የወደ ፊቷ ኢትይጵያ መሪዎች ማሟላት የሚገባቸው መስፈርቶች
ሕዳር ፲፫ ቀን ፳፻፲፮ ዓ/ም
መግቢያ
የውደ ፊቷ ኢትይጵያ የግድ የፍትሐዊት፥ ሰብአዊትና ታሪካዊት ሉዓላዊት የፖለቲካ ርእዮት፣ አስተዳደርና አመራር ያሟላቸ መሆን ይኖርባታል። የኢትዮጵያ ሕዝብ ከዚህ ያነስ ሌላ አይነት ሀገር እንዲኖረው መፍቀድ አይኖርበትም። በባእዳን ፖልቲካው ፍልስፍና ላይ የተመሠረቱ የጎሣ ማንነት ፖልቲካ፣ የቂምና የጥላቻ ትርክት፣ የምለያየትና ሕዝብን በአካባቢ ባሪያ አድርጎ የመንገሥ ጥባብ የሊሂቃን ፍላጎት በሚያስከትለው ግጭት፣ ስደት፣ ሞት፣ ድኽነት የደከመ ሕዝብ የተርጋጋና ሰላማዊ፣ ትስፋ ስጭና ለተውልድ የሚተርፍ ሁለገብ እድገት ጎዳና ውስጥ የሚያራምደው ጎዳና ምርጫው እንደሆን በሚያደረግው ተጋድሎ አሳይቷል።
አገራችን ምንን አንኳ ከዓለም ሁሉ ተለይታ ያልተቆራረጠና ፈሪሃ እግዚአብሔር፥ ከሰብአዊ ክብር፥ ከፍትሐዊነትና ከአገር ልጆች እኩልነት የተለየ በተቃራኒው በጣዖት፥ በሰብአዊ ፍልስፍና እና ሐሰት ላይ የተመሠረተ የሰው ልጆችን የሚያበላልጥ፥ እልቂትና ወረራዎችን የሚፈጽም የፖለቲካ አስተዳደር አንደ ፋርስ ባቢሎን፥ እንደ ግሪክ፥ እንደሮምና የሩቅ ምሥራቅ፥ ወይንም በ18ኛ መቶ ክፍለዘመን አንደተወለደው ሰውን ዝንጀሮ አድርጎ ዓለምን የወረረው የአውሮፓ አስታሰብ ግራ ሳትጋባ ከኖኅ መርከብ ወርደው የሸው ልጆች ርስትን ከተከፋፈሉበት ዘመን አንስቶ ለ6000 ተውፊታዊ እና ለ3000 የተጻፈ ታሪክ መኖር የቻለች ብቸኛ አገር ናት። የባቡሎን፥ የግሪክና የሮም ሥልጣኔዎች ረዥሙ መቆየት የቻለው 600 ዓመታት ብቻ ነበር።
ይሁን እንጂ አገራችን በዓለም ውስጥ አንደ መገኘቷ ከውጭ በመጣባት ተጽእኖ የተለያዩ ባህሎችን፥ እምነቶችን፥ ሥርዓተ ፖለቲካንና በቀጥታ በኃይል በሚደረጉ ወረራዎች፥ ከ1940ዎቹ ወዲህ በትምህርት ስም በሚመጣ የአእምሮ አጠባ ናበር ማንነቷን በማሥበራዊ፥ በፖለቲካዊ፥ በስነ መንግሥትና በፍልስፍና ደረጃ እያጣች መጥታ በመጨረሻም በአምላክ የለሽ የማርክሲስት አስተምህሮ በውጭ-ገብ የባእዳን ትምህርት በሠለጠኑ ልጆቿ ማምነቷን ሙሉ በሙሉ ተነጥቃለች።
