#የትግራይ #ክርስቲያን ሕዝብ ከሁለቱ #አጥፊዎቹ #ነጻ በማውጣት የተወሰደበትን #አገርን እና #ቤተ ክርስቲያኑን #ያስመልስ‼️
✏️ "የትግራይ #ሲኖዶስ የፌዴሬሽን ምክር ቤትና የምርጫ ቦርድን ውሳኔ በጽኑ ተቃወመ" ይላል አዲስ አድማስ ጋዜጣ ለይ የወጣ ዘገባ።
ራሱን #ቅዱስ ብሎ የሚጠራው #የሕወሃት ሲኖዶስ " የኢትዮጵያ ፌዴሬሽን ምክር ቤት እና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያስተላለፉት ውሳኔ #ለዘመናት #አብሮ #የኖረን #ሕዝብ የሚነጥልና #አንድነትን #የሚያፈርስ ነው" ነው ይላል።
✏️ በዚህ አባባሉ "የሕዝብ #አንድነት" ማለት በወያኔ ሕገ መንግሥት መሠረት የተፈጠሩ አዳዲስ የጎሣ ክልሎችን የሚመለከት ነው።
✏️ #አንድነት ፈጽሞ በጥምቀት አንድ የሆነውን የሥላሴን ልጆች በክርስቶስ ግንድነት ላይ መጣበቅ አይደለም።
✏️ ስለዚህ ይህ ስብስብ #የሕወሃት እንጂ #የክርስቶስና የክርስትና አስተምህሮ፣ እምነትና ተስፋ ላይ የተመሠረተ አይደለም። መንግሥተ ሰማያት ሳይሆን የሕወሃትን ታላቋን ትግራይ የሚማልል ነው። የህወሃትን ታላቋን የዘር ሪፐብሊክ በኢትዮጵያና በኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን መቃብር ላይ ለመመሥረት ተልእኮ የተቀበለ ኢክርስቲያናዊ ካድሬ ነው።
✏️ የሕወሃትን ሲኖዶስ ያስቆጣው የአገር በዘር ሕገመንግሥት መፍረስና የቤተ ክርስቲያን መዳከም፣ የጥምቀት ልጆች ተበታትኖ #ለጽንፈኞች እና ፣#ለአብይ #አህመድ ጭፍጨፋ መጋለጥ፣ እንዲሁም የትግራይ ክርስቲያን ወጣት ከክርስትና እፕእምሮ ታጥቦ የህወሃት የጥፋት ሠራዊት መሆን አይደለም።
✏️ የስብስቡ ጭንቀት የወያኔና የባእዳን ሤራ ውጤት የሆነውን የፕሪቶሪያ ስምምናትና የአብይ አህመድ ቤተደብን የማጋጨት ጥመድ ማስፈጸምና አገር እና የቤተ ክርስቲይንን አንድነት በትኖ የሕወሃትን ሪፐብሊክ ለመፍጠር የሚደረገውን ሂደት መንከባከብ ነው።
✏️ ስለዚህ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ጥር 25 ቀን 2018 ዓ.ም ያስተላለፈውን ውሳኔ መሠረት በማድረግ ምርጫ ቦርድ የካቲት 16 ቀን 2018 ዓ.ም የሰጠው መግለጫ የወያኔ ሕገ መንግሥት በአገር መፍረስ ሊጠቀልላቸው አልሞ የከለላቸው እና የፈጠራቸው የአስተዳደር ድንበሮችን እንደ ዓለም አቀፍ የአገራት ድንበር ጉዳይ አድርጎ በመቆጠር መቆጣቱ ነው።
✏️ በዚህ ዕሳቤ ላይ በመመሥረት "ውሳኔው ሰላምን የሚነሳ በመሆኑ በአስቸኳይ እንዲታረም" ሲልጠይቆ ከህወሃት ቀድሞ እንዳወገዘ ገልጧል ።
