ወደ ዋና ይዘት ዘለው ይሂዱ

ኢትዮጵያን የሚመጥን መሪ ለመፍጠር መስፈርት ላይ ሀሳብ እናዋጣ!

ኢትዮጵያን የሚመጥን መሪ ለመፍጠር መስፈርት ላይ ሀሳብ እናዋጣ!

በሰው ደም ካልታጠቡ፣ በዜጎች ዕንባ ካልዋኙ አየር የተነፈሱ የማይመስላቸው  ድውያነ አእምሮ፣ የክፋት አበጋዞች፣ የሐሰት ምንጮች፣ የሤራ መሀንዲሶች እና የቁማር ሱሰኞች ዳግም እንዳይነዱን ከፈለግን ከጭፍን መንጋነትንወጥተን እናስብ!!!

እኔ ለማስጀመር እንዱህ ብያለሁ። እናንተስ?
👉 በነፍሱም በሥጋውም ርኲሰትን የሚጸየፍ፣ ውድቀት ሱያጋጥመው መልሶ በንስሐ የሚታደስብትሁት

👉 ሐቀኛ፦ ለፍትሕ እና ለእውነት የሚኖር፣ ሤራና ቁማርተኝነትን፣ በዜጎች መካከል እድልዎን የሚጸየፍ ደግ አባት/እናት

👉 የህፕገሩቷን የሺ ዘመናት ታሪክ አመዱን ከፍሙንለይቶ ለዛሬ ትውልድ ሙቀትና ከፍታ ወደ ሞተር የሚቀይት፣ የሐሰት ትርክትን፣ ታሪካዊ ጠባሳዎችን አጣምሮ እያጋነነ ለዜጎች ተዋህዶ እንቅፋት የማያኖር፣ የሚከላከል

👉 በሀገሩ ልጆች አእምሮ፣ ጥረትኔ ምክር የሚተማመን፣ የባዕዳን አሻንጉሊትና ተላላኪ ያልሆነ

👉 የቀጠናዊ፣ አህጉራዊና ዓለም ዐቀፋዊ አውዱ ንባብና በሀገሩ ላይ ያለውን  አዎንታዊና አሉታዊ ተጽእኖ ተረድቶ ለሀገር ጥቅም በሁሉም ደረጃ  አመራር እንዲኖረን ስልት መንደፍና መተግበር የሚችል አቅም ያለው፣ እንደ ስድ አደግ ባለጌ ጎሮምሳ ዘለቄታዊነትንየሌለው ግኑኝነት የማፕፈጥር

👉 በጎረቤት ሀገራት መካከል ሰላም ለምስፈን ክሂሎትና ጥበብ ያለው፣ ያሉትን መልካም አጋጣሚዎች የሚጠቀም ብቻ ሳይሆን የሚፈጥር

👉 በሀገር ውስጥ ያሉትን ብዝኃ እምነቶችና ባህሎች። የስነ ምህዳር ብዝኃነት፣ የትፈጥሮ ህብት ብዝኃነትን ሁሉ ለግጭትና ለሽሚያ ያይደለ ለጉድለት መሞላላትና ሕብረታዊንየሕይወት አንድነት እንደ ተቃራኒ ጾታ ተዋህዶ ለፍሬ መምራት የሚችል

👉  ከሀሉ በላይ ክንረ-ሰብእ፣ ክብረ-ሀገር፣ ክብረ፣ ነባርብእሤትና ታሪክ ላይ ቅሚያ የሚሰጥ፣ ጎጠኝነትና ዘረኝነት፣ ሌብነትማ ብልጣብልጥነትን የሚጸየፍ

👉 የሀገሩን ጥበብና እውቀት በመዋቅሬዊ።መንግድ የሚያለማ፣ ሁለገብ የሀገር ጥገኝነትን የሚከላከል

👉 ለእህዚአብሔርና ለሚመራው ሕዝብ ተጠሪና በእረኝነት ተላልፎ የሚሰጥ፤ የማዘዣ ክፍልና የስለላ መዋቅር ተጠቅሞ ዜጎቹን ለጦርነትና ለግጭት  የማያሰልፍ ሰላም ወዳድ

👉 ለጋስና ስለ ዜጎዥ ፍትሕፕዊ ከሀብት ክፍፍል የሚገደው፣ ከሙስናና ሌብነት ጋር ግልፅ ጦርነት የሚያካሄድ

👉 ለሀገራችን ወዳጅ የሚያበዛ ዲፕሎማሲና ትስስር የመፍጥር አቅም ያለው፤ ጠላት የሚቀንስ፣ እንደተናካሽ እብድ ውሻ ሁሉን የማይለክፍና ተለዋዋጭ ያልሆነ

