፣ መንግሥታዊና መንፈሳዊ ክብርን የነሱትን መዋቅራትና ፖልቲካዊ ርዮቶችን እንጂ የጎሣም ሆነ የእምነት ጠላቶች አላበጀም! እናንተም አታብጁለት፣ ሌላውን ማንነቶች "እንትን" እያላችሁ በአማራ ስም አትስደቡ፤

👉አማራ በሀገሩ መንግሥታዊ ሥራዓት ውስጥ እንደ ሕዝብ ከሰው ሁሉ እኩል ሆኖ የሚመራበትና የሚመ'ራበትን ሁኔታ ልፍጠር አለ እንጂ ማንንም ላሳንስ ወይን ባሪያ ላድርግ፣ ላፈናቅል ወይንም ላምክን፣ ከተወሰን አካባቢ ላጽዳ ወይንም ሁለገብ አድልዎ ልፈጽምበት አላለም! እናንተም እንድ አማራ በሉ፤

👉አማራ በፖለቲካዊ ረዮትና በመንግሥታዊ ሥራዓት ተግፋውን ሕዝብ ልዕልና ላስመልስ፣ የሀገርና የርስት ባለቤትነቱን ላረጋግጥ አለ እንጂ የናርሲሲስትና ሤረኛ የግለስቦችን  ንግሥና  ላርጋግጥ፤ ከዚያም እነርሱ  መልሰው ሲያጠፉት ከኖሩት አካላት  መሸነፍ በኋላ ከአብራኬ ለሚከፈሉት ባርያ ልሁን አላለም! ---
----  ይህ እንግዲህ እኔ እስከምረዳው ድረስ ማለት ነው። --- ደግሞ ግልገል ፋሽቶች ብቅ በሉና "በአማራ ትግል ምን አገባህ" ብላችሁ ተንጫጩ አሉ። ነግሬአችኋለሁ --- ስለ ሰው ያገባኛል ( ከሁልተ ዓመታት አስቀድሞ ነግሬአችሁ ነበር 👉 https://youtu.be/j1PeK_LWfKc )። በእርግጥ የናንተ የግል እቃ የሆነ አማራ ከአለ አያገባኝም
===================
 #ሲጠቃለል
የአማራ ሕዝብ የህልውና ትግል የመጨረሻ ግብ ሕዝብን ከህልውና አደጋው በዘለቄታዊነት መታደግ ወይስ የትግራይና የኦሮሞን ሕዝብ በነጻነት ስም አሰልፈውና አድምተው፣ በመጨረሻ በትግሉ ተሳትፈው  ለሞቱት የድንጋይ ሐውልት አቁመው፣ "ታራራን ያንቀጠቀጠ ትውልድ" የመሰለ ድርሰት ደርሰውለት፣  ሤርኞቹ የትግሉ መሪዎች ግን በትግሉ ከሞትና ከስደት የተረፈውን ሕዝብ #1ለ5 አየጠርነፉ የአእምሮና የአካል ባሪያ አድርገው፣ ባዘጋጁት የንዑስ ማንነት የክልል ጎርኖ ውስጥ አሥርው፣  ለ30 ዓመታት  በዘርፋ ሲከብሩ  እና የተከተላቸውን ሕዝብ ሀገር የሚያማስሉበትና የሚያፈርሱበት ሠራዊት እንዳደርጉት እንደ ሕወሃትና እንደ ኦነግ/ኦሮሙማ አይነት ሌላ ዙር #የዘረኞች #ሥርዓት ለመትከል ነውን? ነ  የሚለውን ጥያቄ መመለስ ወቅቱ አሁን ነው።  

እኔ አይደለም የምለው ሕየወቴ ሙሉ ከገበሬው ጋር ከሶማሌ ክልል በስተቀር ከሁሉም ማኅበረሰብ ጋር ቤት ለቤት በደረሰ ደረጃ በመሥራትና በማጥናት፣ በመማርና በማስትማር ስላሳለፍኩ ነው። 

