ወደ ዋና ይዘት ዘለው ይሂዱ

ጭፍን መንጋነት ክፉዎችንና ሐሰተኞችን ያነግሣል

ጭፍን መንጋነት ክፉዎችን ያነግሣል!! 

ከእነዚያ ከኦነግና ሕወሃት የሐሰት ትርክት የማመንጨትና የማከፋፈል፣ ማጠልሸትና ሰብእና የመግደል ባህል የተወለዱ ከጎጠኝነት ልክፍት ልምሾዎች በሚመነጭ ፕሮፓጋንዳ የተጎዳ አንድ የዋህ እና ደግ ወዳጄ የሚከተለውን ጥያቄ በቴሌግራም ማወያያዬ ላይ ላከልኝ።

" ለመምህር. ፍታሁን ዋቄ ያድርሱልኝ ! 
ሞዓ ተዋህዶ ! ፍኖዎችን  ቀብቶ ለማንገስ !
የሚሰራ  ነው ። በማለት በተደጋጋሚ  ይሔ 
ጉዳይ  እየተነሳ ነው ። መምህር ከቻሉ  በዚህ 
ጉዳይ. መልስ ቢሰጡበት እና ! ግራ የተጋቡ 
አካላት እውነቱን እንዲረዱ ። 
እንቅስቃሴው እና አላማው ምን ላይ እንደተመሰረተ  ግልጽ ቢያደርጉት ! ጥሩ 
መስሎ ስለታየኝ ነው ።" ይላል

ለወንድሜ መልስ ለመስጠት ስጀምር እንደ ጠያቂዬ ያሉ መልካም ልብ ያላቸው ሰዎችን ወደ ግል የክፋት መሣሪያቸው የሚቀይሩትን በማሰብ ለእነርሱ ሳይሆን በእነርሱ ለሚታለሉትም እንድትሆን ብዬ የሚከተለውን መልስ ሰጠሁ:- 

"ወዳጄ የኢትዮጵያ ትልቁ መቅሰፍት ማሰብ አቁመው የተጫነባቸውን በጭፍን መንጋነት የሚሰለፉትን እና በቀላሉ ወደ  ሤረኞች  ወንጭፍና ጠጠር በመቀየር  ለጮሌዎች አድርገው  የሕዝብን ትግል ሁሉ ፍሬ ዐልቦ ለሚያደርጉት ማንቂያ ትሁን ብዬ  ነው።
 
ጭፍን ተከታዮች  በጎጥ ቡድን አድሎአዊነት ፣ ወይንም ባለማወቅ፣ ወይንም ከትግል የድል ፍሬ ከሚገባቸው በላይ ለማግኘት የሆነን ወገን ያለ አምክንዮ የመደገፍ እና  በግል ሊገኝ የሚችል ፍርፋሪ እያሰቡ፣ ወይንም ዘረኝነትና ሐሰተኛ ትርክት እንደ ትግሬ እና ኦሮሞ ነጻ አውጭ ነን ባይ አእምሮ አጣቢ እንዶዶች  የሐሰት አመንጭና አከፋፋይ የሠፈራቸውን አውራ ሀሳብ ሁሉ እንደ አእምሮአቸው ምትክ የሚያምኑና የሚከተሉ ሰዎች  መብዛት ክፉኛ ስለጎዳን ከፕሮፓጋንዳ እረፍት ወስደን እግዚአብሔር የሰጠንን እእምሮና ህሊና እንድንጠቀም ለመጎትጎት ነው።

ለጠይቀኸው ጥያቄ መልስ ከእኔ  ወይንም ከሌላ  ለማግኘት መጀመሪያ "አሉ" ያልከውን  "ማን አለ?" ብለህ በመጠየቅ ከላይ ያልኩትን መከራከራዬን  ባታረጋግጥ  ለክስ አቅርበኝና ይቅርታ ጠይቃለሁ። ሐሰትን፣ ግምትን፣ ቅዠትን ሁሉ ሳናረጋግጥ ማሰራጨት በሰብአዊ ሕግ ወንጀል፣ በእግዚአብሔር ሚዛን ኃጢአት ነው።