👉 መሪነቱን ለተሻሉ አእምሮዎች የሙያጋራ፣ አግባብነቱ በሌሎች ብልጫ እንደተወስደበት ሲመለከት ሥልጣኑን አስረክቦ በትህትና በአማካሪነት ለመሥራት በጎ ፈቃድ ያለው፣ ሥልጣን ላይ ለመቆየት በምርጫ ስም የማያጭበረብር፣ የሚበልጡትን ወገኖቹን እንደ ጠላት ፈርጆ የማያሳድድ የዋህ ቤተስብእ

👉 ማኬቬሉያዊ የደም እርካብና መንበርን የሚጸይፍ የእውነት ሰው

በሰው ደም ካልታጠቡ፣ በዜጎች ዕንባ ካልዋኙ አየር የተነፈሱ የማይመስላቸው  ድውያነ አእምሮ፣ የክፋት አበጋዞች፣ የሐሰት ምንጮች፣ የሤራ መሀንዲሶች እና የቁማር ሱሰኞች ዳግም እንዳይነዱን ከፈለግን ከጭፍን መንጋነትንወጥተን እናስብ!!!

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ገድሎና አስገድሎ ብፁዕ እየተባሉ መኖር የተፈቀደላቸው ጳጳሳትና ቆሞሳት እንዳይረሱ

ከጥር 27 ጀምሮ በተለያዩ የኦሮምያ ከተሞች በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቀኖና ውጭ የተሾሞና በቅዱስ ሲኖዶስ ተወግዘው የተለዩ አካላትን ወደ ቤተ ክርስቲያን እናስገባለን ባሉ የመንግስት የጽጥታ አካላት በተትኮሰ ጥይትና ሕገ ወጡ ቡድን ባደራጃቸው ወጣቶች ተደብድበው የተገደሉና የቆሰሉ  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ካህናትና ምእመናን።።   1)  ሻሸመኔ ከተማ   I.   የተገደሉ 1.  አያሌው ተረፈ ●   በሻሸመኔ የደብረ አስቦ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ማህደረ ፃድቃን ሰንበት ትምህርት ቤት አባል ●  ጥር 27 ዓ/ም በሻሸመኔ ከተማ በጸጥታ ሃይሉ በሚመራ የጨፍጫፊ ቡድን በደረሰበት ከፍተኛ ደብደባ ወደ ሆስፒታል ገባ ●  በአላቲዮን ሆስፒታል ሕክምና እየተደረገለት ሕይወቱን ማትረፍ አልተቻለም ●  በ ጥር 30 2015 ዓ/ም  ሰማዕትነትን ተቀብሏል       2.  ሊቀ ኅሩያን ቀሲስ ሐረገወይን ●  የሻሸመኔ ደብረ ስብሐት ቅዱስ ሚካኤል አገልጋይ የነበሩት ●  በሻሸመኔ በሕገወጦች በጸጥታ አካላት  በበግፍ በዱላ ተቀጥቅጠው በጭንቅላታቸው በእጅና በእግራቸው ላይ በደረሰባቸው ድብደባ በሀዋሳ ሕክምና እያሉ አርፈዋል። ●  ከመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች በተተኮሰ ጥይት ተመትተው  በያኔት ሆስፒታል ሕክምና ሲደረግላቸው ቢቆዩም ሕይወታቸውን ማትረፍ አልተቻለም። ●  በዛሬው ዕለት ጥር 30 2015 ዓ/ም  ሰማዕትነትን ተቀብለዋል።     3.  ዘማሪ ፍቃዱ ደጉ ●  የቅዱስ ሚካኤል ከሣቴ ብርሃን ሰ/ትቤት አገል...

ኢትዮጵያ የተገዳደሯትን ሁሉ ቅኝ ገዥወች የተከላከለችባቸው፣ የተዋጋችባቸውና ነጽነቷን ያስከበረችባቸው እሴቶች; በቀሲስ አስተርአየ ጽጌ

