ለሁኔታችን የሚመጥን መሪ እንዴት እንወቅ?
#በአብይ እና ከርእዮት ወላጆቹ ከአመጡብን መከራ ተነስተን ስለ መሪዎች ሰብእና ምን እንማራለን?
==========
#አብይ አህመድ እርሱን ከፈጠሩት ቀዳሚ ዘረኛ መሪዎች በመርከብ በሀገራችን ላይ ያደረሰውና እያደረሰው የሚገኘው ጉዳት ካሣ የማይገኝለት ቢሆንም አንድ ትልቅ ውለታ ለትውልዱ ውሏል።
እርሱም የፖለቲካ መሪዎችን በምላሳቸውና በብልጣብልጥ ንግግሮቻቸው እና በአዲስነትና ለውጥ ሽፋን ምን ያህል ሕዝብን አደንዝዘው በማስከተል ወደ አጠቃላይ ውድቀት ሊወስዷቸው እንደሚችሉ ማሳየቱ ----
እንደ እኔ ግምት ከአሁን በኋላ ትውልድ ሁሉ የፖለቲከኞችን የመጨርሻ ደረጃ ህሊና ቢስነትና የማታለል አቅማቸው ተገንዝቦ መሪዎችን ለመምረጥና ለመታዘዝ ከስሜትና ንግግር ባሻገር በግልጽ መሥፈርት ብቻ እንዲመዝን ትምህርት አግኝቷል እላለሁ።
ስለዚህ -----
መሪ ስንመርጥ ስንከተልና ስን ታዘዝ አስቀድመን በሚከተሉት ነባር ሰብአዊ እናቶች መመዘኛ መሆን ይኖርበታል ብለን የምንግባባ ይመስለኛል:-
፩) ፈሪሃ እግዚአብሔር እንዳለው በአጠቃላይ ሕይወቱ ያስመሰከረ
፪) ለራሱ ሳይሆን ለሚመራቸው ወገኖቹ ለመሰዋት ዝግጁነቱን በተግባራዊ ሕይወቱ ያረጋገጠ፤
፫) ተክለ ሰውነቱን መንጋ አጫፋሪዎችን በጎጥ፣ በጥቅም፣ በተስፋ እያጓጓ በማሰማራት የማይገነባ ትሁትና እውነተኛ፣ በተግባር ብቻ ከፍ የሚል፣#
፬) ወገንተኝነቱን ከጎጥና ከጎሣ ነጻ አውጥቶና እርሱም ወጥቶ ለክብር-ሰብእ፣ ለፍትህ፣ ለእውነት ፣ ለአሁንና ለመጭው ትውልድ ሁለንተናዊ ደኅነት ማድረጉን በተግባር ያስመሰከረ፤
፭) በግል ሕይወቱ ከስግብግብነት፣ ፍቅር ንዋይ፣ ዝሙት፣ ትዳርን ከማርከስ፣ ከሤራ፣ ከከፋፋይነት፣ ከነፍሰ ገዳይነት፣ ፍርድ ከማጣመም እጅግ የራቀና የንጽሕና እና ፍትሐዊነት አርአያ ለመሆን የሚጣጣር፤
፮) በወገኖቹ በኢትዮጵያውያን የጋራ ጥቅሞች ላይ ከጀርባ ከባእዳን ጋር በመደራደር ለግል ሥልጣን የመሥራትን ከሻዕብያ፣ ሕወሃት፣ ኤነግ ውፕዘተ ወደ ትውልዱ የገባውን ክህደት የሙጸየፍ፤
፯) አሁን ለአለውና ለመጭው ትውልድ በሚጠቅም ስሌት ለሀገሩ ወዳጅ የሚያበዛ፣ ጠላት የሚቀንስ ግኑኝነት ላይ በማተኮር የሚታወቅ
፰) በብልሆች ብሔራውያን ሊቃውንት በባህሎችና እምነቶች ሊቃውንት ምክር የደረጀና አስተዋይነቱ ከትህትናና አድማጭነት ጋር የተስማሙለት፤
፱) ራሱን ከፍ ከፍ የማያደርግ፣ ሌሎች የእርሱን ጉድለት የሚሞሉለት መሪዎችን አክብሮ የሚተባበር፣ ከእኔ ወንድም እኅቶቼ ይሻላሉ በሚል እውነት፣ ትህትና ሥልጣኑን ለማስረከብ ዘወትር የሚጋብዝ፤
፲) ሐሰትን፣ ሤረኝነትን፣ የክፋት ቡድነኝነትን፣ የትንኮል መረብን ሳይሆን በፍትህ እውነትን በሰብአዊነትና በሀገር/ሕዝብ ትስስር መተማመንና ህብረት ላይ አተኩሮ የሚሠራ ለመሆኑ ያለፈ ታሪክ ያለው፤
፲፩) ከኢትዮጵያ ሀገራዊ፣ እምነታዊና ባህላዊ የቀኑ እሤቶችና ሁለንተናዊ ሀብታት አንጻር ተጻራሪነት ካላቸው የኮሚኒስት፣ የቅኝ ገዥ ወራሪዎች፣ ከክፋፋይ የጎሣና ውጭ-ገብ አሉታዊ አስተሳሰቤች ጋር ህብረት ፈጥሮ እንደማያውቅ ምስክርነት ያለው
፲፪) በግል የሥልጣንና ሀብት ፍተወት ያልተለከፈ
---- ሰው ብቻ መሪ እንዲሆን ያለ ፍርሃት ይሉኝታና ማስመሰል ትውልዱ እንዱሠራ፣ ከመንጋናንጎጥ ፖለቲካ ጋር በጠላትነት እንዲቆም #የአብይ አህመድ እና ጓዶቹ ነውርና ግፍ ትውልዱን ያስተምረዋል የሚል ተስፋ አለኝ።
ከ#አብይ እና ተመሳሳዮቹ ይእርሱ የርእዮት ወላጆቹ ከአመጡብን የህልውና አደጋ ለመገላገል ሌሎች #አብይ (አብይ-ዎችን) በጭፍን መከተል ከረመጥ ወደ ፋመ እሣት መሸጋገር ይሆናል።
አስተያየቶች