የሕዝቡን ተጋድሎ ለግል ፍተወታቸው ለመጥለፍ የሚጋጋጡ እንደአሉ   ለማወቅ ብዙም የሚያደክም ምርምር አያሻም። አሁን ላይ ተደራጅተው በሚያሠራጩት መርዛማ፣ ከፋፋይና አጠልሺ፣ ኦርቶዶክስ-ጠል፣ ፋሽታዊ የሐሰት መርጃ  ብቻ ከመገመት ያለፈ ብያኔ ላይ መድረስ ይቻላል።  
ሌላው ምልክታቸው 
👉 "አማራ" የእኔ ንብረት ስለሆነ እኔ እና እኔን ብቻ ማዳመጥ አለበት፣ ሌላ አማራጭ ዐስተሳስብ አታሰሙት፣ እ
👉 እናንተ የእንትን ጎሣ አባል ስለሆናችሁ ዐሳባችሁ ሁሉ ለአማራ አሉታዊ ነው፣ 
👉 የደም ጥራታችሁ የተበከለ ስለሆነና እኛ በደምና አጥንት እንጂ በእሤት፣ በባህል፣ በእምነትና በታሪካዊ ማንነት አናምንም እና ጣልቃ አትግቡብን፣ ወዘተ ማለታቸው እና እንዲሁም 
👉  ከአማራነት በወርደ ነውረኝነት ለጥቂት  ሰዎች ቡድናዊ ሤራ  የሚያገለግሉ ገለሰቦችን በመረብ በማደራጀት  በመላው ዓለም የሚገኙ የአማራ ተጋድሎ ድጋፍ ሰጭ ስብስቦች መካከል በማሰማራት መጠምዘዝ፣ ማወክ፣ ማፍረስና መልሶ በልካቸው ለማደራጀት መጣራቸው፣
👉   በፈጠሩት ሀገርና ዓለም ዐቀፍ የሤራዎቻቸው ተጋሪ ወይንም የተታለለ የዋህ ወገን በኩል ዒላማ ያደረጉትን ግለስብም ይሁን ለትግሉ አማራዊ አንድነት የሚጠቅመውን ሁሉ ስም ማጠልሸት --- ወዘት  በቂ ማስርጃ ነው።  
--- ለሚያቀርቡት ክስና ሐሰት አንድም ማስርጃ አቅርበው መሟገት አይችሉም። 
 
እንደ እኔ ከሆን (#"ምን አገባህ" ለምትሉ ፋሽስቶችና ድውያን ቦታ የለኝም፣ የምናገረው ህሊና፣ ፈሪሃ እግዚአብሔር ላላቸው፣ ለክብር-ሰበእ እና ለፍትፍ ለቆሙት ሰዎች እንጅ ለሤርኛ ቡድን የአእምሮ ባርነት ለሚያገለግሉት ተላላኪዎች አይደለምና) የአማራ ወጣትና ገበሬ ደም እየፈሰሰ የሚገኘው የህልውና አደጋ የደቀኑትን ፦ 

(1) የዘር መዋቅራትና መንግሥታዊ ሥራዓታትን፣ 

(2) ዘረኝነትን ወደ ፖለቲካዊ ርእዮተ ዓለም ያሳደገውን የአስተሳስብ መሠረትና ትርክት፣ 

(3)ከዚያም ሰዎችን በንዑስ ማንነታቸው ወደ ሚታሠሩበትና "ሌላ" ከተባለው (በተለይ ከአማሮችና ኦርቶዶክስ ክርሰቲያኖች) ሥፍራ/ክልል የሚጸዱበትን መንግሥታዊ ፖሊሲና አሠራር፣ -----

----  በማሸነፍ እና ሥልጣንን በዘልቄታዊነት ዳግም በእኩያን እጅ እናዳይገባ ለመቆጣጠር የሚያስችል አስተማማኝ ሀገራዊ ሁኔታ መፍጠር ነው!!‼️  --- ለተፈጸሙት የዘመናት ግፎች ፍትሕ ማስገኘት፣ ተገፊዎችን ማስካስ፣ ከፊዎችን በሕግ ፊት ማቅረብ እና የትውልድን የወደፊት ተስፋና አስተማማኝ ሰላም ማረጋገጥ ናቸው። 
--- ከዚህ ያነስ ሁሉ ከንቱ መድማት ነው‼️

