ወደ ዋና ይዘት ዘለው ይሂዱ

በኦርቶዶክሳውያ የዘር ማጥፋት ሂድት የሚመራው የኖቤል የሰላም ሽልማት ተሸላሚው አብይ አህመድ ለመሆኑ ሊቀርቡ የሚችሉ 12 ማሳያዎች ፦

በኦርቶዶክሳውያን ላይ የሚካሄደውን የዘር ማጥፋት ሂድት የሚመራው የኖቤል የሰላም ሽልማት ተሸላሚው ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ አሊ ለመሆኑ በማስርጃነት ሊቀርቡ የሚችሉ 12 ማሳያዎች ፦
1) የአብይ መንግሥት  ባለፉት 8 ዓመታት በተካሄደው መፈናቀልን የጅምላ ፍጅት፣ የሀብትና መሬት መነጠቅ፣ ከቤትና ንብረት ማፈናቀል ሂድት   መከላከልና ማስቆም ባላመቻላቸው ወይንም አቅድውና ፈቅደው ያልቻሉ የቀበሌ፣ የወረዳ፣ የዞን፣ የክልል እና የፌደራል የመንግሥት መዋቅር የጸጥታ፣ የደኅንነት፣ የመከላከያ፣ የአስተዳደር ባለሥልጣናትን ከሥልጣን አንሰተውና ከስሰው አያውቁም፤ እንዳዉም አስጠቂና አጥቂ ባለሥልጣናት በሥልጣናቸው ሲያጸኑና ለአንዳዶቹ የበለጠ ሹመት ሲሰጡ ታይተዋል፤

2) የአብይ መንግሥት  ባለፉት 8 ዓመታት በተካሄደው መፈናቀልን የጅምላ ፍጅት፣ የሀብትና መሬት መነጠቅ፣ ከቤትና ንብረት ማፈናቀል የደረሰባቸውን ዜጎች አንድም ግዜ ሂደቱን የሚገታ አጀንዳ ለፓርላማ አቅርቦ በማስወስን   አዋጅና የተግባር    እርምጃ አልወሰደም፤

3) የአብይ መንግሥት  በወያኔና ኦነግ ጥምረት ተደንግጎ ዚጎችን በመከፋፈልና በማፋጅት፣ ከልሎችን በማንነት የማደራጅት፣ ታሪክን በሐሰት ትርክት የመገልበጥና ኦርቶዶክስ ክርስቲና እና አሻራውን ዒላማ የማድርግ ሂድት ባእማጠናከር ባለፉት 8 ዓመታት አዳዲስ አጥፊ ትርክቶች በቻ ሳይሆን በተግባር የሐዝብ አሠፋፈር ጥምርታን በማንነት ለመቀይር ከገጠር እስከ ከተማ እርምጃ ውስዷል፤


4) የአብይ መንግሥት  ባለፉት 8 ዓመታት  በገድማት በሚኖሩ መነኮሳት፣ በካህናት፣ በአብነት መምህራን፣ በአብነት ተማሪዎች ላይ የተፈጸሙ ግድያዎችና ፍልሰቶችን እውቅና በመንሳት ፍትሕ ነፍጓል፣ ሂደቱንም አስቀጥሏል፤

5) የአብይ መንግሥት በኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ቀኖናዊ መንፈሳዊ ጉዳዮች በቀጥታ ጣልቃ በመግባት በጀት በመመደብ፣ አመራር በመስጠት፣ ጥበቃ በማደረግ በወሊሶና መቀሌ ቤተ ክርስቲያኒቱን የሚያፈርሱ የጎሣ ፖለቲካ-ትክል የሐሰት መነኮሳትን በማጰጰስ  መንበረ ጵጵስና ለማወርስ በጥይት አያሌ ተቃዋሚ መመናን ርሽኗል፤

6) አብይ አህመድ ሲኖዶሱን በጎሣ ጳጳሳት እንዲሞሉ ኢአማንያን የወሊሶ ሥልጣን ናፋቂዎችን የጠፉ በጎች በሚል በአድርባያ የሲኖድሱ አባላት እሽታ የሐዋርያትን ቀኖና አስቀይሮ በጎሣ ስሌት አጥፊዎችን በማሾም ኦርቶዶክሳውያንን ከኦሮምያ በማጽዳቱ ፕሮጄክት እንዲተባበሩት አድርጓል፤

