ወደ ዋና ይዘት ዘለው ይሂዱ

ናርሲሲስት መሪዎችን የሚከተል ታጋይ ደሙ ደመከልብ መስዋዕትነቱ ከንቱ ይሆናል! ለራስህ ዋጋ ስጥ!

#የናርሲሲስት የስብእና ቀውስ ያለባቸው ሰዎች የግድ-መሪዎች ለመሆንንበሚዋደቁበት አውድ ሁሉ የብዙኃን #የመስዋእትነት ዋጋ ይረክሳል፣ #ከዓላማ ውጭ ይባክናል፣ #የቁማርተኞች የግል መጠቀሚያንይሆናል። እና እንንቃ!!!

የተማሪዎች ንቅናቄና መስዋእትነት በደርግ እና የውጭ ጠላት አጀንዳ ተሸካሚዎች በእነ ሻዕብያ፣ በሕወሃት በኦነግ ዋጋ አጣ፣ ኢሕአዴግን ለመጣል የተከፈለው መስዋእትነት በኦነጋዊ ኦሮሙማ የብልጽግና መንግሥት ረከሰ፣ ---

አሁንም #የአማራ ህዝብ የህልውና ትግል የሚከፈልለትን ከፍተኛ ሁለገብ መስዋእትነት በውስጡ በበቀሉ ባንምዳዎች፣ ጎጠኞች፣ ናርሲሲስትና ተላላኪ እጅግ ጥቂት የፋኖ #መሪዎች እንዳይረክስ መጠበቅ የወቅቱ አንገብጋቢ ትኩረት መሆን ወለበት።

ስለ ናርሲሲስቶች ወደገኛ ጠባይ ለዝርዝር ትንተና እንዚህንንቪዲዮዎች ይመልከቱ https://youtube.com/playlist?list=PLauOEW1Em0lKWjJqKDTjVZzJ0yeA3FqpN&si=rUDEQF07CcxRi7Um

ታሪክብእንደሚያስተምረን በማንኛውም የወል ተሳትፎ በሚጠይቅ ትልቅ የህዝብ ትግል ውስጥ አንድነት አደጋ ላይ የሚወድቅባቸው ውስጣዊና ውጭአዊ ምክንያቶች አሉ።

ከሁሉ በላይ ግን የአንድነት ጠላት ናርሲሲስት የስነ ልቦና ("ማን አኽሎኝ፣ እኔ ብቻ፣ ልዩ ፍጡር ነኝ፣ ሁሉ ክብር ይገባኛል፣ አተኬ ነኝ " የሚያሰኝ ስነ ልቦንና) ቀውስ ያለባቸው ሰዎች ያለንሀፍረት ተነስተው ---- " #ሥልጣን#መምራት፣ ከሁሉ በላይ የግድ የሚገባው 'ለእኔ' ብቻ እና ብቻ ነው" በሚል ግብዝነት ሲነሱ፤ ይህንንም ለማስፈጸም የሚችሉትን ማንኛውንም ሤራ ሁሉ ስለሚጎነጉኑና ሌሎች የተሻሉ ጸጋዎች ያሏቸውን ጓዶቻቸውን በማወክ፣ በማጥፋትና በማሰናከል ሲጠመዱ የሚከሰትብየውስጥብቀውስ ይሆናል። እንዚህ ሰዎች በሤራ ስለሚጠመዱ መተማመንንን፣ ብዝኃ ጸጋዎዥን፣ ትብብርን፣ ምሥጢር መጠበቅን፣ በአንድ ድምጽ መናገርን፣ ሕዝብ ማስተባበርን ሁሉ ያመክኑታል።

በራሳቸው ፍተወት ታውረው ለራሳቸው ቅድሚያ በመስጠት ወዋጭ የትግሉን ስትራተጂዎች ሁሉ ያከሽፉታል፤ ዙህ አዙሪት ትግሉን በማዘግየትና ሕዝብን በማድቀቀ ከጠላትብየከፋ አደጋ ያስከትላሉ።

ክፉና ጨካኝ ጠላት ከፊት ቆሞ እያዩ ራሳቸውም ለትግሉ ዓላማ የውስጥ ጠላት በመሆን እንቅፋት ስለሚሆኑ ታጋዮች መስዋእትነታቸው እንዳይባክን ሤረኛን መለማመጥና በማባበል ጊዜ ሳያጠፉ #በአማራጭ #መንገድ ወደ ግቡ መሮጥ ላይ ማተኮር አማራጭ የለዉም።

የዚህ አይነት ሁኔታ ሲያጋጥም በሽተኛ #አዋኪዎችን #እንዳልተፈጠሩና እንደሌሉ በመቁጠር የትግል ዋና ተልእኮና ግብ ላይ በማተኮር በሌላ መንገድ ራስን አደራጅቶና ከናርሲሲስቶችና ሤረኞች ነጻ የሆነ መንገድ ፈልጎ መቀጠል ነው።

