"ሰው ሳትሆን ሰው አትምራ፣ ተመሪዎችን በልክህ ትከረክማቸዋለህ" የሚል ብሂል ላስተዋውቅ መሰለኝ?
በሕይወት ከምመለክተው የእኛ ሀገር ዋና የችግር መንጭ
(1) ሰውን የማያውቁ የሰው መሪዎች እና
(2) ሃይማኖት የሌላቸው የሃይማኖት መሪዎች ድምር ነፍስንም ሥጋንም እየጎዱ ነው።
እነዚህን ለመታገል የሚነሳ ማንኛውም ግለሰብእ ታጋይ ወይንም መሪ እራሱ ከእነዚህ መቅሰፍቶች ለመቃረን፦
"ሰው" መሆኑን፣ ፈሪሃ እግዚአብሔር እንዳለው፣ ለራሱ የግል ፍተወት መርኪያነትና የባዕዳን ማኅደርነት የሚያገለግል አለመሆኑን ማረጋገጥ ይኖርበታል።
ከአጥፊ እንታደጋችኋለን፣ ለህልውናችሁ እንድትታገሉ እንመራችኋለን እያሉ "ሰውን" የማያውቁ፦
--› ስው ሳይሆን ብሔረ-ስብእ፣
--› አማኝ ሳይሆን ካህንና ጳጳስ፣
--› በእውነት ላይ ቆመው ሐርነት ሳይኖራቸው "ነጻ አውጭ ፣ የህለውና ታዳጊ፣ መሪ ወዘተ" ባዮች የአዳዲስ መከራ ፈልፋዮች እንጂ መፍትሔዎች ሊሆኑ አይችሉም።
----- የሥልጣንና የዝና ጥማት ያደነቆራቸውና "ሥጋ ብቻዎችን" (ክብር-ነፍስን የማያውቁ የሆድ ሎሌዎች) መሪ ከማድርግና ሥጋ ብቻ ከመሆን ራስን መጠበቅ፣ ማሰብ፣ ማሰላሰል፣ በእምነት መጽናትን እንለማመድ። ለበለጠ ዐሳብ --› ይህን ይመልከቱ፣ ይሟገቱ፣ አዳዲስ "ሰውነትን" ያገናዘበ ዐሳብ ያመንጩ።
ሰውን የማያውቁቱ የጎጥ ባሮች በሰጡኝ ስሜ "ጃል" ዋቄ. ነኝ
በሕይወት ከምመለክተው የእኛ ሀገር ዋና የችግር መንጭ
(1) ሰውን የማያውቁ የሰው መሪዎች እና
(2) ሃይማኖት የሌላቸው የሃይማኖት መሪዎች ድምር ነፍስንም ሥጋንም እየጎዱ ነው።
እነዚህን ለመታገል የሚነሳ ማንኛውም ግለሰብእ ታጋይ ወይንም መሪ እራሱ ከእነዚህ መቅሰፍቶች ለመቃረን፦
"ሰው" መሆኑን፣ ፈሪሃ እግዚአብሔር እንዳለው፣ ለራሱ የግል ፍተወት መርኪያነትና የባዕዳን ማኅደርነት የሚያገለግል አለመሆኑን ማረጋገጥ ይኖርበታል።
ከአጥፊ እንታደጋችኋለን፣ ለህልውናችሁ እንድትታገሉ እንመራችኋለን እያሉ "ሰውን" የማያውቁ፦
--› ስው ሳይሆን ብሔረ-ስብእ፣
--› አማኝ ሳይሆን ካህንና ጳጳስ፣
--› በእውነት ላይ ቆመው ሐርነት ሳይኖራቸው "ነጻ አውጭ ፣ የህለውና ታዳጊ፣ መሪ ወዘተ" ባዮች የአዳዲስ መከራ ፈልፋዮች እንጂ መፍትሔዎች ሊሆኑ አይችሉም።
----- የሥልጣንና የዝና ጥማት ያደነቆራቸውና "ሥጋ ብቻዎችን" (ክብር-ነፍስን የማያውቁ የሆድ ሎሌዎች) መሪ ከማድርግና ሥጋ ብቻ ከመሆን ራስን መጠበቅ፣ ማሰብ፣ ማሰላሰል፣ በእምነት መጽናትን እንለማመድ። ለበለጠ ዐሳብ --› ይህን ይመልከቱ፣ ይሟገቱ፣ አዳዲስ "ሰውነትን" ያገናዘበ ዐሳብ ያመንጩ።
ሰውን የማያውቁቱ የጎጥ ባሮች በሰጡኝ ስሜ "ጃል" ዋቄ. ነኝ
============
ሰው የማይታወቅበት አመራርና አስተዳደር በኢትዮጵያ
ሰውነትን ያላወቁ ሰው ነን ባዮች ከመክራችን ሊገላግሉን አይችሉም! ጭፍን መንጎች እየተከተላችሁ መከራችሁን አታራዝሙት!