የጽዋዕ ማህበራትና ሰንበቴ ከቅድስት ድንግል ማርያም ጋራ የተሳሰሩት የጽዋ ማሕበራትና ሰንበቴወች ናቸው፡፡  ኢትዮጵያ የተገዳደሯትን ሁሉ ቅኝ ገዥወች የተከላከለችባቸው፣ የተዋጋችባቸውና ነጽነቷን ያስከበረችባቸው እሴቶች  ቀሲስ አስተርአየ ጽጌ  nigatuasteraye@gmail.com  ሚያዚያ ፳፩ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም.  (April 28, 2025)  መግቢያ  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያናችን ኩለንታዊት ቀዳማዊት ደኀራዊት፡ ዘመናዊት ናት ስትባል እም ኀበ አልቦ አይደለም፡፡ በብዙ እሴቶቿ ነው፡፡ ኩለንታዊት ከምታደርጋት ከብዙ እሴቶቿ መካከል የጽሑፌ መነሻ የሆኑት ከቅድስት ድንግል  ማርያም ጋራ የተሳሰሩት የጽዋ ማሕበራትና ሰንበቴወች ናቸው፡፡ ስንበቴ በቀጥታ ከእግዚአብሔር የታዘዘች ናት፡፡ የጽዋ ማኅበርም እንደ ሰንበቴው ቀጥታ ከግዚአብሔር ባይሆንም፡ በዮቶር በኩል ለሙሴ የደረሰው የግዚአብሔር ምሪት ናት፡፡ የጽዋ ማሕበርና ሰንበቴ የትርጉማቸው መነሻ፡ መድረሻና የመጨረሻ ዋና ዓላማቸው ሰባዊ ክብርና ነጻነት ነው፡፡   ኢትዮጵያ የተፈታተኗትን ሁሉ ቅኝ ገዥወች ከተከላከለችባቸው ከተዋጋችባቸውና ነጽነቷን ካስከበረችባቸው ዋናወቹ እሴቶቿ ውስጥ የጽዋ ማሕበራትና ሰንበቴወች ናቸው፡፡ በቅኝ ገዥወች ሲቀጠቀጡ ከኖሩት ካጎራባች አገሮች ልዩና የነጻነት ምሳሌ ያደርጓትም የጽዋ ማህበርና ሰንበቴ ናቸው፡፡ የጽዋ ማኅበራትና የሰንበቴ ድርጅቶች እንዴት ተመሰረቱ? ለኢትዮጵያ ምን ጠቀሙ? ትሩፋታቸው ምንድነው? የደርግንና የወያኔን ዘመናት እንዴት ተሻገሩ? በብልጽግና ዘመንስ እንዴት ናቸው? እንዴት ይቀጥሉ ? የሚሉትን ጥያቄወች ለመመለስ ከጽዋ ማኅበር እንጀምር፡፡   የጽዋ ማኅበር መነሻ...

ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን እና ቋንቋና ማንነት ተኮር እንቅስቃሴዎች

  ኦ ርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን እና ቋንቋና ማንነት ተኮር እንቅስቃሴዎች   ፩ . ቋንቋን በተመለከተ ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮና ትውፊት ከሰው ልጅ መበደል በፊት ፍጥረት ሁሉ የሚግባባው በአንድ ቋንቋ ነበር፡፡ “ ምድርም ሁሉ በአንድ ቋንቋና በአንድ ንግግር ነበረች” እንዲል፡፡ ዘፍ. 11፡1 በኃጢአት ምክንያት ግን ሰውና መላው ፍጥረት በአንድ ቋንቋ መግባባታቸው ቀረ፡፡ ኃጢአት እየበዛ ሲሄድ የሰው ልጅ ቋንቋም በባቢሎን ተደበላለቀ፣ አንዳቸው ከሌላቸው ጋር የማይግባቡ ብዙ ዓይነት ቋንቋዎችም ተፈጠሩ፡፡ በበደል የመጣውን ሁሉ ሊያስተካክልና ሊያድን በመጣው በአምላካችንና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አዳኝነት ያ የቀደመው ጸጋ ስለ ተመለሰልን በበዐለ ሃምሳ ሰዎች በልዩ ልዩ ቋንቋ አንድ ዐይነት የእግዚአብሔርን መልእክት ሰሙ፡፡ በዚህ ጸጋ የተጠቀሙና የበቁ ቅዱሳን የእንስሳትን ቋንቋ እስከ ማወቅ ደረጃ ይደርሳሉ፡፡   የክርስትና ጉዞ ወደ ቀደመው በአንድ ቋንቋ መግባባት መመለስ ነው፡፡ ወደዚያ ለመድረስ ደግሞ ሰው የእግዚአብሔርን ቃል በሚሰማው ቋንቋ መማር አለበት፡፡ በበዐለ ሃምሳ ጊዜ ለቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስ ብዙ ቋንቋ የገለጠላቸው ሰውን ሁሉ የእግዚአብሔርን የማዳን ጸጋ በሚሰማው ቋንቋ እንዲያስተምሩት ነው፡፡ ሆኖም ቋንቋ መልእክት ማድረሻና መግባቢያ እንጂ ከዚያ ያለፈ ሰዎችን በሆነ መደብ ለመመደብና የልዩነት አጥር ለመሥራት እንደ መሳሪያ ሊሆን አይገባውም፡፡ ይህ ከክርስትና ዐላማ ጋር ተቃራኒ ነው፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያት ወደ ዐለም ሁሉ ሲልካቸው ሰዎች የሚቀበሏቸው በሚያስተምሩት ትምህርት መሠረት ነበር እንጂ በትውልድ፣ በብሔርና በመሳሰለው መስፈርት የእኛ ናቸው/አይደሉም በሚል አልነበረም፡፡ የቤተ ክርስቲያ...