✏️ "ሲኖዶስ" ተብዬው እንዲህም ሲል #የግዛት #ጥያቄ አቅርቧል:- "በደቡብ ትግራይ ሀገረ ስብከት ስር ያሉትን #ኮረም፣ #ኦፍላ እና #ራያ #አላማጣ ወረዳዎችን፣ በሰሜን ምዕራብ ትግራይ #የጸለምቲ ወረዳን እንዲሁም #የምዕራብ #ትግራይ ዞን ሀገረ ስብከትን #ርስት በመንጠቅ ወደ አማራ ክልል በማካለል 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ እንዲካሄድ መወሰኑ" የተወገዘ ነው ይላል።
👉 ይህ የጥፋት ስብስብ የክርስቶስ ልጆች በመላው አገሪቱ እንደ እንስሳ በሚታደኑበት፣ በኦሮምያ ክልል መንግሥት በቤተ ክርስቲያንን በሚያጠፋበት፣ የአማራና የትግራይ ሕዝብ አንድ ላይ ቆሞ ከዘር ጥፋት ራሱን እንዳይከላከል #ሕወሃት የተባለ የጥፋት ድርጅት #እንቅፋት በሆነበት በአሁኑ ግዜ ክርስቲያኖችን ከማቀራረብ ይልቅ እርስ በርሱ የማለያየት መግለጫ አውጥቷል።
👉 እንዲህም ሲል ኢክርስቲያናዊ ስብስብ መሆኑን የበለጠ ግልጽ አድርጓል :- ውሳኔው "ሕዝብን ከቀዬው ካፈናቀለ በኋላ ርስቱን የሚነጥቅና በትግራይና በአማራ ሕዝብ መካከል ሆነ ተብሎ መለያየትን የሚዘራ ተግባር ነው ሲል" ለዚህ ሀሉ መለያየትና እልቂት ሕወሃት ዋና የመርዝ ምንጭ መሆኑን ለመሸፈን ሞክሯል።
✏️ የሕወሃቱ ሲኖዶስ የጥምቀት ልጆችን ሳይሆን የሕወሃትን አዲሱን "ትግራዋይነት" የተሰኘ የኦነግ ፖለቲካዊ የ "ኦሮሙማ" "ሃይማኖት" ጋር አቻ ፖለቲካዊ #የዘር #ጣዖት አምልኮ እንደሚወከል የሚያረጋግጠውን ጥሪ እንዲህ ሲል አስተላልፏል:-
✏️ "በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ የትግራይ ተወላጆችም ያላቸውን የፖለቲካ ልዩነት ወደ ጎን በመተው ለሕዝባቸው ህልውና እና ለግዛታዊ አንድነት የሚያደርጉትን ጥረት እናደንቃለን። በቀጣይም ከሕዝባችሁ ጋር በመሆን ለህልውናው በጋራ እንድትመክሩና እንድትሠሩ እንመክራለን" ይላል።
👉 በዚህም አቋሙ ስለ ክርስቲያኖች አንድነት ሳይሆን የበለጠ የተመሠረተለትን የሕወሃትን ክርስቲያኖችን ከፋፍሎ የማዳከም መሠሪ ፕሮጀክት ለማሳለጥ የተፈጠረ እና በአብዛኛው የኢአማንያን ዘረኛ መነኮሳት ስብስብ መሆኑን ገልጧል።
ኦርቴዶክሳውያን የክርስቶስ ልጆች ሆይ‼ መገንዘብ የሚገባን -----
👉 #የትግራይ ኦርቶዶክስ ክርስትና ተከታይ ሕዝብ #ሙሉ #ኢትዮጵያ #ርስታቸው፣ #ሙሉ ቤተ ክርስቲያን #ቤታቸው መሆኑን ዘንግተው ይህን መሠሪ የፖለቲካ ድርጅት ተከታይ በመሆን ለ፶ ድፍን ዘመን ተሰቃይቷል።
👉 በጦርነት አልቋል፣ በስደት ተበትኗል፣ ከሁሉ በላይ ለክርስቶስ የማይስማማውን ዘረኝነትና ጥላቻ በመጋት ነፍሱን ጎድቷል።



አስተያየቶች
አስተያየት ይለጥፉ