7) የአብይ መንግሥት  ባለፉት 8 ዓመታት   ከመላው ኦሮምያና ቤኒሻንጉል ጉምዝ፣ ከሚሴ ከርስቲያኖችን በጅምላ በመጭፍጨፍና በመቅበር፣ በማፈናቀል፣ በማደኸየት በመቀጠል የፍትሕ፣ የመልሶ መቋቋም፣ የድኅንነት ዋስትና ማግኝት፣ የመካስ አጀንዳ በሚዲያ፣ በፓርላማ፣ በፌዴሬሽ ምክር ቤት እንዳይነሳ ተከላክሏል፤

8) አብይ አህመድ አሊ በሕወሃትና ኦነግ ተጀምሮ፣ በኢሓዴግ መንግሥት የቀተለውን የዝር ፖለቲካ፣ በኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያንና ክርስቲያኖች ተቋማት፣ አትሪክና ማንነት ላይ የሚነዛውን እና እልቂት ያሰጀመረውን ሂድት አባብሶ በመቀጠል በ8ቱ ዓመት አያሌ ንግግሮችን በራሱም ሆነ በባልሥልጣናቱ በኩል፣ በተገዙ ጳጳጳስት፣ ዑስታዞችና የባህል መሪዎች በኩል ማሰነዛቱን ከመቀጠሉም በላይ በዙ መጽሕፍት፣ ጋዜጦች፣ መጽሔቶች፣ ዘፈኖች፣ መስሎች እንዲመረቱ አድርጓል፤

9) አብይ አህመድ በኢትዮጵያ የመንግሥት እና የፓርቲ ፖለቲካ ድርጀቶች ውስጥ ኦርቶዶክሳውያን ክርስቲያኖች የውሳኔ ተስትፎ እንዳይኖራቸው ከሁሉም ወሳኝ የሥልጣን ቦታዎች ሁሉ አሰወግዶአቸው ነባርነትን በሚጠሉና የማያውቁትን አዲስነት በሚናፍቁ ጸረ ኦርቶዶክስ ክርስትና ቡድኖች ሞልቶታል፤

10) አብይ አህመድ የፌደራል መንግሥት ሥልጣንን ሙሉ በሙሉ በአምባገነንነት በመቆታጠር የደኅንነትና የጸጥታ መዋቅሩን፣ መከላከያውን፣ የኦሮምያን ለዩ ኃይል ሙሉ በሙሉ ለራሱ ተጠሪ በማደርግ ኦርቶዶክሳውያን ላይ ጦርነት በማወጅ፣ ከቱርክ፣ ከአርብ ኢምሬት፣ ከሱዳን አንዳን ኃይሎች እና ከመራባውያን ጋር በመተባበር ኦርቶድኮሳውያን በሚበዙባቸው አካባቢዎች እልቂት እየፈጸመ መገኘቱ፤

11) የአብይ መንግሥት  ባለፉት 8 ዓመታት በተካሄደው መፈናቀልን የጅምላ ፍጅት፣ የሀብትና መሬት መነጠቅ፣ ከቤትና ንብረት ማፈናቀል የደረሰባቸውን ዜጎች የብዙኃን መገናኛ ሽፋን እንዳያገኙ በማድረግ፣ እልቂት በሚፈጸምባቸው ሳምንታትና ወራት ሁሉ አዳዲስ አቅጣጫ የሚያስቀይሩ አጀንዳዎችን፣ ለምሳሌ፦ ችግኝ ተከላ፣ የግደብ በከርመት ውሃ ጎርፍ መሙላ፣ የሶማሌና አሰብ ወደብ፣ የፋኖና የፕሪቶሪያ ስምምነት፣ የኮሪደር ልማትና መናፈሻ፣ የሌሎች አገራት አደጋ የሐዘን መግለጫ ወዘተ በመደረብ  እልቂቱና ሁለ-ገብ ጥቃቱ ትኩረት እንዳያገኝ አድርጓል፤
12) መከላከያው፣ የፍትሕና የጸጥታ፣ የደኅንነትና ሚዲያ፣ የውጭና ይፋይናንስ መዋቀራት ሙሉ በሙሉ በኦርቶዶክስ ጠልና ቡድኖች እንዲያዙ በማድረግ ወንጀሉን በመሰውርና ግፍ በማስቀጠሉ ----
---- ሲጠቃለል በአሁኑ ገዜ የሚፈሰው የክርስቲያኖች ደምና የሚፈጸመው ግፍ በቀጥታ የሚመራው በአብይ አህመድ አሊ መሆኑን ያርጋግጣል።