ለሰው ያለን ትርጉ እንኳ አላግባባ ይበለን? ለብልጽግና ወንጌል እና ለዘረኞች፣ ለብዚኃኑ ኢትዮጵያዊ ግን ትርጉሙ ለሺ ዘመናት ታውቆ የኖረና የተኖረለት ግልጽ ማኅበራዊ፣ ሃይማኖታዊ፣ ፖልቲካዊ፣ ሳይንሳዊ ትርጉም አለው።
ዛሬ ሰው የብሔረ ሰብ ነጻ አውጭዎች ፖልቲካዊ ርዮት ትርጉም ያንሳል፤ ለብልጽግና ወንጌል መንግሥት መሪዎች ሰው ከችግኝ፣ ከአስፋልት ማስፋት ሥራ፣ ከመናፍሻ፣ ከፎቅ ርዝመት፣ ከባልሥልጣን ምቾትና ቤተ መንግሥት ሁሉ ያነሰ የባልሥልጣን መጠቀሚያ መሣሪያ ነው።
የሰው ትርጉም በመዛባቱ ምክንያት ሙሉ ሰብእና (ህሊና እና ፈሪሃ እግዚአብሔር፣ ክብር-ሰበ) ያላቸው ሰዎች ከሚርዱት ተርጉም ሁሉ በተለየ “ሰውነትን” ዝቅ ባደረጉ የኑዑስ-ማንነትን በፖልቲካ ብያኔ ከሚተረጉሙ የዘመናችን የሀገር መቅሰፍቶች የፖለቲካ መንጋዎች ጋር በሚከተሉት ወሳኝ መግባቢያና የእሤት መሠረት ከሚመሩት ቃላት ትርጉም ላይ ተቃራኒ ጎራ ይዘናል፦
መዳን፣ ሰላም፣ መብት፣ ብሔረ-ስብእ፣ እኩልነት፣ “የራስ ዕድል” በራስ መወሰን፣ ሀገር፣ ሕዝብ፣ ኦሮሞ፣ አማራ፣ ትግራዋይነት፣ ህልውና፣ ተግል፣ ሃይማኖት፣ ሰው፣ ሴት፣ --- ወዘተ ሁሉ ላይ አዲሱ የአዲሲቷ ኢትዮጵያና እኛ በሰውነታችን ጸንተን ከምንገኘው ጋር አንግባባም።
ስለዚህ ሕዝብን ከእንዚህ የቁም ሙታን መሪዎች ጥፋት ለመገላገል ትግል ውስጥ የገቡትን እንምራ የምትሉ ወገኖቻችን ከብልጣብልጥነት ውጡ፤ የትዛባውን የመግባቢያዎቻችንን ቃላት፣ ከሁሉም በላይ “ሰውን” ተርጉማችሁ ንገሩን!! ከስሑታኑ መቅሰፍቶቻችን የምትለዩበትን እምነታችሁን፣ ርእያችሁን፣ ርእያችሁን ለማሳካት የምትከተሉትን መርህ፣ የምትመሩበትን ፖልቲካዊ ርእዮት ግልጽ አድርጉት። “የእገሌ ብሔርተኝነት” የሚለውን የድንቆሮዎች ጡሩምባ መንፋት አቁሙ። በእምነት ቤት የምትምሩም እግዚአብሔርን አክብራችሁ አክባሪ በማፍራት ሰውን ማዳን ሲገባችሁ እግዚአብሔርን ክዳችሁ፣ ሆዳችሁን አምልካችሁ ሰውነትን አታጥፉት።
አስተያየቶች