አጥርተን እያየን እውነቱን ለማግኘት አንድ የሳትነው ቁልፍ ጉዳይ አለ።  እርሱም እኛ ማን ነን? ለምን እንኖራለን? ለምን እንቆማለን? ለምንስ እንሰዋለን? በምንስ መስፈርት ጠላትና ወዳጅ ስንል ወገኖችን እንፈርጃለን? ለምን?  የሚሉትን  እነዚህን ጥያቄዎች እንደሚገባ ባለመመለሳችን የተውለበለበ ምላስ ሁሉ ያንሳፈናል።

 መሬት እንርገጥ። እንቁም፣ ራሳችንን እንወቅና ለሌሎች መድኅኒት፣ ብርሃንና ጨው ለመሆን እንጋደል። ክርስቶስን የማይመስል ወቅታዊ ገበያ ያሳፈፈው አርፋና አሬራ ሁሉ ከፍታ እንዳልሆነ በቀላሉ እናያለን። ቀዳዳው ከማፍሰሰሱ በፊት በእውነት ወስፌ እየወጋን እንሰፋዋለን። ሳይወጉ መስፋት አይገኝማ። እንቀባባ!

ለአንተ የምለው:- 
ከቡድን እዕሳቤ እስረኝነት አምልጥ (ምናልባት ተጠልፈህ እንደሆነ) ፣ መንጋነትህን ለእውነት ክርስቶስ ብቻ አድርግ፤  ያን ጊዜ ነጻ ትወጣለህ፣ አጥርተህም ታያለህ!! 

እያየሁ ነው ካልክ "የአማራ ትግል ሞኖፖሊ" የወሰደ ማነው? አማራን የተረጎመ ማነው? ስለ እማራ መናገርና መሥራት  ለእዚያ  ሰው እና ቡድን ብቻ ሥልጣን ማን ሰጠው?  
"ከህልውና አደጋ ወገኔን ውታደጋለሁ" ብሎ ከቤቱ ከወጣና አንዴት ውድ ነፍሱን ለመስጠት ቃል የገባለትን ሕዝብ፣   ሊያድነው የሚዋጋለትን ሕዝብ መልሶ እንዴት "እቃዬ ነው እና አትንኩብኝ" በሚል ስነ ልቦና የማሰብና አማራጭ የማየት መብቱን ስንኳ ሊገስስ ይደፋፈራል።
ትልጋይ እውነትኛ የትግለን ግብ ለማሳካት ከሆነ እና   ሊሰዋለት ከትሰለፈለት ሕዝብ ሌላ ወዳጅም፣ እምነትም፣ እውነትም አይገባውም ብሎ ይበልጣል?
 ነው ወይስ  ራሱን በስውር ለሥልጣንና ለዘረፋ ሊያዘጋጅ እና ነውሩን ጸሐይ እንዳይመታው በአመክንዮ ሳይሆን በስሜትና በፕሮፓጋንዳ አርብ መልእክት የነጠፈ እንደ ወያኔና ኦነግ መንጋ መፍጠር ፈለግ?  ማን ነው ሞዐን የመክሰስ ሞራል ያለው? 

የአማራ ሕዝብ ብዙ እያለ እንደ አናሳ ተበታትኖ በአናሳዎች ለዘመናት የተጠቃን ሕዝብን አንድ አድርጎ መምራት ተስኖት በመንደር የሐሰት ትርክት የተጠመደ፤  የድውያን ፖለቲካ ርእዮት እያመነጨ የማኅበረሰቡን ስቃይ የሚያራዝም ህሊና ቢሶችን  (ባለ ህሊናዎቹ ለወገን ልቅደም ብለው ይሰዋሉ፣ ቀማርተኞችና ህሊና ቢሶች እየ ሰው ይከተላሉ፣ በወንድም እኅቶቻቸው ደም እነርሱ ይደምቃሉ)  ከእውነተኞቹ ለይቶ መቃወም ማሰብን፣ የነጻነት ስነልቦና ባለቦትነትን፣ እፕርቄና ከግል ፍተወት ባላይ ማሰብን ይጥይቃል።

በነገራችን ላይ ይህ ሁሉ ነገሬ ለአንተ ብቻ አይደለም፣ መነሻ ሆነህ ተናገርኩ እንጂ ፤ እግረ መንገዴን ብዙ የሳቱ ወገኖቻችንን  ምልከታዬን  ለማጋራት ነው። ቅር አትሰኝብኝ። 

በፍቅር እውነትን ለመናገር ስንጨካከን ከብዙ ጥፋት እንተርፋለን።
እግዚአብሔር ያክብርልኝ። አገራችንን የምናድንበት ዓይነ ልቡና ያድለን።

