ይበቃል! ታሞ ከመማቀቅ አስቀድሞ መጠንቀቅ እንዲሉ የበሽታው ምልክት ታይቷልና ሕክምና ያስፈልጋል!!!
አምላክ የለሾች፣ ሀሰትኞች፣ የባእዳን ዕሳቤ ባሮች የድፕቅኑትን የህልውና አደጋ ለመቀልበስ የተሰለፈውን ክቡር የሰው ልጅ ሕይወት እየከፈሉ፣ በተቃራኒው ሕይወቱን የሚሰጠውን ማኅበረ-ሰብእ ሃይማኖት፣ እሤት፣ ነባር ትርክት ከጀርባ ለማጥቃት መሞከር ከባድብክህደትም ኃጢአትም ነው።
" ጸረ-ኦርቶዶክስ ካልሆንን ትግል አይሳካም" የሚል መዝሙር የማነው? መልስ ይፈልጋል። ፶ እና ከዚያም እጥፍ የሆነውን ሕዝብ የእሤትና የማነት ምንጭ የሄነችዋን ኦርቶዶክሳዊት ክርስትና እንደሌለች ቆጥሮ ፖለቲካና ትግል ለማካሄድ ማሤርን ከደርግ፣ ከኦነግ፣ ከወያናና ከድቅል ልጃቸው ከብልጽግና ወንጌሉ ፖለቲካዊ ኦሮሙማ ውጤቱን አጭደናል። ተምረናል። የአማራንም ተጋድሎ ጠልፎ በጸረ-ኦርቶዶክስ አጀንዳ መበከል ተቀባይነት አይኖረዉም።
ይህንን በአቃፊነት ስም ያልተጻፈውን፣ በተክባር አግልሎ የማያውቀውን አማራነትና ኢትዮጵያዊነት በጠላት በጠለሸ ትርክት እየተመሩ "ሃይማኖታዊ መብቶችን ካነሳን አንድ መሆን አንችልም" የሚል ውሃ የማያነሳ ማደናገሪያ ከፊት አስቀድመው በኦርቶዶክስ ክርስትና ላይ መርዛቸውን የሚረጩ አንዳንድ ድብቅ ተልእኮ ይዘው ፋኖ ውስጥ የሰረጉትን ወገኖች በጥንቃቄ መመልከትን ችላ አንልም።
አንድነትህን ያደነቃቀፈው እስልምናና ክርስትና ሳይሆን የሥልጣን ጥምና ጎጠኝነት፣ ሤረኝነትና ራስ ወዳድነት፣ ከዚያንካለፈ ድብቅ የጠላት ተልእኮ፣ ተሸካሚነት ወይንም ይትግሉን ውስብስብነትና የሚጠይቀውን ጥንቃቄ ያለማወቅ ድንቁርና ሊሆኑ ይችላሉ።
አማራን እንደ ኮድ አድርጎ ኦርቶዶክስን ለማጥፋት ፶ ዓመት ሙሉ የመጥውን አስተሳሰብ ለማሸነፍ የሚዋጋው ወገን እንደ ጠላቱ "እግዚአብሔር አያስፈልገኝም፣ የኦርቶዶክስ ንቅናቄ የእማራ ትግል ጠላት ነው" ለማለት ደፈረ? ይህ መልእክት መልእክት በዝግ የማኅበራዊ ሚዲያ ቡድን ሲብላላ ቆይቶ የሚቃወም የለም በሚል ስሌት አደባባይ ወጣ።
በዚህ ጉዳይ ፋኖዎች ትኩረት ሰጥተው መምከር ይኖርባቸዋል። ተሸፋፍነው ቢተኙ የመገላለጥ ሰዓት መኖሯ አይቀርም። በአማራ ትግል ውስጥ ከሚሳተፉ ሰዎች መካከል በሚከተሉት ደዌ የተለከፈ ከአለ ይመርመር፦
- ጸረ ሰሎሞናዊነት
- ጸረ ኦርቶዶሳዊነት
- ጸረ ኢትዮጽያዊነት
- ጸረ ነባርነትና ታሪክ ክለሳ
- ጎጠኝነት
- አማራ "ንብረቴ፣ መጠቀሚያዬ፣ የብቻዬ" የሚል የዘር ነጻ አውጭ መንፈስ ቁራኝነት
- ናርሲሲስት #አብይ-ነት ( የበዛ ራስ ወዳድነትና ማን-አህሎኝነት)።
የዚህ አይነት ደዌኛ ሲገኝ በፍጥነት ከአማራ ታጋዮችና ሕዝብ ለይቶ በማቆያ መእከል ማከም ይገባዋል። በሽታው ተላላፊና መጨረሻው አሁን አማራ የተጸየፈውን እና የሚዋጋውን ኢሰብአዉነት፣ ኢፍትሀዊነት፣ ጭፍን መንጋነት እና ስግብግብነት መልሶ ከጠላቶቹ በመውረስ ከሕወሃትና ኦነግ/ብልጽግና እኩል የሚያዋርድ ነው።