የኢትያጵያ ረዥም ታሪካዊ ሂደቷን ያገናዘበ፥ በፈሪሃ እግዚአብሔርና በትወፊት ላይ የተመሠረተ ሥርዓተ መንግሥት እና ሥርዓተ ማኅበር፥ የሰው ልጆች ፍጹም እኩልነትና የአገር ሙሉ ባለቤትነት ወደ ሊመለስ የሚችለው አገሪቷን ለመምራት ወደ ሥልጣን እና የፖለቲካዊ አስተዳደር ኃላፊነት የሚወስዱ ዜጎች ስነ ልቦናዊ ውቅር፥ ነፅሮተ ዓለም፥ እምነትና ባህል ተጠቃሎ በውጭ-ገብነት የአገር ሥርዓተ ትምህርት ይዘት አካል በመሆን ልሂቅ ወይንም ምሁር በሚያሰኝ ደረጃ ከሚያስገኘው በላይና ዳኛ እንደሆነ የሚያምን፥ እንደተለመደው “ሳይማር ያስተማረን ሕዝባችን” እያለ ራሱን በመኮፈስ ነባር እና አገር-ፈለቅ አውቀቶችን፥ ማሥበራዊና መንፈሳዊ መዋቅራትን፥ የሕዝብ አሠፋፈርና አኗኗርን፥ የአስተዳደርና የፍትሕ ሥርዓትን ሁሉ አንድ ሕንፃ ውስጥና በየዩኒቨርሲቲው ተሰብስቦ በመቀየር ወይንም በመዋስ በሕዝቡ ላይ ለማጫን የማይሞክር መሆን ይኖርበታል።
ወደ ፖለቲካ ሥልጣን የሚመጣ ማንኛውም ዜጋ የአካባቢንና የአገርን አጠቃላይ ነባር ባህሎች፥ እምነቶች፥ ማኅበራዊና መንፈሰዊ መዋቅራት፥ የአስተዳደርና የፍትሕ ሥርዓቶች አክብሮ ለማጎልበት፥ ከውጭ የተማረውን እንደተጨማሪ እንጂ አሁን ለጥፋት እንዳበቁን ፖለቲከኞች ሕዝብን በአፈና ይዞና የራሱን ብቻ የሚጭን ነቅሎ-ተከል መሆንን የሚያወግዝ መሆን ይኖርበታል። ወደ ፖለቲካው ሥልጣን የሚመጡ ዜጎቻችን ፀረ አምልኮተ-እግዚአብሔር፥ ፀረ-ታሪክ፥ ፀረ-ነባርነትና ፀረ-ኢትዮጵያ አቋም ሲያራምዱ ከኖሩ ወይንም ከሚገኙ ስብስቦችና የፖለቲካ ተቋማት ጋር ምንም አይነት ተሳትፎና ወዳጅነት የሌለው፥ የእነዚህንም አካላት ማንነትና ምንነት ጠንቅቆ የሚያውቅ መሆን ይገበዋል።
በአጠቃላይ አሁን የምንገኝበት በቅድሚያ አማራን በዋናነት ህልውናውን ማረጋገጥ፥ ቀጥሎ የብዙኃን ባህል፥ ቋንቋ፥ እመነት፥ ማኅበራዊ አደረጃጀት፥ የአካበቢ ንዑስ ታሪክና ማንነት ያላቸው የአንድ ቤተሰብ የኢትዮጵያ ልጆች መኖሩያ የሆነችዋን ታሪካዊት አገር ከጠባብ፥ ሤረኛና ዘረኛ የጎሣ ሥርዓት በማዳን ሉዓላዊነቷ የተከበረ፥ ታላቅና አንዲት፥ ለሁሉም እኩል እናት የሆነች አገርን ከአደጋ ለማዳን የሚከተሉትን መሥፈርቶች ከግምት ውስጥ በማስገባት የፖለቲካ መሪዎችን በመለየት መቀበል ወይንም ከተሳትፎ ማገድ አስፈላጊ ነው። ይህም መሥፈርት በመላው የኢትዮጵያ ሕዝብና ወጣት ዘንድ የታወቀ፥ የተረዳና እንደ ማጣሪያ የሚገለገሉበት መሣሪያ እንዲሆን በሰፊው ማስተዋወቅ አግባብነት ይኖረዋል።
አስተያየቶች