ወደ ዋና ይዘት ዘለው ይሂዱ

አገርና ሕዝብ የሚጠፋው ምላስናንሆድ ብቻ የሆኑ ከሰብእና እየጎደሉንሰዎች ቤተ መንግሥትብሲገቡ ነው!

አገር ያጠፋው፣ ትውልድን ያከፋው፣ የደም አባላ እያስከፈለን የሚገኘው  ከሁሉ በላይ ----
ሰው ክቡር ፍጡር ነውው።  ግን ነፃ ፈቃዱን ተጠቅሞ ከዱር አራዊት የከፋና ዱያብሎስን የሚያስቀና እኲይ መሆን ይችላል።

ህሊና፣ ፈሪሃ እግዚአብሔርን፣ ፍትሕ እና ክበረ-ሰብእን ወዲያ ጥለው ወይንም ትፕስውሮባቸው   #ምላስና #ሆድ #ብቻም የሆኑ፤ ---  በአምሳለ እግዚአብሔር መፈጠራቸውን የካዱ  እና በዚህ ምክንያት ለሰውነት ትርጉም ከሚሰጠው ከሕያው   እግዚአብሔር በመለየታቸው #ሰውነትን #የማያሟሉ #የቁም #ሙታን ናቸው።

#ሻዕብያን፣ #ደርግን፣ #ሕወሃትን፣ #ኦነግን፣ #ብልጽግናን  እና የመሳሰሉትን በአምሳላቸው ለጥፋት ፈጥረው #የሚመሩ #ሰዎች በፈቃዳቸው ራሳቸውን #ከሰውነት #ያጎደሉ የቁም #ምውታን  ናቸው። 

ሕዝብን፣ ትውልድን፣ አገርን #ገድለው ሁለተኛ ሞት በንፍስም በሥጋም የሚሞቱ የዓለማችን ዕዳዎች እነዚህ ናቸው።  በሕዝብ ስደት፣ ረሃብ፣ እልቂት ከእምነት መፍለስ፣ መፈናቀል፣ መደኸየት ምንም የማይሰማቸው ብቻ ሳይሆ በግፍ የሚደሰቱ ናቸው። 

እንደ #አብይ  #አህመድ  #አማካሪ አይነቱ #ከ፻፳ ሚሊዮኑ ፲ሩ ሚሊዮን ሰላም ቢያጣ የቀረው ሰላም ነው" ነው በማለት የሰው ልጅን እንደ እቃ በቁጥር የሚለካ #ዳርዉናዊና ናዚያዊ የቁም ሙት  የሚመራት አገር የፈጠርነው ከሰውነት የጎደሉ ሰዎች ሰውን እንዲመሩ  ጤናማዎቹ ብዙኃን በዝምታና በፍዘት በመፍቀዳችን ነው።

የሚገርመው እነዚህን #ከሰብእና #የጎደሉትን #የተበላሹ #ፍጡራን   በውትድርና፣ በፖሊስነት፣ በጄሮ ጠቢነት፣ በአማካሪነት፣ በዲፕሎማሲ፣ በካድሬነት፣ በተለይ በእምነት ቤት ውስጥ ተልእኮ ወስደው የቅድስናን ቦታ እና  ምንጭ ለማራከስ የሚሞክሩ   እየገድሉ ብፁዕ የሚባሉ፣ ጎሣ ጠቅሰው ንጹህ ተብለው የሚጰጵሱ ከንቱዎች በፈቃዳቸው ሰውነታቸውን ላጎደሉ አጥፊዎች  የሚያገለግሉ በየዘመኑ መኖራቸው ነው። 

