ወደ ዋና ይዘት ዘለው ይሂዱ

ልጥፎች

ከጁን, 2026 ልጥፎች በማሳየት ላይ

የትግራይ ሕዝብ መከራ የሚያበቃው ራሱን ከነጻ አውጭ ነኝ ባዩ ዘረኛ ቡድን ነጻ ወጥቶ ወደ ኢትዮጵያዊነቱ ሲመልስ ብቻ ነው

መከራ ለጸናበት የትግራይ ሕዝብ ትድረስ የትግራይ ሕዝብ ከፍተኛ ስቃይ ውስጥ ነው። ይህን የማያውቅ፣ አብሮ የማይታመም አራት አካል ነው፦ (1) የሕወሃት እና የኦነግ ዕሳቤዎች ተጠቂና በሰው ልጆች መከራ ታሪካዊ አገር አፍርሰው አዳዲስ ሪፐብሊክ በመፈጠር የስስት‹ የበተአችነት፣ የተላላኪነት ስነ ልቦናቸውን ለማከም የሚጣጣሩ ጨካኞች፤ (2) ኢትዮጵያ እንድትፈርስላቸውና ስም አጠርሯ ከዓለም ካርታ እንዲፋቅ ለብዙ ዘመናት ለፍተው በእኛው የእርስብርስ መጠፋፋት ሂደት እንድናጥፋት ሻዕብአን፣ ሕወሃትንና ኦነግን ፈጥረውን ደግፈው የጫኑብን የአድዋ ቁስለኞችና የግራኝ አህመድ መሸንፍ የሚያንገበግባቸው የውጭ አካላት፣ (3) በኢትዮጵያ መደምሰስና ቤተ ክርስቲያን መዳከም ታሪኳን ደምሰሰው በሊቢያ፣ በሶርያ፣ በየመን፣ በአልጄርያ፣ በቁስጥንጥንያ የክርስትናና አሻራ አጭልመው በደም ላይ አዲስ የክህደት መልክ ለማቆም በድማችን መፈሰስና በስቃያችን ግባቸውን ለማአስካት አጋጣሚዎችን የሚጠቀሙ ጽንፈኞች ናቸው፤ (4) ኦርቶቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያንና ክርስቲያኖችን በማዳከም በቅኝ ገዥዎቹ የማደንዘዣ እምነት ለመተካት በዙ ዘመናት የልፉቱ ቀሳጢዎች። የትግራይን ሕዝብ ለመከራ አጋልጦ 50 ዓመት ደም ያፈሰሰው፣ የስደትና የመከራ በር የክፈተው ሕወሃትና የእርሱ ፍልፍሎች ለሁሉም ኢትዮጵያን ለሚሉ የአማራ፣ የጉራጌ፣ የኦሮሞ፣ የቤኒሻንጉል ሕዝብም ሁሉ የሰቃይ ፋብሪካ የሆነውን የዘር ፖለቲካ፣ ትርክት፣ ክልል፣ ሠራዊት፣ ኢኮኖሚ፣ ጥላቻ አከፋፍለዉለታል። ከዚህ አንፃር ሁሉ ስቃይ ውስጥ ነው። የትግራይ ሕዝብ መከራ ግን ልዩ ነው። ልዩነቱ ያለው የሌላው ማኅበረሰብ የሚሰቃየው ሕወሃት በዘረጋው የዘር ፖለቲካ ነው። ችግሩን ምንጭ ከራሱ ጉያ አርቆ ይመለከተዋል፣ እናም ሐውሃትንና ፍጡራኑን ማስወገድ መፍ...

ስለ አርሲ የዘር ማጥፋት ሂደት ጳጳሳት ከሰላም ሚኒስቴር ጋር ምን ተጨባጭ ውሳኔ ላይ ደረሱ?

ባለፉት 8 ዓመታት የመንግሥት መዋቅእ ባልፈረሰባቸው የአገሪቱ ወረዳዎችና ቀበሌዎች ሁሉ በኦርቶዶክሳዊ እምነታቸው ምክንያት (በነፍጠኛ ኮድ ተደርገው ነገር ግን ቋንቋ ሳይለይ ማሰኛውንም ኦርቶዶክስ ክርስቲያን)፦ ፩) የተገደሉ ክርሰቲያኖች ቁጥር በየአጥባያው ተቆጥሮ በአደባባይ ለመንግሥት ቀርቦ ፍትሕ ይጠየቅ፤ ፪) ከቀያቸው የተፈናቀሉ ተቆጥረው ወደ ቀያቸው ይመለሱ፣ የወደመ ንብረታቸው ይተካ፣ አፈናቃዮች ሥልጣን ለቅቀው ለሕግ ይቅረቡ፤ ፫) የመንግሥት መዋቅር ላይጰተቀምጠው የዜጎችን እልቂትና መፈናቀል የመሩ፣ የተሳተፉ፣ ያልተከላከሉ፣ ከተፈጸመም በኋላ ፍተሕና ካሣ ያላሰጡ ከፌደራል እስከ ቀበሌ ተለይተው ከሥልጣን ይነሱ፣ ይከሰሱ፤ ፬) ፌደራል መንግሥት ለደረሰው ጉዳት ሁሉ በመካስ ተፈናቃዮችን በቦታቸው መልሶ በመቋቋምጨራሳቸውን የሐከላከል አቅም ይስጣቸው፣ ፭) ጸረ ኦርቶዶክስ ትርክቶች የማካሄድባቸው፣ ከመንግሥታዊ ኃላፊነት፣ ከመረጃ፣ ከኢኮኖሚ የማግለሉ አሠራር መገለላቸው በአስቸኳይ ይስተካከል ---- ----- ብላችሁ በመጠየቅ ይህንን "ተወያይተናል" የምቱልትን የ8 ዓመታቱን ዋጋቢስ ማዘናጊያና ማስፈጂያ ድራማ አለመቀጠሉን አረጋግጡልን። እረኝነታችሁን በተግባር አስመስክሩ