ወደ ዋና ይዘት ዘለው ይሂዱ

ልጥፎች

ከጁን, 2026 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ስለ አርሲ የዘር ማጥፋት ሂደት ጳጳሳት ከሰላም ሚኒስቴር ጋር ምን ተጨባጭ ውሳኔ ላይ ደረሱ?

ባለፉት 8 ዓመታት የመንግሥት መዋቅእ ባልፈረሰባቸው የአገሪቱ ወረዳዎችና ቀበሌዎች ሁሉ በኦርቶዶክሳዊ እምነታቸው ምክንያት (በነፍጠኛ ኮድ ተደርገው ነገር ግን ቋንቋ ሳይለይ ማሰኛውንም ኦርቶዶክስ ክርስቲያን)፦ ፩) የተገደሉ ክርሰቲያኖች ቁጥር በየአጥባያው ተቆጥሮ በአደባባይ ለመንግሥት ቀርቦ ፍትሕ ይጠየቅ፤ ፪) ከቀያቸው የተፈናቀሉ ተቆጥረው ወደ ቀያቸው ይመለሱ፣ የወደመ ንብረታቸው ይተካ፣ አፈናቃዮች ሥልጣን ለቅቀው ለሕግ ይቅረቡ፤ ፫) የመንግሥት መዋቅር ላይጰተቀምጠው የዜጎችን እልቂትና መፈናቀል የመሩ፣ የተሳተፉ፣ ያልተከላከሉ፣ ከተፈጸመም በኋላ ፍተሕና ካሣ ያላሰጡ ከፌደራል እስከ ቀበሌ ተለይተው ከሥልጣን ይነሱ፣ ይከሰሱ፤ ፬) ፌደራል መንግሥት ለደረሰው ጉዳት ሁሉ በመካስ ተፈናቃዮችን በቦታቸው መልሶ በመቋቋምጨራሳቸውን የሐከላከል አቅም ይስጣቸው፣ ፭) ጸረ ኦርቶዶክስ ትርክቶች የማካሄድባቸው፣ ከመንግሥታዊ ኃላፊነት፣ ከመረጃ፣ ከኢኮኖሚ የማግለሉ አሠራር መገለላቸው በአስቸኳይ ይስተካከል ---- ----- ብላችሁ በመጠየቅ ይህንን "ተወያይተናል" የምቱልትን የ8 ዓመታቱን ዋጋቢስ ማዘናጊያና ማስፈጂያ ድራማ አለመቀጠሉን አረጋግጡልን። እረኝነታችሁን በተግባር አስመስክሩ