ራሳችንን እንጠይቅ⁉️ ምን ነካን⁉️ የማያድን ፍርሃት ለምን እንፈራለን ⁉️
ሃምሳ ዓመት ሙሉ እንዲገድሉን ለምን ፈቀድን?⁉️
የሚያስገድሉንና ከገዳዮቻችን ጋር የሚተባበሩትን ምንደኞች እንዴት እረኛ ባለን ተቀበልን⁉️
እግዚአብሔር ሲፈጥረን ከሰጠን የመዳን ጸጋዎች መካከል አንደኛው ወደ ፍጹም ፍቅር እስክንደርስ ድረስ እርሱን በመፍራት ከጥፋት መጠበቅን ነው።
#ቅዱስ #ዳዊትና ሰሎሞን "የጥበብ ሁሉ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው" አሉን፤ ለፍጹማን መነኮሳት የሚመክረው ሶሪያዊው ቅዱስ ይስሃቅ (ማር ይስሃቅ) "የጥበብ ሁሉ መጀምሪያ እግዚአብሔርን ማፍቀር ነው" ሲል "ፍርሃት" ወደ ፍቅር ማድረሻ መሆኗን ይጠቁመናል።
ጌታችን "ሥጋን የሚገድሉትን አትፍሩ፣ ይልቁንም ስጋና ነፍስን አዋህዶ በሲዖል ሊቀጣ የሚችለውን እግዚአብሔርን ብቻ ፍሩ" ብሎናል።
ከእነዚህ መልእክቶች የሚያድን ፍርሃትና የሚገድል ፍርሃት መኖሩን እንረዳለን።
እኛ በዚህ ዘመን ያለን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ክርስትና ተከታዮች ፍርሃንታችን የሚገድልና የሚያስገድለው አይነት ፍርሃት ነው።
የሚያድነው ፍርሃት እግዚአብሔርን ብቻና ብቻ በመፍራት የእውነት ምስክርነት (ሰማእትነት) ሕይወት መኖር ነበር። ይህ አይነቱ አኗኗር በሥጋም፣ በንፍስም ነጻነት እንድናገኝ አባቶቻችን ኑረዉት ባስረከቡን ነጻ ሀገርና ብርሃን በሆኑ ቅዱሳን ታሪኬቻችን ይታወቃል።
ዛሬ ያለነው ሀገር ተነጥቀን፣ ቤተ ክርስቱያናችን የምንደኛ መንጋ ተንሰራፍቶባት፣ ታሪካችን ባእዳን አሠልጥነው ምሁራን ባሰኟቸውና ለሀገራቸው ዕንቁ ምሥጢር በማወቅ ዘርፍ ደንቆሮ የሆኑ፣ መዋስ እንጂ ማሰብን እርም ያደረጉ ሰዎች ጠልሽቶ፣ ፖለቲካችን እኛን በማጥፋት ፕሮጀክት ላይ ተዋቅሮ፣ እንደ ወያኔና ኦነግ፣ እንዲሁም እነርሱ ተዳቅለው ባስገኙት የጭንጋፎች መሰብሰቢያ በሆነው የብልጽግና ወንጌል መንጋ ጥቃት ሥር ስንኖር የምንፈራ እግዚአብሔርን ሳይሆን ጠላቶቻችን እነርሱን ነው።
በዚህ ምክንያት እውነት መናገር፣ ፍትህን መሥራት፣ ግፍን መቃወም፣ ሐሰትን መሞገት፣ ራስን መከላከል፣ አንድ ሆኖ ለሰብአዊብክብር መረጋገጥ መነሳት ሁሉ ተሰውሮናል።
የተለማመድነውና በተለይ ከማኅበራዊ ሚዲያ ጋር ተጣምሮ የወረስነው ጎጅ ዐመል:-
፩) እውነት የሚናገሩትን በአሉታዊ መንገድ ማዳከም፤
፪) ሰይጣንም ቢሆን ሥልጣንና የቁስ ሀብት ያለውን ሁሉ የትክክለኝነትና የእውነት ሚዛን ማድረግና ማጎብደድ፣
፫) ያለ አመክንዮአዊ ተጠየቅ ሩቅ ቆሞ በጭፍን መቃወም ወይንም መደገፍ
፬) በሌሎች መስዋእትነት ነጻነትና ሰላም እንዲገኝ መጠበቅ
፭) ሀገርን ለጠላት ሰጥቶ መሰደድ
፮) ከእውነት፣ ከሰብአዊነት፣ ከፍትህና ከፈሪሃ እግዚአብሔር አስበልጠን ለጎጥና ቋንቋ ቡድን ጥብቅና መቆም
፯) የሰይጣን ድግስም ቢሆን በደመቀበት ሁሉ ማጨብጨብ፣ የእህዚአብሔርን የምስጋናን ዜማና ቅኔ ሁሉ ለሆድ መሙያ ለጠላት ሳይቀር ማወደሻ ማድረግ ፣ ወዘተ በእግዚአብሔርና ህሊና ባላቸው የሰው ልጆች ዘንድ ሁሉ የተጸይፉ ጠባዮቻችን ናቸው።
እልቂት እጣ ፈንታዬ ነው ያለው ኦርቶዶክሳዊን ዜጋና በአባትነት ስም በዓላት እያደመቁ፣ እርስ በርሳቸው እየተመሰጋገኑ፣ ከአድርባዮችና አስመሳዮች የቅኔ ሙገሳ እየተቀባበሉ መኖር የማይሰለቻቸው የሐሰት እረኞች፣
እና
መንግሥት ሆኖ የመንግሥትነት ወግ ለአንድ ዕለት ስንኳ ማሳየት የተሳናቸው ከሰውነት ዝቅ ያሉ ድውያን የሚጫወቱበት ሕዝብ አንድ ሆኖ ይህ ግፍ ይቁም ለማለት ምን አገደው?
እየገደለ የሚገዛ መንግሥትን መንህሥቴ፣ እያስገደለ የሚጠብቅ እረኛን እረኛዬ፣ ሁለቱንም የቤተ መንግሥትና የቤተ እምነት ሸክሞችን አዝሎ ለምንንቀጠለ?
ሕዝብ የራሱን ሞትና ስደት ለመከላከል ዝግጁ መሆን አቅቶት፣ ጸሎተ ፍትሀትና የሰማእትነት ክብር ተነፍጎት ለምን በመከራው ይቀጥላል?
መልሱ የቱ ነው?⁉️
፩) እፕሁንም ነጻ አውጭ እየጠበቀ?
፪) መንግሥት ልብ ገዝቶ እንደ ሰው ሊመለከተኝና ሊከላከልልኝ ይጀምራል ብሎ?
፫) ሲኖዶሱ በክርስትና አባትነቱ ድምጽ ይሆነኛል ብሎ?
፬) ፋኖ ይደርስልኛል ብሎ?
፭) ከመሞት ሌላ ምርጫ የለኝም ብሎ ተስፋ ቆርጦ ለሞት ወድዶ ተሰልፎ?
፮) ሀገርህ በሰማይ ነው በዙህ ምድር መጨፍጨፍ ያጸድቀኛል ብሎ አምኖ?
፯) የታወጅበት ጦርነት ከምድረ ገጽ ሊያጠፉት የተማማሉት በብልጽግና አስተባባሪነት የሚመሩ፣ በዘረኝነት፣ በዉሀቢ ጽንፈኛ፣ በሰይጣን አምናኪዎች፣ በቁስና መሬት አምላኪዎች ((ለፌ ፊ ለፋ (አጥንትና መሬት) Blood & Soil)) በሚሉ በሽተኞች ጥምረት መሆኑን፣ ካልተሸነፈ በስተቀር መግደል የማያቆም የአራዊቶች ፕሮጄክት መሆኑን መረዳት ተስኖት?
ለምን ሽባ ሆንን⁉️
ብቻ የኢትዮጵያ ሕዝብ በአጠቃላይ ሰውነቱን ያዋረደው ለምንንይሆን? ግማሹ የወያኔ፣ ሌላው የኦነግ ኦሮሙማ፣ ትግራዋይነት ወዘተ (ከሂትለር Germenness ተቀድቶ. በOromoness የተውሶ ምሁርነት የተቀመረ መሆኑ ነው) አምላኪ ሆኖ ሃምሳ ዓመት ሙሉ በተጋተው ሀሰተኛ ትርክት፣ በቃዠው በሌላው መቃብር ላይ የሚጨብጠው ታላቅነት እየተመራ ለምን ከትልቅና ሰፊ ሀገሩ፣ ከረዥሙና አኩሩ ታሪኩ ወርዶ በቋንቋና በቦታ ጠብቦ በማሰቡ ቀጠለ?
በመላውብሀገሪቱንስለሚጨፈጨፉ፣ ስለሚፈናቀሉ፣ ከእምነት ስለሚፈልሱ፣ ተሰድደው ሀገርዐልባ ባዛንኝ ስለሚሆኑ ልጆቹ የማይገደውን ሲኖዶስ ተብዬ የጎሣ ፖለቲካ ባሮችን ስብስብ እንዴት "ቅዱስ" ጉባኤንእያለ መጃጃሉን ቀጠለ?
እንዳው በአጠቃላይ ምን ነካን?⁉️
አስተያየቶች