ኤዲያ! ራስህን ተከላከል!
ምን የማይለቅ ጽኑ አዚም ነው ኦርቶዶክስ ክርስቲያኑን የተፀናወተው?
አታልቅስ! ሰሚ ወገን የለህም! ካለቀስክ ውድ እግዚአብሔር ብቻ!
እንዴት የሚገድልህ መንግሥት ሊታደግህ ይደርስልሃል? ነው መንግሥት ይድረስልኝ እያልክ ፯ ዓመት ሙሉ ምን ሆንክ አላየኸውም?
ራስህን ተከላከል! ነፃ አውጭም መፍትሄ ሰጭም የለም። በቤተመንህሥትም ሆነ ብቤተ ክህነት የተካድክ፣ እረኞች ግድ ይህን እያወደሱና ካባ እያለበሱ "በርታልን፣ እኛን ብቻ ከድሎታችን አታፈናቅለን ብለው አላግጠውብሃል።
መፍትሄው አንድ ሆኖ መነሳት ብቻ ነው።
ለነገሩ የጎሣ ፖለቲካ ጭፍን መንጋ ለ፶ ዓመታት ያጠቃውን የሃይማኖትና የቋንቋ መለያ የለጠለፈለትን ክፍለ-ሕዝብ በግልፅ እና በመደበኛ ሠራዊት እየጨፈጨፈው እንደተለመደው "መንግሥት ይድረስልን" የምትል ድምጽ ከወደ ወለጋ ዛሬም ቀጥሏል።
አዚሙ ምንድነው? አጥፉውን ድረስልን የሚል እንደ ኦርቶዶክስ ክርስቲያን የደነዘዘ ዜጋንየለም!!!
የባእዳኑ ተላላኪዎች ገብቷቸዋል፣ በጎሣ መንጋነት ከከፋፈልናቸው እንኳን ምእመኑ መነኩሴውና. ጳጳሱም ዳግም ተመልሶ የክርስቶስ አንድ መንጋ መሆን አይችሉም ብለው ሠርተዉበት አሁን የምናየውን ጎጠኛ፣ በደም ውስጥ ቆሞ የግል ፍተወቱን የሚያርካ፣ የአንድ እምነትና ቋንቋ ባለቤትና ተጠቂ የሆነውን አማራን ሕዝብ እንኳ የሚከፋፍል ሆኖ አገኙት። ፈነጩበት።
ከዘረኛ ፖለቲካ የበለጠ የአማራ ጠላቱ ጎጠኛና ናርሲሱስት ባህርይ ያላቸው የፋኖና የዲያስፖራ ደጋፊያቸው ነው። እነዚህ ቅርብ አዳሪ ጎጠኞች ከህዝብ ሞይ፣ ስደት፣ መራብ፣ የሕፃናት ትምህርት ማጣት፣ የወጣት በጤርነት መጠበስ፣ የማኅበረንሰብ መፍረስ በሁለተኛ ደረጃንየሚመለከቱት ነው። አምልኮአቸውን የሚፈጽሙት በሤራና ጎጠኝነት በየሥርቻው ፈጥረው ከሙከተሉት የቡድን ጣዖታቸው ነው።
ከእነዚህ መፍትሄ አትጠብቅ! አምላክህን እግዚአብሔርን ይዘክ፣ ትዳር ማርክስ፣ ማመንዘር፣ በደም-መላሽነት ንጹህ ደም ለማፍሰስ ማቄሙን አቁመህ፣ በሥጋ ወደሙ ታትመህ፣ ባንዳና ጎጠኛን ከመካከልህ መንጥረህ ዝመት ትድናለህ!
አታልቅስ! ሰሚ ወገን የለህም! ካለቀስክ እይቀር ወደ እግዚአብሔር ብቻ!!
አስተያየቶች