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ገድሎና አስገድሎ ብፁዕ እየተባሉ መኖር የተፈቀደላቸው ጳጳሳትና ቆሞሳት እንዳይረሱ

ከጥር 27 ጀምሮ በተለያዩ የኦሮምያ ከተሞች በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቀኖና ውጭ የተሾሞና በቅዱስ ሲኖዶስ ተወግዘው የተለዩ አካላትን ወደ ቤተ ክርስቲያን እናስገባለን ባሉ የመንግስት የጽጥታ አካላት በተትኮሰ ጥይትና ሕገ ወጡ ቡድን ባደራጃቸው ወጣቶች ተደብድበው የተገደሉና የቆሰሉ  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ካህናትና ምእመናን።።   1)  ሻሸመኔ ከተማ   I.   የተገደሉ 1.  አያሌው ተረፈ ●   በሻሸመኔ የደብረ አስቦ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ማህደረ ፃድቃን ሰንበት ትምህርት ቤት አባል ●  ጥር 27 ዓ/ም በሻሸመኔ ከተማ በጸጥታ ሃይሉ በሚመራ የጨፍጫፊ ቡድን በደረሰበት ከፍተኛ ደብደባ ወደ ሆስፒታል ገባ ●  በአላቲዮን ሆስፒታል ሕክምና እየተደረገለት ሕይወቱን ማትረፍ አልተቻለም ●  በ ጥር 30 2015 ዓ/ም  ሰማዕትነትን ተቀብሏል       2.  ሊቀ ኅሩያን ቀሲስ ሐረገወይን ●  የሻሸመኔ ደብረ ስብሐት ቅዱስ ሚካኤል አገልጋይ የነበሩት ●  በሻሸመኔ በሕገወጦች በጸጥታ አካላት  በበግፍ በዱላ ተቀጥቅጠው በጭንቅላታቸው በእጅና በእግራቸው ላይ በደረሰባቸው ድብደባ በሀዋሳ ሕክምና እያሉ አርፈዋል። ●  ከመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች በተተኮሰ ጥይት ተመትተው  በያኔት ሆስፒታል ሕክምና ሲደረግላቸው ቢቆዩም ሕይወታቸውን ማትረፍ አልተቻለም። ●  በዛሬው ዕለት ጥር 30 2015 ዓ/ም  ሰማዕትነትን ተቀብለዋል።     3.  ዘማሪ ፍቃዱ ደጉ ●  የቅዱስ ሚካኤል ከሣቴ ብርሃን ሰ/ትቤት አገል...

ኢትዮጵያ የተገዳደሯትን ሁሉ ቅኝ ገዥወች የተከላከለችባቸው፣ የተዋጋችባቸውና ነጽነቷን ያስከበረችባቸው እሴቶች; በቀሲስ አስተርአየ ጽጌ

የጽዋዕ ማህበራትና ሰንበቴ ከቅድስት ድንግል ማርያም ጋራ የተሳሰሩት የጽዋ ማሕበራትና ሰንበቴወች ናቸው፡፡  ኢትዮጵያ የተገዳደሯትን ሁሉ ቅኝ ገዥወች የተከላከለችባቸው፣ የተዋጋችባቸውና ነጽነቷን ያስከበረችባቸው እሴቶች  ቀሲስ አስተርአየ ጽጌ  nigatuasteraye@gmail.com  ሚያዚያ ፳፩ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም.  (April 28, 2025)  መግቢያ  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያናችን ኩለንታዊት ቀዳማዊት ደኀራዊት፡ ዘመናዊት ናት ስትባል እም ኀበ አልቦ አይደለም፡፡ በብዙ እሴቶቿ ነው፡፡ ኩለንታዊት ከምታደርጋት ከብዙ እሴቶቿ መካከል የጽሑፌ መነሻ የሆኑት ከቅድስት ድንግል  ማርያም ጋራ የተሳሰሩት የጽዋ ማሕበራትና ሰንበቴወች ናቸው፡፡ ስንበቴ በቀጥታ ከእግዚአብሔር የታዘዘች ናት፡፡ የጽዋ ማኅበርም እንደ ሰንበቴው ቀጥታ ከግዚአብሔር ባይሆንም፡ በዮቶር በኩል ለሙሴ የደረሰው የግዚአብሔር ምሪት ናት፡፡ የጽዋ ማሕበርና ሰንበቴ የትርጉማቸው መነሻ፡ መድረሻና የመጨረሻ ዋና ዓላማቸው ሰባዊ ክብርና ነጻነት ነው፡፡   ኢትዮጵያ የተፈታተኗትን ሁሉ ቅኝ ገዥወች ከተከላከለችባቸው ከተዋጋችባቸውና ነጽነቷን ካስከበረችባቸው ዋናወቹ እሴቶቿ ውስጥ የጽዋ ማሕበራትና ሰንበቴወች ናቸው፡፡ በቅኝ ገዥወች ሲቀጠቀጡ ከኖሩት ካጎራባች አገሮች ልዩና የነጻነት ምሳሌ ያደርጓትም የጽዋ ማህበርና ሰንበቴ ናቸው፡፡ የጽዋ ማኅበራትና የሰንበቴ ድርጅቶች እንዴት ተመሰረቱ? ለኢትዮጵያ ምን ጠቀሙ? ትሩፋታቸው ምንድነው? የደርግንና የወያኔን ዘመናት እንዴት ተሻገሩ? በብልጽግና ዘመንስ እንዴት ናቸው? እንዴት ይቀጥሉ ? የሚሉትን ጥያቄወች ለመመለስ ከጽዋ ማኅበር እንጀምር፡፡   የጽዋ ማኅበር መነሻ...

ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን እና ቋንቋና ማንነት ተኮር እንቅስቃሴዎች

  ኦ ርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን እና ቋንቋና ማንነት ተኮር እንቅስቃሴዎች   ፩ . ቋንቋን በተመለከተ ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮና ትውፊት ከሰው ልጅ መበደል በፊት ፍጥረት ሁሉ የሚግባባው በአንድ ቋንቋ ነበር፡፡ “ ምድርም ሁሉ በአንድ ቋንቋና በአንድ ንግግር ነበረች” እንዲል፡፡ ዘፍ. 11፡1 በኃጢአት ምክንያት ግን ሰውና መላው ፍጥረት በአንድ ቋንቋ መግባባታቸው ቀረ፡፡ ኃጢአት እየበዛ ሲሄድ የሰው ልጅ ቋንቋም በባቢሎን ተደበላለቀ፣ አንዳቸው ከሌላቸው ጋር የማይግባቡ ብዙ ዓይነት ቋንቋዎችም ተፈጠሩ፡፡ በበደል የመጣውን ሁሉ ሊያስተካክልና ሊያድን በመጣው በአምላካችንና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አዳኝነት ያ የቀደመው ጸጋ ስለ ተመለሰልን በበዐለ ሃምሳ ሰዎች በልዩ ልዩ ቋንቋ አንድ ዐይነት የእግዚአብሔርን መልእክት ሰሙ፡፡ በዚህ ጸጋ የተጠቀሙና የበቁ ቅዱሳን የእንስሳትን ቋንቋ እስከ ማወቅ ደረጃ ይደርሳሉ፡፡   የክርስትና ጉዞ ወደ ቀደመው በአንድ ቋንቋ መግባባት መመለስ ነው፡፡ ወደዚያ ለመድረስ ደግሞ ሰው የእግዚአብሔርን ቃል በሚሰማው ቋንቋ መማር አለበት፡፡ በበዐለ ሃምሳ ጊዜ ለቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስ ብዙ ቋንቋ የገለጠላቸው ሰውን ሁሉ የእግዚአብሔርን የማዳን ጸጋ በሚሰማው ቋንቋ እንዲያስተምሩት ነው፡፡ ሆኖም ቋንቋ መልእክት ማድረሻና መግባቢያ እንጂ ከዚያ ያለፈ ሰዎችን በሆነ መደብ ለመመደብና የልዩነት አጥር ለመሥራት እንደ መሳሪያ ሊሆን አይገባውም፡፡ ይህ ከክርስትና ዐላማ ጋር ተቃራኒ ነው፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያት ወደ ዐለም ሁሉ ሲልካቸው ሰዎች የሚቀበሏቸው በሚያስተምሩት ትምህርት መሠረት ነበር እንጂ በትውልድ፣ በብሔርና በመሳሰለው መስፈርት የእኛ ናቸው/አይደሉም በሚል አልነበረም፡፡ የቤተ ክርስቲያ...