ለሻዕብያ ተልከው አገር ወግተው ያስገነጠሉ፣ #የትግራይን ሕዝብ ኢትዮጵያን አስጥለው በክልል ያሠሩና ከገዛ ቤተሰቡ የሚያዋጉ፣ #የኦሮሞን ሕዝብ በሐሰት ትርክት የተሸነፈላቸውን ያህል አጎሳቅለው    በበታችነት የስነ ልቦና ስሜት ውስጥ በማስገባት ያገኙትን   ውስን ወጣት ለፍጅት ያሰማሩ፣ #የአማራን ሕዝብ አደንዝዘው የባንዳ መፈልፈያ ያደረጉ፣ ሌሎችንም ወገኖች ወደ ጠራፋማ ባእድነት የገፉና ከጋራብትርክትናብእሤት የበለጠ አፍራሽ ንዑስ ትርክትን የብዙ ----  እነዚህ ከደምሰውነት የጎደሉና የፖለተካ ሥልጣን የጨበጡ፣ በሐሰት እውቀት በተባለ ከንቱ ድንቁርና #ምሁራን የተባሉ ፤ ሳያምኑ የእምነት አባትነትን ለምንዳ ሲሉ የተጣበቁ  ጎዶሎ ሰዎች ናቸው።  

እነዙህ ናቸው ትውልዱን ግራ እያጋቡ አሁን ለሚገኝበት መለያየት፣ አለመተባበር፣ መሳደድና እልቂት የዳረጉት። 
  
እነዚህ ናቸው  #በምርጫ ስም  ትውልዱ ግራ ተጋብቶ #መግደል-እትንፋሱ የሆነ ከሰብ እናብ የጎደለ  መሪዎችን   እንዲመርጥም፣ እንዲያጨበጭብለትና እንዲታዘዘው የሚያደርጉት። 

እንንቃ!!!

ከታች የተያያዘውን  #የታማኝ  #በየነ #የቩዲዮ መልእክት ሳደምጥ  ይህ  ከላይ የገልጽኩትን እንዳጋራ ገፋፋኝ። 

መልእክቴን የተረዳና #ከሙታን የፖለቲካ የአእምሮ ባርነት ነጻ የሆነ፣ #ሰው #ሁሉ #በእግዚአብሔር #አርአያ የተፈጠረ #ክቡር እርሱን ፈጣሪውን በቅድስና፣ በመልካምነት፣ በአፍቃሪነት፣ በለጋስናት፣ በይቅርባይነት፣ በታዳጊነት እና በመሳሰሉት ሁሉ ለመምሰል ለመጋደል  የተጠራ መሆኑን የሚያምን፣ ----
 በተቃራኒው ግን በነፃ ፈቃዱ ክፋትን መርጦ በቁሙ   ልክ ዛሬ እንደሚያሰቃዩን እንደ ጎሣ የማንነት ፖለቱካ ልሂቃን  በቁሙ ሙት እንደሚሆን፣ በምዉታንነቱ ሕያዋንን በሥጋ  እንደሚገድል  #የሚያምን እና የተረዳ ሁሉ  "ትክክል" እያለ ግብረ መልስ ይስጠኝ።

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ገድሎና አስገድሎ ብፁዕ እየተባሉ መኖር የተፈቀደላቸው ጳጳሳትና ቆሞሳት እንዳይረሱ