ይህን በዝምታ ማለፍ ለአማራ የሥጋ ህልውናውን ማሳጣት ብቻ ሳይሆን የዘላለም ሕይወቱንም መንጠቅ ይሆናል። በዚህ መንገድ የተጓዙት ሕወሃትና ኦነግ/ብልጽግና ያስከተሉትን መንጋ ከእምነት አስወጥተው ብሔርተኝነትን በጣዖት ደረጃ ያስመለኩ፣ ሲኖዶስና መጅልስን የጎሣ አገልጋይ ያደረጉ፣ በአድባባይ ይግራዋይነት እና ኦሮሙማ ከሃይማኖት ይበልጣል እስ ከማለት የደረሱ፣ መነኮሳትና ካህናተ ክትስቶስን በዘር ደልድለውና የክልል ሲኖዶስ ፈጥረው አንደ እካለ-ክርስቶስ ምእመናን በፕሮፓጋንዳ አጨልመው ንጹህ ዘርና ዲቃላ ያሰኙ ጽቋቁርብሂትለሮች ሆነዋል።
አማራንም "ለህልውናህ" እየታገልኩልህ ነው ብለው ራሳቸውን ለመስዋእትነት ያቀረቡ ወጣቶችን እየማገዱ ከእግዚአብሔር የሚለይ መንገድ ለመውሰድ ማሤር የነውር ነውር፣ የግፍ ሁሉ ግፍ ነውና ኦርቶዶክሳዊንየሆነ ብቻ ሳይሆን ሰው በእምነት መኖርንየሚገባው ፍጡር መሆኑን የሚቀበል ሁሉ ሉቃወመው ይገባል።
ለሥጋህ ህልውና ቆሜልሃለው፣ ነፍስህ ግን ገሃነም ትግባ የሚል ፋኖ ሱገኝ የአማራ ጠላትብእንጂ ወዳጅ ሊባል አይችልም። እንዲህ አይነት ስውር ጠላቶች ሀሳብን በሀስብ መሞገት ስለማይችሉ ሤራቸውን ሰውረው በስሜታዊ ጉዳዮች ያጭበረብራሉ። ከማጭነርበሪያዎቻቸው መካከል የሚከተሉት የተለመዱ የፋሽቶች ስልቶች ናቸው:-
፩) የተቺውን ደምና አጥንት ቆጥሮ "አንተ በአማራ ጉዳይ ማን ፈትፋች አደረገህ"
፪) አንተ ለምሳሌ እኔን "ጃል ዋቄ" ነህ
፫) ሃይማኖት ይዘህ አትምጣብን (ትግላችን አምላክ የለሽ እና የጠላቶቻችን አምሳል አራዊታዊ ነው እንደማለት ያል አማራን የማይመስል ክርክር)
፬) እኛ እገሌ የሞባል መሲህ፣ ዐስበን የፈጸምነው ፍጹም ሀሳብ ስላለን ሌላ ማሰብ አያስፈልገንም፣
፭) አማራ የማያስብ፣ እኛ ብቻ የምናስብለት በእጃችን ያለ ግዑዝ መሣሩያችን ስለሆነ ሌላ መልእክት አታስተላልፉለት
፮) ጥልቃ የምይገቡብን ሥልጣን ፈልጋችሁ፣ እኛን ለመከፋፈልና ለማዳከም ነው ---- ወዘት ይሏችኋል።
ቁም ነገሩ ይህ አይነት ማደናገሩያን እየሰሙ ጸውስጥ ጠላትን ሤራ እንዳይገለጥ የሚከላከሉ የዋሀን መብዛት አደጋውን ማክፋቱ ነው። ከትግራይ ሕዝብን ነጻንላደርጋችሁ ነውንተከተሉኝ ብለው ሀገር አስግንጥለው፣ ሌላውን አናልሰው፣ ሀገሩን ዘርፈውና ሕዝቡን አለያይተው፣ በመጨርሻ ከታላቅ ሀገሩ ይልቅ መንደርንእያሰበ በአውራጃና ወረዳ ይገባኛል የሚገድልና የሚሞት ትውልድ ፈጠሩ፣ መቶ ሽዎች እናቶችን ያለ ልጅ አስቀሩ።
አማራ ከዚህ ተምሮ ትግሉን ግልጽ በሆነ መርህ፣ እግዚአብሔርንና ክብረ-ሰብእን ማእከል ባደረገ ዕሳቤ የህልውና ይግሉን ከግብ በማድረስ ለሰው ሁሉንፋይዳ ያለው ሥርዓት ማቆም ይጠይቃል።
አስተያየቶች