ያን ጊዜ ፀሐይ ያለ እነርሱ ወጥታ እንደምትገባ ሲገነዘቡ ራሳቸውን ከጓዶቻቸው እንደ አንዱ እንጂ የአምላክነት ሚና እንደሌላቸው እና የዘረጉት የሤራ ወጥመድና ፕሮፓጋንዳ ራሳቸውን እንደሚጥላቸው ይገነዘባሉ። ወይ ያርፋሉ ወይንም ከሰው እኩል መሆናቸውን ተቀብለው የድርሻቸውን ይወጣሉ።

ወደ ፊት ብቻ!

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ገድሎና አስገድሎ ብፁዕ እየተባሉ መኖር የተፈቀደላቸው ጳጳሳትና ቆሞሳት እንዳይረሱ

ከጥር 27 ጀምሮ በተለያዩ የኦሮምያ ከተሞች በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቀኖና ውጭ የተሾሞና በቅዱስ ሲኖዶስ ተወግዘው የተለዩ አካላትን ወደ ቤተ ክርስቲያን እናስገባለን ባሉ የመንግስት የጽጥታ አካላት በተትኮሰ ጥይትና ሕገ ወጡ ቡድን ባደራጃቸው ወጣቶች ተደብድበው የተገደሉና የቆሰሉ  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ካህናትና ምእመናን።።   1)  ሻሸመኔ ከተማ   I.   የተገደሉ 1.  አያሌው ተረፈ ●   በሻሸመኔ የደብረ አስቦ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ማህደረ ፃድቃን ሰንበት ትምህርት ቤት አባል ●  ጥር 27 ዓ/ም በሻሸመኔ ከተማ በጸጥታ ሃይሉ በሚመራ የጨፍጫፊ ቡድን በደረሰበት ከፍተኛ ደብደባ ወደ ሆስፒታል ገባ ●  በአላቲዮን ሆስፒታል ሕክምና እየተደረገለት ሕይወቱን ማትረፍ አልተቻለም ●  በ ጥር 30 2015 ዓ/ም  ሰማዕትነትን ተቀብሏል       2.  ሊቀ ኅሩያን ቀሲስ ሐረገወይን ●  የሻሸመኔ ደብረ ስብሐት ቅዱስ ሚካኤል አገልጋይ የነበሩት ●  በሻሸመኔ በሕገወጦች በጸጥታ አካላት  በበግፍ በዱላ ተቀጥቅጠው በጭንቅላታቸው በእጅና በእግራቸው ላይ በደረሰባቸው ድብደባ በሀዋሳ ሕክምና እያሉ አርፈዋል። ●  ከመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች በተተኮሰ ጥይት ተመትተው  በያኔት ሆስፒታል ሕክምና ሲደረግላቸው ቢቆዩም ሕይወታቸውን ማትረፍ አልተቻለም። ●  በዛሬው ዕለት ጥር 30 2015 ዓ/ም  ሰማዕትነትን ተቀብለዋል።     3.  ዘማሪ ፍቃዱ ደጉ ●  የቅዱስ ሚካኤል ከሣቴ ብርሃን ሰ/ትቤት አገል...

ኢትዮጵያ የተገዳደሯትን ሁሉ ቅኝ ገዥወች የተከላከለችባቸው፣ የተዋጋችባቸውና ነጽነቷን ያስከበረችባቸው እሴቶች; በቀሲስ አስተርአየ ጽጌ

