ባለፉት 8 ዓመታት የመንግሥት መዋቅእ ባልፈረሰባቸው የአገሪቱ ወረዳዎችና ቀበሌዎች ሁሉ በኦርቶዶክሳዊ እምነታቸው ምክንያት (በነፍጠኛ ኮድ ተደርገው ነገር ግን ቋንቋ ሳይለይ ማሰኛውንም ኦርቶዶክስ ክርስቲያን)፦ ፩) የተገደሉ ክርሰቲያኖች ቁጥር በየአጥባያው ተቆጥሮ በአደባባይ ለመንግሥት ቀርቦ ፍትሕ ይጠየቅ፤ ፪) ከቀያቸው የተፈናቀሉ ተቆጥረው ወደ ቀያቸው ይመለሱ፣ የወደመ ንብረታቸው ይተካ፣ አፈናቃዮች ሥልጣን ለቅቀው ለሕግ ይቅረቡ፤ ፫) የመንግሥት መዋቅር ላይጰተቀምጠው የዜጎችን እልቂትና መፈናቀል የመሩ፣ የተሳተፉ፣ ያልተከላከሉ፣ ከተፈጸመም በኋላ ፍተሕና ካሣ ያላሰጡ ከፌደራል እስከ ቀበሌ ተለይተው ከሥልጣን ይነሱ፣ ይከሰሱ፤ ፬) ፌደራል መንግሥት ለደረሰው ጉዳት ሁሉ በመካስ ተፈናቃዮችን በቦታቸው መልሶ በመቋቋምጨራሳቸውን የሐከላከል አቅም ይስጣቸው፣ ፭) ጸረ ኦርቶዶክስ ትርክቶች የማካሄድባቸው፣ ከመንግሥታዊ ኃላፊነት፣ ከመረጃ፣ ከኢኮኖሚ የማግለሉ አሠራር መገለላቸው በአስቸኳይ ይስተካከል ---- ----- ብላችሁ በመጠየቅ ይህንን "ተወያይተናል" የምቱልትን የ8 ዓመታቱን ዋጋቢስ ማዘናጊያና ማስፈጂያ ድራማ አለመቀጠሉን አረጋግጡልን። እረኝነታችሁን በተግባር አስመስክሩ
የመንግሥት 10 ዋና ተግባር እና ቀዳሚ ኃላፊነት 1) የዜጎችን ደኅንነት ማረጋገጥ፣ 2) ከሁለገብ ሥጋት መከላል፣ 3) የማንኛዉም ዜጋ አካልና ነፍስ፣ ሞራልና ህሊና እንዳይቆስል መከላከል፤ 4) የታወቁ መሠረታውያን መብቶችን መጠበቅና ማስጠበቅ፣ የ 5) ተረጋጋ የዜጎችና ማኅበራዊ መስተጋብሮቻቸው በታውቁና ተገማች፣ ተአማኒ የሕግና የፍት ሥርዓት ማረጋገጥ፣ 6) የምጣኔ ሀብት እደገት፣ የማኅበራዊ ልማት፣ ትምህርትና ጤና ወዘተ በሚፈለገው ፍጥነት፣ ስፋት፣ ነጻነት እንዲሄድ መሥመር ማሳየት እና --- ለሚፈጽሙት ዜጎች እድል ማመቻቸት --- የግልና የወል ጥረቶችን መደግፈና መጠበቅ 7) ከውጭ ጠላት መከላከል 8) የዓለም አቅፍ ግኑኝነቶችንና ጂኦ ፖለቲካዊ ፍላጎቶችን በጠበበ ጠቃሚ ማድረግ 9) ሕግ ማስከበር 10) ብዝኃነትን ማመጋገብና ጠቅላይ፣ አናባቢ የጋራ ትርክትና እሤቶችን ማጠናከር፣ አፍራሾቹን መከላከል ለምን እነዚህ 10ሩ አስፈላጊ ሆኑ? ምክንያቱም ያለ አተቃላይ የዜጎችና የማኅበራዊ መስተጋብሮቻቸው ድኅንነት፡ 1) ሰዎች መሥራት፣ መማር፣ ቤተ ሰብ መመሥረትና ማስተዳደር አይችሉም 2) ነጋዴዎችና አራሾች፣ ተመራማሪዎችና የፈጠራ ሰዎች ውጤት ተስፋ አድርገው መዋዕለ ንዋያቸውን፣ ጉልበታቸውንና ዕውቀታቸውን አያፈሱም፣ ቢያፈስሱም መተግበርና መፈጸም አይችሉም፤ 3) ማኅበረሰቦች እርስብርሳቸው አይተማመኑም፣ የጋራ ግብና ርእይ ላይ አይተባበሩም፣ ለውስጥ ቀውስና ለውጭ ወረራ የተጋለጡ ይሆናሉ 4) መንግሥታዊና ማኅበራዊ ተቋማት ኃላፊነታቸውን ለመወጣት የሚያስችላቸው አፈጻጸም ማረጋገጥ አይችሉም፤ ...