ከጥር 27 ጀምሮ በተለያዩ የኦሮምያ ከተሞች በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቀኖና ውጭ የተሾሞና በቅዱስ ሲኖዶስ ተወግዘው የተለዩ አካላትን ወደ ቤተ ክርስቲያን እናስገባለን ባሉ የመንግስት የጽጥታ አካላት በተትኮሰ ጥይትና ሕገ ወጡ ቡድን ባደራጃቸው ወጣቶች ተደብድበው የተገደሉና የቆሰሉ  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ካህናትና ምእመናን።።   1)  ሻሸመኔ ከተማ   I.   የተገደሉ 1.  አያሌው ተረፈ ●   በሻሸመኔ የደብረ አስቦ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ማህደረ ፃድቃን ሰንበት ትምህርት ቤት አባል ●  ጥር 27 ዓ/ም በሻሸመኔ ከተማ በጸጥታ ሃይሉ በሚመራ የጨፍጫፊ ቡድን በደረሰበት ከፍተኛ ደብደባ ወደ ሆስፒታል ገባ ●  በአላቲዮን ሆስፒታል ሕክምና እየተደረገለት ሕይወቱን ማትረፍ አልተቻለም ●  በ ጥር 30 2015 ዓ/ም  ሰማዕትነትን ተቀብሏል       2.  ሊቀ ኅሩያን ቀሲስ ሐረገወይን ●  የሻሸመኔ ደብረ ስብሐት ቅዱስ ሚካኤል አገልጋይ የነበሩት ●  በሻሸመኔ በሕገወጦች በጸጥታ አካላት  በበግፍ በዱላ ተቀጥቅጠው በጭንቅላታቸው በእጅና በእግራቸው ላይ በደረሰባቸው ድብደባ በሀዋሳ ሕክምና እያሉ አርፈዋል። ●  ከመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች በተተኮሰ ጥይት ተመትተው  በያኔት ሆስፒታል ሕክምና ሲደረግላቸው ቢቆዩም ሕይወታቸውን ማትረፍ አልተቻለም። ●  በዛሬው ዕለት ጥር 30 2015 ዓ/ም  ሰማዕትነትን ተቀብለዋል።     3.  ዘማሪ ፍቃዱ ደጉ ●  የቅዱስ ሚካኤል ከሣቴ ብርሃን ሰ/ትቤት አገል...

ኢትዮጵያ የተገዳደሯትን ሁሉ ቅኝ ገዥወች የተከላከለችባቸው፣ የተዋጋችባቸውና ነጽነቷን ያስከበረችባቸው እሴቶች; በቀሲስ አስተርአየ ጽጌ

የጽዋዕ ማህበራትና ሰንበቴ ከቅድስት ድንግል ማርያም ጋራ የተሳሰሩት የጽዋ ማሕበራትና ሰንበቴወች ናቸው፡፡  ኢትዮጵያ የተገዳደሯትን ሁሉ ቅኝ ገዥወች የተከላከለችባቸው፣ የተዋጋችባቸውና ነጽነቷን ያስከበረችባቸው እሴቶች  ቀሲስ አስተርአየ ጽጌ  nigatuasteraye@gmail.com  ሚያዚያ ፳፩ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም.  (April 28, 2025)  መግቢያ  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያናችን ኩለንታዊት ቀዳማዊት ደኀራዊት፡ ዘመናዊት ናት ስትባል እም ኀበ አልቦ አይደለም፡፡ በብዙ እሴቶቿ ነው፡፡ ኩለንታዊት ከምታደርጋት ከብዙ እሴቶቿ መካከል የጽሑፌ መነሻ የሆኑት ከቅድስት ድንግል  ማርያም ጋራ የተሳሰሩት የጽዋ ማሕበራትና ሰንበቴወች ናቸው፡፡ ስንበቴ በቀጥታ ከእግዚአብሔር የታዘዘች ናት፡፡ የጽዋ ማኅበርም እንደ ሰንበቴው ቀጥታ ከግዚአብሔር ባይሆንም፡ በዮቶር በኩል ለሙሴ የደረሰው የግዚአብሔር ምሪት ናት፡፡ የጽዋ ማሕበርና ሰንበቴ የትርጉማቸው መነሻ፡ መድረሻና የመጨረሻ ዋና ዓላማቸው ሰባዊ ክብርና ነጻነት ነው፡፡   ኢትዮጵያ የተፈታተኗትን ሁሉ ቅኝ ገዥወች ከተከላከለችባቸው ከተዋጋችባቸውና ነጽነቷን ካስከበረችባቸው ዋናወቹ እሴቶቿ ውስጥ የጽዋ ማሕበራትና ሰንበቴወች ናቸው፡፡ በቅኝ ገዥወች ሲቀጠቀጡ ከኖሩት ካጎራባች አገሮች ልዩና የነጻነት ምሳሌ ያደርጓትም የጽዋ ማህበርና ሰንበቴ ናቸው፡፡ የጽዋ ማኅበራትና የሰንበቴ ድርጅቶች እንዴት ተመሰረቱ? ለኢትዮጵያ ምን ጠቀሙ? ትሩፋታቸው ምንድነው? የደርግንና የወያኔን ዘመናት እንዴት ተሻገሩ? በብልጽግና ዘመንስ እንዴት ናቸው? እንዴት ይቀጥሉ ? የሚሉትን ጥያቄወች ለመመለስ ከጽዋ ማኅበር እንጀምር፡፡   የጽዋ ማኅበር መነሻ...

