ከዝክረ ኒቂያ ምን እንጠብቅ?
በትንሹ ከዚህ በታች ያለውን ጉዳይ የመፍትሔ አቅጣጫና ቀኖና ነው፦
(1) በጎሣ ፖለቲካ እየተመራ የተሾሙ ኤጲስቆጶሳትና ጳጳሳት እንዲሁመ መለካዊነት፣ ሲሞናዊነት፣ ዘረኝነት በደዌ ደረጃ የተጣባቸው፣ በቁሳዊ ሃብት ማጋበስ ምንኩስናን ያዋረዱ ወገኖቻችን ሕይወት የሚመዘንበትና የሚታረምበት ውሳኔና ቀኖና ማወጅ፤
(2) ምእመናንን በጎጥና በቋንቋ፣ በትርክት፣ በውጭ-ገብ የፖለቲካ ርእዮተ ዓለም ክርስቲያኖችን መከፋፈሉን፣ እያጭራርሰ እንደሚገኝ፣ የጎሣ ሲኖዶሳት እየትፈለፈሉ በመሆኑ የተከተለውን የምእመናን መለያየት፣ መጠላላት፣ መዋጋት፣ ተበትኖ ለክርስትና ጠላት ለሆኑት አካላት የተመቻቹ መሆናቸውን ያገናዘበ ኦርቶዶከሳዊ መመሪያና ለመእመንና ለካህናት ማስተላለፍ፤
(3) አርአያ ምንኩስናን በማራከስ በከተማ የከተሙ መነኮሳት፣ ሀብት በማፍራት ላይ በማተኮር ምእመናንን፣ ካህናትን አጠቃላይ የቤተ ክርስቲያን ተልእኮን የዘነጋ አኗኗርን የሚመለከት ግልጽ የእርምት መመሪያና ቀኖና፤
(4) ሲኖዶስ የጳጳሳት ብቻ እንጂ የካህናትና ምእመናን ተሳትፎ የሌለበት ሆኖ መቀጠሉ ያስከተላቸውን ጥቅሞችና ጉዳቶች በመገምገም ለወደፊቱ ግልጽ የሆነ የተሳታስፊዎች፣ የአጀንዳ አቀራርጽ፣ የውሳኔ አሰጣጥና አፈጻጸም ቀኖና ፤
(5) በምእመናን ላይ በመንግሥት የተፈጸመውን ጭፍጨፋ፣ ማፈናቀል፣ ሲኖዶስ ውስጥ የሚገባውን ጣልቃ ገብነት፣ የገዳማትና አድባራት፣ መናኒያን መደፈርን፣ የነገረ መለኮት ት/ቤቶችና ማሠልጠኛዎች ከመናፍቃን መምህራን፣ ከመናፍቃን መጽሐፍትና ኮርስ የመጠበቅነ አሠራርና የሊቃውንት መዋቅራዊ ተሳትፎ መበየን፤
(6) የሚሊዮኖች መመናን ፍለሰት የውስጥና የውጭ መንሴዎችና መፍትሔዎችን በግልጽ ማሳየትና ለመፍትሔው ቀኖናዊ ግዴታ ያለባቸውን የቤተ ክርስቲያን መዋቅራትን ቀጣይ ድርሻ፣ የአፈጻጸም ክትትል ሥራዓት ማመላከት፤
(7) ኦርቶዶከሳዊነትን የሚጻረሩ ሐገራዊና ክልላዊ ሕጎችን በሚመለከት ምእመናን ምን አይነት ክርስቲያናዊ ምላሽ መስጥት እንድሚግባቸው ግልጽ ቀኖናዊ መመሪያ፤
(8) በጎሣ ፓርቲዎችና ሊቃውንት ቤተ ክርስቲያንን፣ እርሷ የቀባቻቸው ነግሥታትን፣ ታሪከን፣ አስተምህሮዎችን፣ ሃይማኖትን የአንድ ጎሣ ቋንቋ ተናጋሪ በማድርገ ፈርጆ ማጥቃትን፣ የጨቋኝና የተጭቋኝ ትርክት በመተርክ ቤተ ክርስቲያንን አጥፊ ተብሎ ከሚሰየመው ወገን አድርጎ በመዋቅር ማጠቃት ላይ በሚገኘው የፖልቲካ ሥራዓት አንጻር ምእመናን፣ ካህናት፣ ኦርቶዶክሳውያን ምሁራንና ሊቃውንት ሊወጡት የሚገባቸው ድርሻን የሚያሳይ ቅኖናቂ መመሪያ መስጠት፤
