ትንሳዔን የምናከብረው እኛ ራሳችን ልንነሳ ነው! አዘቅት ውስጥ ሆነው ክንፍ ስላበቀሉት መዘመርና በዓል ማክበር በእግርም አያራምድም! በንስሐ ለመብረር መነሳት ይቀድማል!
ትንሳዔን የምናከብረው እኛ ራሳችን ልንነሳ ነው! አዘቅት ውስጥ ሆነው ክንፍ ስላበቀሉት መዘመርና በዓል ማክበር በእግርም አያራምድም! በንስሐ ለመብረር መነሳት ይቀድማል! በ2014 ተጽፎ የተሰራጨ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቀዳማዊ ቃል ነው፥ ያቃል እግዚአብሔር ነው፥ ያቃል በአግዚአብሐየር አብና በአግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ዘንድ ነበረ። ያ ቃል ሰው ሆነ። ለምን? እኛ በገዛ ፈቃዳችን ከሕይወት አልባውና በሐሰቱ ራሱን ካጠፋው ከሰይጣን ጋር ተወዳጅተን፥ የሕይወት ምንጭና መሠረት ከሆነው ከእግዚአብሔር በአመጻችን ተለይተን ሙታን ሆንን። ከዚህ አይነት ከሕይወት ምኝጭና መሠረት ከእግዚአብሔር በመለየት ሚሞቱት ሞት በፍጡር ኃይልና ጥበብ፥ ተጋድሎና ምልጃ መዳን አይቻልም። ከዚህ አይነት ሞት መዳን የሚቻለው በማይሞት፥ በጥበቡ በሞት ላይ ሥልጣን ባለው፥ በደልን መሰረዝ በሚችል፥ ሙቶ ሞትን ድል በሚነሳ፥ በሁሉ ላይ ሥልጣን ባለው አካል ብቻ ነው። ይህ ደግሞ እግዚአብሔር ብቻ ነው። እርሱ ከሶስቱ አካል አንዱ ቃል ከባርሕይ አባቱ ከአግዚአብሔር አብ እና ከባሕርይ ሕይወቱ ከእግዚአብሔር መንፍስ ቅዱስ በመለኮት ሳይለይና ሳይንስ በተለየ አካሉ ቃል ከእመቤታችን ከቅድሰት ድንግል ማርያም ሞት የሚስማማውን የእኛን ሥጋና ነፍስ ነስቶ በመዋሀድ ስለ እኛ ለመሞት ፈቀደ። ከአዳም በደልና ጉስቁልና ነጻ አድርጎ ከጠበቃት ከእናታችን ሰው ሆነ፥ አርሱን የሚመለከት አንዳች ኃጢአትና በደል ሳይኖርበት እኛ በነፃ ፈቃዳችን መርጠን ስለሞትንበት አመጽ አርሱ እኛን ተገብቶ መከራ ተቀበለ፥ ታመመ፥ ሞተ፥ መለኮት በተዋሐደው ሥጋው ወደ መቃብር፥ መለኮት በተዋሐዳት ነፍሱ ወደ ሲዖል ወርዶ ከሞ...