  

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

የሐሰት ትርክት ኦነጋውያንና የሕወሃታውያ የጋራ ስልት ከነግሥታት ወደ ተራ ግለሰቦች

✏️ እግዚአብሔር ይስጥልኝ።  እርሱ ይመስገን። ምድራችንን #በደም #ያጨቀየው $ህሊና #የነሳን ፣ #ልቦናችንን #ያጨለመን ፣ #ሰብእናችንን ያዋረደው:- 👉 የሕወሐታውያንናንየኦነጋውያን የንዑስ ማንነት የጎሣ ፖለቲካ የደንቆሮ ርእዮትና፣ 👉 መርዛማን ጥላቻን ለ፶ ዘመናት ያከፋፈሉት የሐሰት ትርክት ናቸው። ✏️እንደ ዳግማዊ #ምንልክ ያሉ   ከዋክብት መሪዎች፣ እንደራሴቻቸው፣ ደጃዝማቾችና ቀኝና ግራ አዝማቾቻቸው  ከትውልድ ትውልድ የሚሸጋገር ብዙ ውለታ ውለውልናል:- 👉 በዘመነ ኦቶማንና አውሮፓ፣ በዘመነ መሳፍንት የተበታተነውን እና የተቆነጻጸለውን፣ ጎሠኛ የአርብቶ አደሮች  መሬት ፍለጋ  የደመሰሱትን ክርስቲያናዊ የግዕዝ/የነፃነት ሥልጣኔ አሻራ እንዲያገግም ደክመውልናል፤ 👉 የጥንት አገርን እና ሕዝቦችን   በከፊልም ቢሆን በመሰብሰብ  ጠንካራና ብቸኛ የነጭ ቅኝነትንና ባርነትን በመከላከል፣ ከኦቶማን ቱርክ ወር ትናንት ውስጥ ጥረኛ  አህመድ ግራኝ በመጋደል  ልዩ የነጻነት ማንነት ያላትን አገር ብበቸኝነት በዓለም ካርታንላይ አቆይተዋል፤ 👉 የሬማ ግዛት በጎሣ ተብልቶ ፲ ትንንሽ ሲሆን ከበበባውን ተቋቁማ በዝኃነታችን በተመጋጋቢ አንድነት ከ፹ በላይብቋንቋ፣ ከዓለም ትልልቅ እምነቶች ክትስትናን ፣ ይሁዲን፣ እስልምናን፣ የእረማውያንን ቅሪት የሆኑ የባህል እምነቶችን ሁሉን ይዛ በአውሮፓ በአርብ አምሳል ሳትሠራ ለእኛ አቀብዋል፤ 👉 ወያኔና ኦነግ፣ ገንጣዩ ሻዕብያ፣ ከሃዲው የማርክሲስት የአእምሮ  ባሪያን ስብስብ  እስኪፈትናት ድረስ ራሷን የቻለች አገር እንድንፈጥር ያስተባበሩን ነገስታት የተመሰገኑ ናቸው። አገር ሲያረጅ ጃርት ያብቅላል እንዱሉ: መል...

ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን እና ቋንቋና ማንነት ተኮር እንቅስቃሴዎች

ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን እና ቋንቋና ማንነት ተኮር እንቅስቃሴዎች   ፩. ቋንቋን በተመለከተ ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮና ትውፊት ከሰው ልጅ መበደል በፊት ፍጥረት ሁሉ የሚግባባው በአንድ ቋንቋ ነበር፡፡ “ምድርም ሁሉ በአንድ ቋንቋና በአንድ ንግግር ነበረች” እንዲል፡፡ ዘፍ. 11፡1 በኃጢአት ምክንያት ግን ሰውና መላው ፍጥረት በአንድ ቋንቋ መግባባታቸው ቀረ፡፡ ኃጢአት እየበዛ ሲሄድ የሰው ልጅ ቋንቋም በባቢሎን ተደበላለቀ፣ አንዳቸው ከሌላቸው ጋር የማይግባቡ ብዙ ዓይነት ቋንቋዎችም ተፈጠሩ፡፡  በበደል የመጣውን ሁሉ ሊያስተካክልና ሊያድን በመጣው በአምላካችንና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አዳኝነት ያ የቀደመው ጸጋ ስለ ተመለሰልን በበዐለ ሃምሳ ሰዎች በልዩ ልዩ ቋንቋ አንድ ዐይነት የእግዚአብሔርን መልእክት ሰሙ፡፡ በዚህ ጸጋ የተጠቀሙና የበቁ ቅዱሳን የእንስሳትን ቋንቋ እስከ ማወቅ ደረጃ ይደርሳሉ፡፡   የክርስትና ጉዞ ወደ ቀደመው በአንድ ቋንቋ መግባባት መመለስ ነው፡፡ ወደዚያ ለመድረስ ደግሞ ሰው የእግዚአብሔርን ቃል በሚሰማው ቋንቋ መማር አለበት፡፡ በበዐለ ሃምሳ ጊዜ ለቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስ ብዙ ቋንቋ የገለጠላቸው ሰውን ሁሉ የእግዚአብሔርን የማዳን ጸጋ በሚሰማው ቋንቋ እንዲያስተምሩት ነው፡፡ ሆኖም ቋንቋ መልእክት ማድረሻና መግባቢያ እንጂ ከዚያ ያለፈ ሰዎችን በሆነ መደብ ለመመደብና የልዩነት አጥር ለመሥራት እንደ መሳሪያ ሊሆን አይገባውም፡፡ ይህ ከክርስትና ዐላማ ጋር ተቃራኒ ነው፡፡  ቅዱሳን ሐዋርያት ወደ ዐለም ሁሉ ሲልካቸው ሰዎች የሚቀበሏቸው በሚያስተምሩት ትምህርት መሠረት ነበር እንጂ በትውልድ፣ በብሔርና በመሳሰለው መስፈርት የእኛ ናቸው/አይደሉም በሚል አልነበረም፡፡ የቤተ ክርስቲያን አባቶችን በቋንቋ መ...

ገድሎና አስገድሎ ብፁዕ እየተባሉ መኖር የተፈቀደላቸው ጳጳሳትና ቆሞሳት እንዳይረሱ

ከጥር 27 ጀምሮ በተለያዩ የኦሮምያ ከተሞች በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቀኖና ውጭ የተሾሞና በቅዱስ ሲኖዶስ ተወግዘው የተለዩ አካላትን ወደ ቤተ ክርስቲያን እናስገባለን ባሉ የመንግስት የጽጥታ አካላት በተትኮሰ ጥይትና ሕገ ወጡ ቡድን ባደራጃቸው ወጣቶች ተደብድበው የተገደሉና የቆሰሉ  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ካህናትና ምእመናን።።   1)  ሻሸመኔ ከተማ   I.   የተገደሉ 1.  አያሌው ተረፈ ●   በሻሸመኔ የደብረ አስቦ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ማህደረ ፃድቃን ሰንበት ትምህርት ቤት አባል ●  ጥር 27 ዓ/ም በሻሸመኔ ከተማ በጸጥታ ሃይሉ በሚመራ የጨፍጫፊ ቡድን በደረሰበት ከፍተኛ ደብደባ ወደ ሆስፒታል ገባ ●  በአላቲዮን ሆስፒታል ሕክምና እየተደረገለት ሕይወቱን ማትረፍ አልተቻለም ●  በ ጥር 30 2015 ዓ/ም  ሰማዕትነትን ተቀብሏል       2.  ሊቀ ኅሩያን ቀሲስ ሐረገወይን ●  የሻሸመኔ ደብረ ስብሐት ቅዱስ ሚካኤል አገልጋይ የነበሩት ●  በሻሸመኔ በሕገወጦች በጸጥታ አካላት  በበግፍ በዱላ ተቀጥቅጠው በጭንቅላታቸው በእጅና በእግራቸው ላይ በደረሰባቸው ድብደባ በሀዋሳ ሕክምና እያሉ አርፈዋል። ●  ከመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች በተተኮሰ ጥይት ተመትተው  በያኔት ሆስፒታል ሕክምና ሲደረግላቸው ቢቆዩም ሕይወታቸውን ማትረፍ አልተቻለም። ●  በዛሬው ዕለት ጥር 30 2015 ዓ/ም  ሰማዕትነትን ተቀብለዋል።     3.  ዘማሪ ፍቃዱ ደጉ ●  የቅዱስ ሚካኤል ከሣቴ ብርሃን ሰ/ትቤት አገል...