(9) የቤተ ክርስቲያን ሥራ መፈጸሚያ የሆነው ከመንበረ ፓትሪያርክ እስከ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን በተዝረጋው መዋቅር ላይ የተሰየሙ ኃላፊዎች ሁሉ ምእመናን ከማብዛት፣ ከማጽናት፣ ከመጠበቅ፣ አንድነታቸውን ከዘርም ሆነ ከዘመናዊ የአቅሌሲያው ቅዱስ ሕብረት የሚነጥል ሁኔታ በመጠበቅ አንጻር የሚገመገሙበትና የሚጠየቁበት አሠራር እንዲኖር አቅጣጫና ቀኖና ማስቀመጥ
(10) የቤተ ክርስቲያን የገንዘብና የሰው አስተዳደር ማእከላዊ አመራርና ስርጭት ኖሮት አገልግሎት ከከትማ ክምችት ወደ ጠረፍና ገጠር እንዲወጣ የማድርገ አቅጣጫ ማስቀመጥ
(11) መነኮሳት ሀብት ከማፍራት የታገዱ እንዲሆኑ ነባሩን ቀኖና ማጽናትና የአፈጻጸም መመሪያ መስጠት፤
(12) የጎሣ ሲመተ ጵጵስና እንዲሻር ቀኖናውን መመለስ፣ በየክፍለ ሀገሩ ዘርኞች የሚመሠርቱት ፖለቲካዊ ሲኖዶስ ምእመናን እንዳይከትሉ፣ ቢከተሉ በንፍሳቸው ላይ የሚምጣውን ጥፋት የሚያሳይ መግለጫና ትምህርት መስጠት፤
(13) ሥራዓተ ገዳም፣ ሥራዓተ ምንኩስና፣ መነገጃ የሆነው ጸበል፣ ስለ መሳለም ጉዞና ሥራዓቱ፣ የካህናትና መነኮሳት አለባብስ፣ የመመናን ጋብቻ፣ ውርጃ፣ ቅድመ ጋብዛ ዝሙት፣ የዘር ፖልቲካ ወዘት የትብራራ ቀኖና
(14) አጠቃላይ የቤተ ክርስቲያን መዋቅርና የመንግሥት መዋቅር ግኑኝነት፣
(15) የቤተ ክርስቲያን ሚዲያ የምእመናን (የአጥቢያ፣ ወረዳ፣ ሀገረ ስብከት ጉዳዮቸ፣ የትምህርት) ንብረትና ጉዳይ መነጋገሪያ እንዲሆን ህግ መድንገግ
(16) ኦርቶዶክሳውያን በየአጥቢያው ተመዝግበው እንዲታወቁ፣ አስተዋጾአቸው ብቻ ሳይሆን መፍናቅል፣ መገለል፣ መግደልና ልዩ ልዩ ምንግሥታዊና ማኅበራዊ ጥቃቶች መዝገብና ሥርጭት ሥራዓት እንዲዘርጋ
(17) የቀደሙ ለክርስትና መልካም ነግሥታት ክብር፣ አሁን ክፋት የሚፈጽሙትን የመውቀስ
(18) የቤተ ክርስቲያን ተከታዮች ዕቅበትና የመዋቅሩን ኃላፊዎች ተጠያቂነት ግልጽ ማድረግ
(19) በስደትና በውጭ ስላለችው ቤ/ክ፣ አስተዳደር፣ መመናን፣ ካህናት አገልግሎትና አኗኗርን የሚመለከት ቀኖናና አሠራር ማመልከት
ስ/rSGreMfBtOw
አስተያየቶች