ባለፉት 8 ዓመታት የመንግሥት መዋቅእ ባልፈረሰባቸው የአገሪቱ ወረዳዎችና ቀበሌዎች ሁሉ በኦርቶዶክሳዊ እምነታቸው ምክንያት (በነፍጠኛ ኮድ ተደርገው ነገር ግን ቋንቋ ሳይለይ ማሰኛውንም ኦርቶዶክስ ክርስቲያን)፦ ፩) የተገደሉ ክርሰቲያኖች ቁጥር በየአጥባያው ተቆጥሮ በአደባባይ ለመንግሥት ቀርቦ ፍትሕ ይጠየቅ፤ ፪) ከቀያቸው የተፈናቀሉ ተቆጥረው ወደ ቀያቸው ይመለሱ፣ የወደመ ንብረታቸው ይተካ፣ አፈናቃዮች ሥልጣን ለቅቀው ለሕግ ይቅረቡ፤ ፫) የመንግሥት መዋቅር ላይጰተቀምጠው የዜጎችን እልቂትና መፈናቀል የመሩ፣ የተሳተፉ፣ ያልተከላከሉ፣ ከተፈጸመም በኋላ ፍተሕና ካሣ ያላሰጡ ከፌደራል እስከ ቀበሌ ተለይተው ከሥልጣን ይነሱ፣ ይከሰሱ፤ ፬) ፌደራል መንግሥት ለደረሰው ጉዳት ሁሉ በመካስ ተፈናቃዮችን በቦታቸው መልሶ በመቋቋምጨራሳቸውን የሐከላከል አቅም ይስጣቸው፣ ፭) ጸረ ኦርቶዶክስ ትርክቶች የማካሄድባቸው፣ ከመንግሥታዊ ኃላፊነት፣ ከመረጃ፣ ከኢኮኖሚ የማግለሉ አሠራር መገለላቸው በአስቸኳይ ይስተካከል ---- ----- ብላችሁ በመጠየቅ ይህንን "ተወያይተናል" የምቱልትን የ8 ዓመታቱን ዋጋቢስ ማዘናጊያና ማስፈጂያ ድራማ አለመቀጠሉን አረጋግጡልን። እረኝነታችሁን በተግባር አስመስክሩ
This is a spot where I post and share part of my daily reality. I would love to hear from others too to learn how differently we interpret daily encounters including our imaginations. ይህ ሥፍራ የየዕለት ገጠመኞቼን፣ እንዴት በዕለቱ እንደተረደሁትና የማስበውን ለሌሎች ያማጋራበት ነው፡፡ የሌሎችን በመስማትና ምን ያህል ዓለማችንን በተለያየ መንገድ እንደምንመለከታት ለመማር እጓጓለሁ፡፡