በአጭሩ፦ 
የህልውና አደጋ የተደቀነበት፣ ላልፉት 50 ዓመታት መንግሥታዊ ሥልጣንን በተቆጣጠሩ የአሉታዊ ብሔርተኞች(ዘረኞች)ሲፈናቀል፣ ሲዋረድ፣ ሲገደል፣ ሲመክን፣ ሲደኸይ የኖረውን፣ አሁን እየተጨፈጨፈ ያለውን አማራንና በአማራ ምሥጢራዊ "ኮድነት"የ የሚደመሰሰውን ኦርቶዶክሳዊ ክርስቲያን ፍትሕና ሰብአዊ ክብር፣ የሀገር ባለቤትነት እና ከሌሎች ወገኖቹ በንዑስ ማንነቱ ሳይለይ ዋስትና ባለው ሀገር ውስጥ እንዲኖር ማስቻል ነው።

ከዚያ ያለፈም፣ ያነሰም  ድብቅ አጀንዳ አንግቦ፣ ከባእዳንና ለመክራው መከስት ምክንያት ከሆኑ አካላትም ሆነ ከአስተሳሰቦቻቸው እይተዋሱ የሕዝብን የደምና አጥንት ዋጋ  በማርከስ  ለጥቂት ግለሰቦችና ቡድኖች የፍተወት እርካታ ለማዋል መሞከር ወንጀልም፣ ኃጢአትም ነው።

በዚያ ላይ አማራንም ሆነ ሌሎችን የቋንቋና የእምነት ንዑስ ማንነቶች የህልውና አደጋ ላይ የጣሉ አካላትን ትፋት መልሶ መላስ ያህል ክህደት  መዋስ ያሳፍራል። የእነርሱን የትግል መርህና ስልት በተለይ የሐሰት ትርክት መፈብርክ፣ ሤረኝነት፣ ቁማርተኝነት፣ ፋሽታዊ ዘርኝነት፣ ነባር-ጠልነት፣ ጸረ ኦርቶዶክሳዊነትን  ለአማራ ሕዝብ የህልውና ትግል እንደ መሣሪያ መጠቀም አማራን መልሶ እንደምውጋት የሚቆጠር የውስጥ  እሾኽነት ነው።  
--- በዚህ መንገድ እየተገለጣችሁ ያላችሁ ግለሰቦችና ተከታዮቻቸው ሁልት ጊዚ አስቡበት። ከእውነት ጋር ስትጋጩ፣ ቤተ ክርስቲያንን ስታፈርሱ እንዳትገኙ። ቤተ ክርስቲያ የጥምቀት ለጆች ሁሉ አንድነት ነው እና ለትግላችሁ አእምሮአችሁን አስፍታችሁና ተጨንቃችሁ እርሷን ሳትነኩ አንድ ጠንካራ ኃይል ሁኑ። የለም ከርሷ ተነጥለን እና ተነጣጥለን፣  በአምላክ-የለሽነት መርህ (ፈረንጆቹ ሴኩላር/ሊብራል (ዶግማ አለባ)) እንድሚሉት) ፋሽስታዊ የደምና የአጥንት  ቀምርን ተጠቅመን ብቻ ነው የሚያዋጣን ካላችሁ የምታጡት አማራን ነው። 

አማራ በእግዚአእብሒር የሚያምን ሕዝብ ነው፤ ነጻ የሚወጣውም እግዚአብሔርን ይዞና መከታው አድርጎ እንጂ እናንተ እንደምትሉት ትቶት አይደልም‼️
https://youtu.be/j1PeK_LWfKc?si=84-B0j09I708VP45

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ገድሎና አስገድሎ ብፁዕ እየተባሉ መኖር የተፈቀደላቸው ጳጳሳትና ቆሞሳት እንዳይረሱ