የሐሰት ትርክት ኦነጋውያንና የሕወሃታውያ የጋራ ስልት ከነግሥታት ወደ ተራ ግለሰቦች

✏️ እግዚአብሔር ይስጥልኝ።  እርሱ ይመስገን። ምድራችንን #በደም #ያጨቀየው $ህሊና #የነሳን ፣ #ልቦናችንን #ያጨለመን ፣ #ሰብእናችንን ያዋረደው:- 👉 የሕወሐታውያንናንየኦነጋውያን የንዑስ ማንነት የጎሣ ፖለቲካ የደንቆሮ ርእዮትና፣ 👉 መርዛማን ጥላቻን ለ፶ ዘመናት ያከፋፈሉት የሐሰት ትርክት ናቸው። ✏️እንደ ዳግማዊ #ምንልክ ያሉ   ከዋክብት መሪዎች፣ እንደራሴቻቸው፣ ደጃዝማቾችና ቀኝና ግራ አዝማቾቻቸው  ከትውልድ ትውልድ የሚሸጋገር ብዙ ውለታ ውለውልናል:- 👉 በዘመነ ኦቶማንና አውሮፓ፣ በዘመነ መሳፍንት የተበታተነውን እና የተቆነጻጸለውን፣ ጎሠኛ የአርብቶ አደሮች  መሬት ፍለጋ  የደመሰሱትን ክርስቲያናዊ የግዕዝ/የነፃነት ሥልጣኔ አሻራ እንዲያገግም ደክመውልናል፤ 👉 የጥንት አገርን እና ሕዝቦችን   በከፊልም ቢሆን በመሰብሰብ  ጠንካራና ብቸኛ የነጭ ቅኝነትንና ባርነትን በመከላከል፣ ከኦቶማን ቱርክ ወር ትናንት ውስጥ ጥረኛ  አህመድ ግራኝ በመጋደል  ልዩ የነጻነት ማንነት ያላትን አገር ብበቸኝነት በዓለም ካርታንላይ አቆይተዋል፤ 👉 የሬማ ግዛት በጎሣ ተብልቶ ፲ ትንንሽ ሲሆን ከበበባውን ተቋቁማ በዝኃነታችን በተመጋጋቢ አንድነት ከ፹ በላይብቋንቋ፣ ከዓለም ትልልቅ እምነቶች ክትስትናን ፣ ይሁዲን፣ እስልምናን፣ የእረማውያንን ቅሪት የሆኑ የባህል እምነቶችን ሁሉን ይዛ በአውሮፓ በአርብ አምሳል ሳትሠራ ለእኛ አቀብዋል፤ 👉 ወያኔና ኦነግ፣ ገንጣዩ ሻዕብያ፣ ከሃዲው የማርክሲስት የአእምሮ  ባሪያን ስብስብ  እስኪፈትናት ድረስ ራሷን የቻለች አገር እንድንፈጥር ያስተባበሩን ነገስታት የተመሰገኑ ናቸው። አገር ሲያረጅ ጃርት ያብቅላል እንዱሉ: መል...