የጽዋዕ ማህበራትና ሰንበቴ ከቅድስት ድንግል ማርያም ጋራ የተሳሰሩት የጽዋ ማሕበራትና ሰንበቴወች ናቸው፡፡  ኢትዮጵያ የተገዳደሯትን ሁሉ ቅኝ ገዥወች የተከላከለችባቸው፣ የተዋጋችባቸውና ነጽነቷን ያስከበረችባቸው እሴቶች  ቀሲስ አስተርአየ ጽጌ  nigatuasteraye@gmail.com  ሚያዚያ ፳፩ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም.  (April 28, 2025)  መግቢያ  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያናችን ኩለንታዊት ቀዳማዊት ደኀራዊት፡ ዘመናዊት ናት ስትባል እም ኀበ አልቦ አይደለም፡፡ በብዙ እሴቶቿ ነው፡፡ ኩለንታዊት ከምታደርጋት ከብዙ እሴቶቿ መካከል የጽሑፌ መነሻ የሆኑት ከቅድስት ድንግል  ማርያም ጋራ የተሳሰሩት የጽዋ ማሕበራትና ሰንበቴወች ናቸው፡፡ ስንበቴ በቀጥታ ከእግዚአብሔር የታዘዘች ናት፡፡ የጽዋ ማኅበርም እንደ ሰንበቴው ቀጥታ ከግዚአብሔር ባይሆንም፡ በዮቶር በኩል ለሙሴ የደረሰው የግዚአብሔር ምሪት ናት፡፡ የጽዋ ማሕበርና ሰንበቴ የትርጉማቸው መነሻ፡ መድረሻና የመጨረሻ ዋና ዓላማቸው ሰባዊ ክብርና ነጻነት ነው፡፡   ኢትዮጵያ የተፈታተኗትን ሁሉ ቅኝ ገዥወች ከተከላከለችባቸው ከተዋጋችባቸውና ነጽነቷን ካስከበረችባቸው ዋናወቹ እሴቶቿ ውስጥ የጽዋ ማሕበራትና ሰንበቴወች ናቸው፡፡ በቅኝ ገዥወች ሲቀጠቀጡ ከኖሩት ካጎራባች አገሮች ልዩና የነጻነት ምሳሌ ያደርጓትም የጽዋ ማህበርና ሰንበቴ ናቸው፡፡ የጽዋ ማኅበራትና የሰንበቴ ድርጅቶች እንዴት ተመሰረቱ? ለኢትዮጵያ ምን ጠቀሙ? ትሩፋታቸው ምንድነው? የደርግንና የወያኔን ዘመናት እንዴት ተሻገሩ? በብልጽግና ዘመንስ እንዴት ናቸው? እንዴት ይቀጥሉ ? የሚሉትን ጥያቄወች ለመመለስ ከጽዋ ማኅበር እንጀምር፡፡   የጽዋ ማኅበር መነሻ...

ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን እና ቋንቋና ማንነት ተኮር እንቅስቃሴዎች

  ኦ ርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን እና ቋንቋና ማንነት ተኮር እንቅስቃሴዎች   ፩ . ቋንቋን በተመለከተ ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮና ትውፊት ከሰው ልጅ መበደል በፊት ፍጥረት ሁሉ የሚግባባው በአንድ ቋንቋ ነበር፡፡ “ ምድርም ሁሉ በአንድ ቋንቋና በአንድ ንግግር ነበረች” እንዲል፡፡ ዘፍ. 11፡1 በኃጢአት ምክንያት ግን ሰውና መላው ፍጥረት በአንድ ቋንቋ መግባባታቸው ቀረ፡፡ ኃጢአት እየበዛ ሲሄድ የሰው ልጅ ቋንቋም በባቢሎን ተደበላለቀ፣ አንዳቸው ከሌላቸው ጋር የማይግባቡ ብዙ ዓይነት ቋንቋዎችም ተፈጠሩ፡፡ በበደል የመጣውን ሁሉ ሊያስተካክልና ሊያድን በመጣው በአምላካችንና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አዳኝነት ያ የቀደመው ጸጋ ስለ ተመለሰልን በበዐለ ሃምሳ ሰዎች በልዩ ልዩ ቋንቋ አንድ ዐይነት የእግዚአብሔርን መልእክት ሰሙ፡፡ በዚህ ጸጋ የተጠቀሙና የበቁ ቅዱሳን የእንስሳትን ቋንቋ እስከ ማወቅ ደረጃ ይደርሳሉ፡፡   የክርስትና ጉዞ ወደ ቀደመው በአንድ ቋንቋ መግባባት መመለስ ነው፡፡ ወደዚያ ለመድረስ ደግሞ ሰው የእግዚአብሔርን ቃል በሚሰማው ቋንቋ መማር አለበት፡፡ በበዐለ ሃምሳ ጊዜ ለቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስ ብዙ ቋንቋ የገለጠላቸው ሰውን ሁሉ የእግዚአብሔርን የማዳን ጸጋ በሚሰማው ቋንቋ እንዲያስተምሩት ነው፡፡ ሆኖም ቋንቋ መልእክት ማድረሻና መግባቢያ እንጂ ከዚያ ያለፈ ሰዎችን በሆነ መደብ ለመመደብና የልዩነት አጥር ለመሥራት እንደ መሳሪያ ሊሆን አይገባውም፡፡ ይህ ከክርስትና ዐላማ ጋር ተቃራኒ ነው፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያት ወደ ዐለም ሁሉ ሲልካቸው ሰዎች የሚቀበሏቸው በሚያስተምሩት ትምህርት መሠረት ነበር እንጂ በትውልድ፣ በብሔርና በመሳሰለው መስፈርት የእኛ ናቸው/አይደሉም በሚል አልነበረም፡፡ የቤተ ክርስቲያ...