ረዥም ያልተቆራረጠ የሥነ መንግሥት ያላት አገራችን ኢትዮጵያ ብዙ ጠላት ያፈሩላት ጸጋዎች አሏት። በተፈጥሮ ከምትገኝበት የመልክዐ ምድር አቀማመጥ ጀምሮ ሕዝቧ ካዳበረው የነጻነትና የጸረ ቅኝ ግዛት ጋር ተጣምሮ ነባር እሤቶችና የአፍሪካ መግቢያ በር፥ የአባይ ወንዝ መነሻ፥ የቀይ ባህርና የህንድ ውቂያኖስ መተላለፊያ የመቆጣጠር አቅም የሚሰጣት አቀማመጧና የገናና ታሪኳ መመለስ አስፈሪነት፥ በዓረብና በአፍሪካ ድንበሮች አካባቢ መኖሯና አፍሪካን የጓሮ አርሻቸው፥ የተለያዩ አደንዛዥ እምነቶቻቸው ማራገፊያነት እንቅፋት መሆኗ፤ እንዲሁም ልዩ የተፈጥሮና የማዕድናት ሀብት ባለቤትነት፥ የሕዝቡ ጥበብኝነትና የጀግንነት ታሪክ፥ የአክሱምና ቀዳሚ ሥልጣኔ የመመለስ እድል ሁሉ ዓይን ውስጥ አስገብቷታል።
ፖረቱጋል፥ ኦቶማን ቱርክ፥ ጣሊያን፥ ኢንገሊዝ፥ ጀርመን፥ ፈረንሳይ፥ አሜሪካ ዛሬ የአውሮፓ ሕብረት፥ ሩሲያ፥ ቻይና፥ ግብጽ ወዘተ ወደ አፍሪካ አህጉር፥ ወደ ህንድ ውቅያኖስ፥ ወደ ቀይ ባሕር ሲመለከቱ የኢትዮጵያን አቅምና ሚና ከጥቅማቸው አንጻር የመበየን ፍላጎታቸውን መግታት አይችሉም። በዚህም ኢሰብአዊና ኢፍትሐዊ ፍልስፍናን ከሤራ ጋር ቀምረው፥ አገር በቀል ባንዳን መረማመጃ አድርገው ኢትዮጵያ ያለማቋረጥ በሁለገብ ጥቃት ሥር ማኖራቸው ይታወቃል። ይህ ሂደት በትንሹ ከ15ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ጀምሮ አገሪቷን ሲያቆስላት፥ ሲቆነጻጽላት፥ ከህንድ ውቅያኖስ ባለቤትነት ወደ ባህር በር አልባነትና አሁን ወዳለዉ የክልል አፓርታይድ ሥርዓት ያደረሳት ነው።
ሂደቱ ከቀጥታ ወረራ ጀምሮ፥ የንግድ በር መዝጋት፥ አገርን አንድ ሉዓላዊ ሕዝብ በጎኃና በእምነት ዘውግ ከፋፍሎ ማጋጨት፥ በመጨረሻ በትምህርትና በእውቀት ስም ልጆቿን አእምሮ በማጠብና በመከፋፈል በባዕዳንና በተውሶ ርአዮተ ዓለም ሺ ዘመናት አገር ያቆመውን ስነ መንግሥት የሚያጠፋና የሚቃረን መንግሥታዊ ሥርዓት እና ሥርዓተ ትምሕርት በአገር ላይ የሚያጸኑ ቡድኖችን መፍጠር ችለዋል። ዛሬ የምንገኘው ኢትዮጵያዊነትን፥ ነባር እምነቶችንና ባህሎችን፥ የኢትዮጵያን የግዛት አንድነትና ሉዓላዊነት፥ ከሁሉም በላይ የአማራን ማኅበረሰብና ኦርቶዶክሳዊ ክርስትናን በዋና ጠላትነት የፈረጁ የጎሣ ነጻ አውጭዎችና ከፋፋዮች የፖለቲካውን ሥልጣንና አውድ የተረከቡበት ግዜ ነው። በዚህ የጥፋት አውድ ውስጥ የአማራን ሕዝብ፥ ኦርቶዶክሳዊ ክርስቲያንን፥ ነባር እስልምንና ባህሎችን የማጥፋት ግብ ያለው መንግሥት ሥልጣን በመያዝ የዘር ማጥፋት መርሐግብርን ዘርግቶ እየከወነ ነው።
ስለሆነም ይህ የቡድናዊ ጥቃትንና ሀገራዊ ጥፋትን ለመታደግ የአማራ ሕዝብ ልጆች ከሌሎች ኢትዮጵያዊያን ጋር ጥምረት በመፍጠት ሀገራዊ የቁልቁልት ጉዞውን ለማስቆምና የማኅበረሰብ አንድነት ለማምጣት የአንድነት ሚዲያ በመመሥረት ውይንም አሁን ካሉት መካከል በመምርጥ በማጠናከር ዙሪያ ኢትዮጵያውያን በተለይ ለሰው ልጅ እኩልነት፣ ለሀገር ሏአላዊነትና አንድነት፣ ለፍትህ፣ አሁን ቦርቶዶክሳውያንና አማራ ላይ የተቃጣውን የህልውና አድጋ ለመቀልበስ፣ የተዘራውን የ50 ዓመት የጎሣ ፓርቲዎችና ምሁራን መርዛማ የሐሰት ትርክት ማጽዳት ላይ እንዲተኮር ምክረዐሳብ ያላችሁ በዚህ ቴሌግራም ላይ አጋሩን https://t.me/+Sl9K6hQuMjFmNzU8 ።
አስተያየቶች