ከጥር 27 ጀምሮ በተለያዩ የኦሮምያ ከተሞች በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቀኖና ውጭ የተሾሞና በቅዱስ ሲኖዶስ ተወግዘው የተለዩ አካላትን ወደ ቤተ ክርስቲያን እናስገባለን ባሉ የመንግስት የጽጥታ አካላት በተትኮሰ ጥይትና ሕገ ወጡ ቡድን ባደራጃቸው ወጣቶች ተደብድበው የተገደሉና የቆሰሉ  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ካህናትና ምእመናን።።   1)  ሻሸመኔ ከተማ   I.   የተገደሉ 1.  አያሌው ተረፈ ●   በሻሸመኔ የደብረ አስቦ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ማህደረ ፃድቃን ሰንበት ትምህርት ቤት አባል ●  ጥር 27 ዓ/ም በሻሸመኔ ከተማ በጸጥታ ሃይሉ በሚመራ የጨፍጫፊ ቡድን በደረሰበት ከፍተኛ ደብደባ ወደ ሆስፒታል ገባ ●  በአላቲዮን ሆስፒታል ሕክምና እየተደረገለት ሕይወቱን ማትረፍ አልተቻለም ●  በ ጥር 30 2015 ዓ/ም  ሰማዕትነትን ተቀብሏል       2.  ሊቀ ኅሩያን ቀሲስ ሐረገወይን ●  የሻሸመኔ ደብረ ስብሐት ቅዱስ ሚካኤል አገልጋይ የነበሩት ●  በሻሸመኔ በሕገወጦች በጸጥታ አካላት  በበግፍ በዱላ ተቀጥቅጠው በጭንቅላታቸው በእጅና በእግራቸው ላይ በደረሰባቸው ድብደባ በሀዋሳ ሕክምና እያሉ አርፈዋል። ●  ከመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች በተተኮሰ ጥይት ተመትተው  በያኔት ሆስፒታል ሕክምና ሲደረግላቸው ቢቆዩም ሕይወታቸውን ማትረፍ አልተቻለም። ●  በዛሬው ዕለት ጥር 30 2015 ዓ/ም  ሰማዕትነትን ተቀብለዋል።     3.  ዘማሪ ፍቃዱ ደጉ ●  የቅዱስ ሚካኤል ከሣቴ ብርሃን ሰ/ትቤት አገል...

ኢትዮጵያ የተገዳደሯትን ሁሉ ቅኝ ገዥወች የተከላከለችባቸው፣ የተዋጋችባቸውና ነጽነቷን ያስከበረችባቸው እሴቶች; በቀሲስ አስተርአየ ጽጌ

የጽዋዕ ማህበራትና ሰንበቴ ከቅድስት ድንግል ማርያም ጋራ የተሳሰሩት የጽዋ ማሕበራትና ሰንበቴወች ናቸው፡፡  ኢትዮጵያ የተገዳደሯትን ሁሉ ቅኝ ገዥወች የተከላከለችባቸው፣ የተዋጋችባቸውና ነጽነቷን ያስከበረችባቸው እሴቶች  ቀሲስ አስተርአየ ጽጌ  nigatuasteraye@gmail.com  ሚያዚያ ፳፩ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም.  (April 28, 2025)  መግቢያ  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያናችን ኩለንታዊት ቀዳማዊት ደኀራዊት፡ ዘመናዊት ናት ስትባል እም ኀበ አልቦ አይደለም፡፡ በብዙ እሴቶቿ ነው፡፡ ኩለንታዊት ከምታደርጋት ከብዙ እሴቶቿ መካከል የጽሑፌ መነሻ የሆኑት ከቅድስት ድንግል  ማርያም ጋራ የተሳሰሩት የጽዋ ማሕበራትና ሰንበቴወች ናቸው፡፡ ስንበቴ በቀጥታ ከእግዚአብሔር የታዘዘች ናት፡፡ የጽዋ ማኅበርም እንደ ሰንበቴው ቀጥታ ከግዚአብሔር ባይሆንም፡ በዮቶር በኩል ለሙሴ የደረሰው የግዚአብሔር ምሪት ናት፡፡ የጽዋ ማሕበርና ሰንበቴ የትርጉማቸው መነሻ፡ መድረሻና የመጨረሻ ዋና ዓላማቸው ሰባዊ ክብርና ነጻነት ነው፡፡   ኢትዮጵያ የተፈታተኗትን ሁሉ ቅኝ ገዥወች ከተከላከለችባቸው ከተዋጋችባቸውና ነጽነቷን ካስከበረችባቸው ዋናወቹ እሴቶቿ ውስጥ የጽዋ ማሕበራትና ሰንበቴወች ናቸው፡፡ በቅኝ ገዥወች ሲቀጠቀጡ ከኖሩት ካጎራባች አገሮች ልዩና የነጻነት ምሳሌ ያደርጓትም የጽዋ ማህበርና ሰንበቴ ናቸው፡፡ የጽዋ ማኅበራትና የሰንበቴ ድርጅቶች እንዴት ተመሰረቱ? ለኢትዮጵያ ምን ጠቀሙ? ትሩፋታቸው ምንድነው? የደርግንና የወያኔን ዘመናት እንዴት ተሻገሩ? በብልጽግና ዘመንስ እንዴት ናቸው? እንዴት ይቀጥሉ ? የሚሉትን ጥያቄወች ለመመለስ ከጽዋ ማኅበር እንጀምር፡፡   የጽዋ ማኅበር መነሻ...

ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን እና ቋንቋና ማንነት ተኮር እንቅስቃሴዎች

  ኦ ርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን እና ቋንቋና ማንነት ተኮር እንቅስቃሴዎች   ፩ . ቋንቋን በተመለከተ ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮና ትውፊት ከሰው ልጅ መበደል በፊት ፍጥረት ሁሉ የሚግባባው በአንድ ቋንቋ ነበር፡፡ “ ምድርም ሁሉ በአንድ ቋንቋና በአንድ ንግግር ነበረች” እንዲል፡፡ ዘፍ. 11፡1 በኃጢአት ምክንያት ግን ሰውና መላው ፍጥረት በአንድ ቋንቋ መግባባታቸው ቀረ፡፡ ኃጢአት እየበዛ ሲሄድ የሰው ልጅ ቋንቋም በባቢሎን ተደበላለቀ፣ አንዳቸው ከሌላቸው ጋር የማይግባቡ ብዙ ዓይነት ቋንቋዎችም ተፈጠሩ፡፡ በበደል የመጣውን ሁሉ ሊያስተካክልና ሊያድን በመጣው በአምላካችንና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አዳኝነት ያ የቀደመው ጸጋ ስለ ተመለሰልን በበዐለ ሃምሳ ሰዎች በልዩ ልዩ ቋንቋ አንድ ዐይነት የእግዚአብሔርን መልእክት ሰሙ፡፡ በዚህ ጸጋ የተጠቀሙና የበቁ ቅዱሳን የእንስሳትን ቋንቋ እስከ ማወቅ ደረጃ ይደርሳሉ፡፡   የክርስትና ጉዞ ወደ ቀደመው በአንድ ቋንቋ መግባባት መመለስ ነው፡፡ ወደዚያ ለመድረስ ደግሞ ሰው የእግዚአብሔርን ቃል በሚሰማው ቋንቋ መማር አለበት፡፡ በበዐለ ሃምሳ ጊዜ ለቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስ ብዙ ቋንቋ የገለጠላቸው ሰውን ሁሉ የእግዚአብሔርን የማዳን ጸጋ በሚሰማው ቋንቋ እንዲያስተምሩት ነው፡፡ ሆኖም ቋንቋ መልእክት ማድረሻና መግባቢያ እንጂ ከዚያ ያለፈ ሰዎችን በሆነ መደብ ለመመደብና የልዩነት አጥር ለመሥራት እንደ መሳሪያ ሊሆን አይገባውም፡፡ ይህ ከክርስትና ዐላማ ጋር ተቃራኒ ነው፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያት ወደ ዐለም ሁሉ ሲልካቸው ሰዎች የሚቀበሏቸው በሚያስተምሩት ትምህርት መሠረት ነበር እንጂ በትውልድ፣ በብሔርና በመሳሰለው መስፈርት የእኛ ናቸው/አይደሉም በሚል አልነበረም፡፡ የቤተ ክርስቲያ...