ወደ ዋና ይዘት ዘለው ይሂዱ

የገዳዩንስ አውቀን እድረናል። እረኛ ተሰኝቶ የአስገዳይ ሆኖ መገኘት ይባስ!! ብለን ከምንተኛ መፍትሄ እንጠቋቆም።

የገዳዩንስ አውቀን እድረናል። እረኛ ተሰኝቶ የአስገዳይ ሆኖ መገኘት ይባስ!! ብለን ከምንተኛ መፍትሄ እንጠቋቆም። ============== ይህ እኮ እልቂት አይገርምም። እነርሱ የተስማሙበት ዘር የማጥፋት ፕሮጀክት ነው!!! እኛ ነን እንጂ "ሶፍት አቀብሏቸው" በሚሉን ነፍሰ ገዳይ መሪዎች ፰ ዓመት ሙሉ እያለቀስን "ድረስልን" የምንለው። ============ እስቲ የውጭውን አቆይተን የውስጡን እረኛ ተብዬ እንጠይቅ!!! ዘወትር ከሞት የተረፍነውንና ወረፋ የምንጠብቀውን የጥምቀት ልጆች በከተማና በውጭ አገር ሰብስበው :+ ! ምእመናንን! ወላችሁ፣ ድምጻችሁ አይሰማም፣ አመስግኑ!! እሪሪሪሪሪ!!! ! እልል በሉ ! አጨብጭቡ ! እንኳን ደስ ያላችሁ ! አባታችንን የሰጠን እርሱን አንዴ ሞቅ አድርጋችሁ አመስግኑ ! እጃችሁን ወደ ኪሳችሁ አግቡና ጣል ጣል ! በረከት ከቤት ይቆያችኋል ስጡ ! ዘምሩ ! ሞቅ ሞቅ ! ! ጳጳሱ መጡ! ጌታ እንዳስተማረን ዘምሩ --- “ወኵሉ ዘዚኣየ ዚኣከ ውእቱ ወዘዚኣከኒ ዚኣየ ውእቱ ወተሰባሕኩ ቦሙ። ወኢይሄሉ እንከ ውስተ ዓለም ወእሙንቱሰ ውስተ ዓለም ይሄልዉ ወአንሰ ኀቤከ እመጽእ። #ኦ #አባ #ቅዱስ #ዕቀቦሙ በስምከ ለእለ ወሀብከኒ ከመ #ይኩኑ #አሐደ #ብነ #ከማነ።" (እኔና አንተ አንድ እንደሆን አንድ ይሁኑ) (ዮሐ:፲፯:፲-፲፩ --- ያለውን የሰበኩንና የዘመርንለት ጳጳስ ዞር ብሎ ምነውሳ #በዘር እና #በጎጥ እየተካፈለን መበተኑን ለ፴ ዓመት አለማምዶን ይባስ ብሎ በዘመነ ብልጽግና ላይ #አስክሬናችን #እንዳይቆጠር አለ? ይህ ነገር ገብቷችኋል? ================= ነፍሳት በክህደት ነፍሳቸው ስትነጠቅ፣ የጥምቀት ልጅ ያለ እረፍት ከበደኖ እስከ ማይካድራና አክሱም በጎሣና ጽንፈኛ የጂሃድ አውሬ፣ በሕወሃት ሤራ፣ በኦነጋዊው ብልጽግና ትብብር በሥጋ ሞት ሲያልቅ ---- የበለጠ ቀጣይ የእልቂት ድግስ እንደአለ በብልጽግና ባለሥልጣናት ቅስቀሳ ሲካሄድና "የያዛችሁትን #ዱላ ወደ #በክላሽ ቀይረን ለጭፍጨፋ እናሠማራችኋለን" እያሉ በአደባባይ ሲሰበክ፤ አብይ በፓርላማው በወደብ ስም ክርስቲያኖችን ለማስጨረስ ሲያውጅ ---- ስለምን ---- በአንድም ተቋም ውስጥ የሰው መከራን ለማስቆም አጀንዳ የጠፋው? ለምን "ባልታወቁ ታጣቂዎች" ብለው የሚዘግቡ የቤተ ክህነት ጋዜጠኞችና ትዕዛዝ ሰጭ አባቶች በረከቱ? ======= ከሁሉ በላይ --- ለፈጣሪ ተገዝተን ፍትህን እንጠብቃለን ያሉ የሃይማኖት መሪዎችም እልቂቱን ለመከላከል ሳይሆን ፍጅት የሚፈጽመውን ሥርዓት ገጽታ ለመጠበቅ ሠራተኛ ሲሆኑ ፣ "ክፉውን ለማድረግ ብዙ ሰዎችን አትከተል፤ ፍርድንም ለማጥመም ከብዙ ሰዎች ጋር ተስማምተህ አትመስክር።" (ዘጸ ፳፫:፪) በተግባር ሲሽሩት ለምን ሁላችንም ፈዘዝን? #የአርሲ፣ #የወለጋ የመላው #አማራ ክልል እልቂት እንዳይነገር አቡነ ያራድ፣ አቡነ ርሩፋኤል፣ አቡነ አብርሃም፣ አቡነ እንትና ወዘተ ለምን ይከላከላሉ? በጭንቅ ከውጭ በሕገ ወጥ መንገድ ጋዜጠኛ እስገብተው የትግራይን ሕዝብ እልቂት ለዓለም የነገሩት #ፓትሪያሪክ #ማትያስ ለምን አሜሪካ ድረስ ተጉዘው የተወገዘውን መንበረ ህወሃትን/"ሰላማን" ሲባርኩ ጋዜጠኛ ጠርተው #እልቂቱን ለዓለም ለማጋለጥ #ለገሙ? መልሱ:- መስቀል የጨበጡ ካባ የደረቡ ይህን #የዘር #ማጥፋት ፖሊሲ ትግበራ ተጨባጭ እውነታ በዓይናቸው እያዩ #እንዳይነገር እንዲከላከሉ #በአብይ አህመድ ትዕዛዝ ተቀብለው እየትገበሩ ስለሄነ። ከክርስቶስ ድሎት ስለበለጠናቸው። የደብረንኤልያስን እልቂት ያድበደበሰት አቡነ አብርሃም ምእመናንን ለማታለለል ተቀንጥሶ የማያልቀውን አንገታቸውን "ስለ ሃይማኖት አንገታን እሰጣለሁ" የምትል መዝሙራቸው "ሃይማኖት" ለእርሳቸው የሚያልቀው የጥምቀት ልጅ ሳይሆን "ፍሎታቸውን ላማስጠበቅ ከአብይና ከዳንኤልብክብረት ጋር መስማማት ነው" አሁን ሁሉም መመራት የጀምሩት በቀኔና ሐርያት ሳይሆን በሌላ በመሆኑ ከሐዋርያት አንድነት ራሳቸው #እንደለዩ ማረጋገጥ ይቻላል። ከሐርያት መንገድ #አልተለየንም የሚሉ ከሆነ በተግባር:- ፩) ቀኖናውን መልሰው፣ ፪) በብርና በጎሣ የተሰበሰበውን ጳጳሳት ሽረው፣ ፫) ያደለቡትን ሀብት ለቤተ ክርስቲያን አስረክበው ፬) በንፍስና በሥጋ ያስጠፉትን የጥምቀት ልጅ ቄጥረውና ተናዝዘው ፭) ከጎሰኝነትና ጎጠኝነት ተፋትተው ፮) የሰበሰቡትን ዘመድ አስማድ አሰናብተው እና አንዳንዶች የወለዱትን ልጅና ቅምጥ ተናዝዘውና ተለይተው ---- የተጠሩበትን የምንኩስና ሕይወት፣ ቃል የገቡበትን የእረኝነት ሥራቸውን ጀምረው ያሳዩ። ይህን #እምቢኝ ብሎ ---- እንደተለመደው በምንደኛ ሰባኪና የማኅበራዊ ሚዲያ አጽዳቂ ዘመቻ፣ እንዲሁም እያስገደለ አክብሩኝ እንደሚሉት አባቶች በመግለጫ እና በፕሮፓጋንዳ #የሐዋርያት #መንበር #ወራሽነትን ማጽናት አይቻልም። በብልጽግና መንግሥት ድጋፍ ሲፈልጉ #ወሊሶ ሳይመች አምስት ኪሎ እየመጡ #ብፁዕ መባባል ለረዥም ጊዜ በጥምቀት ልጆች ደምና የነፍስ ጉዳት ላይ መቀለድ የሚቀጥል አይመስለኝም። ወይ ብፁዕ #ሆኖ #መገኘት ወይ ከገዳዮቹ ጋር ካራ ይዞ መሀዝገዝ! ቀኖና ሐዋርያትን በአብይ ደብዳቤ ቀይረው እና ሕገ ቤተ ክርስቲያንን ሸቅጠው በእንድ የደሞዝ ሰንድ ላይ መገረም. ወይንም ነአንድ አዳሽ መሰብሰብ "ከቅዱስ" ሲኖዶስነትን አያሟላም። ወድ ጎሣ ምክር ቤት የወረደ ድብሰባ በወሊሶም በአራት ኩሎም ተሀኝቶ በምእመናን ደም ላይ ቆሞ "እኛና መንገድ ቅዱስ ወስነናል" እያሉ በእግዚአብሔር ላይ ጽረፈት ማወጁ ማብቃት አለበት ። እግዚአብሔርን በመዳፈር አሰገዳዩን "ብፁዕ"፣ ተሿሚውን የጎሣ የፓርቲ ወኪል በቅድስና ሕይወቱ መሆኑ ቀርቶ "ንፁህ ጎሣ" እያሉ በሚሾሙት ሰው ጉባኤ መንፈስ ቅዱስ ወሰነ ማለት እንዴት ይቻላል? የተቀደሰውን የሐዋርያት መንበር በስሙ ቢጠሩበትም ይህ ገባኤ ከሚያስጨፈጭፈን፣ ክብረ-ሰብእና ፍትሕን ከማያውቁት ከዘረኞቹ ከጀዋር መሀመድ ተከታዮች፣ ከመረራ ጉዲና ፓርቲ፣ ከሽመልስ አብዲሳ ካቢኔ፣ ከአብይ አህመድ መንግሥታዊ መዋቅር የሚለዩበት ሚዛን ምንድነው? ይለያል ወይንም።አይለይም ለማለት በማስረጃ እንሟገት። በሚከተሉት የምርመራ ነጥቦች እንፈትሽ ----- የሲኖዶሱ ከተጠሩትብተቋማት ጋር ፩) በአጀንዳቸው ፪) በቃለ ጉባኤአቸው ፫) ሞትና ስደትን በመከላከል ፬) ፍትህን እና እውነትን በመከላከል ፭) የተጎዱትን በማስካስና በማጽናናት ፮) ገዳዮችን በማውገዝ ፯) መናፍቃንን ከምእመናንን በመለየት ----- ሲመዘኑ:- ---- በምን እንደሚለዩ በትህትና የሚያስርዳኝ ሰው ፈልጋለሁ። ማስመሰል፣ እውነትን ሸቅጦ፣ የተቀደሰ ቀኖና ትውፊትን ደፍጥጦ ለአድርባይነት መካካብ አያድነንም። በፍቅር እውነትን እየተነጋገርንና ተጨካክነን የድኅነት መንገዳችንን እንሥራ! ሐዋርያው በፊልጵስዩስ መልእክቱ 2:12 "ስለዚህ፥ ወዳጆቼ ሆይ፥ ሁልጊዜ እንደ ታዘዛችሁ፥ በእናንተ ዘንድ በመኖሬ ብቻ ሳይሆን ይልቁን አሁን ስርቅ፥ በፍርሃትና በመንቀጥቀጥ የራሳችሁን መዳን ፈጽሙ፤'

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ገድሎና አስገድሎ ብፁዕ እየተባሉ መኖር የተፈቀደላቸው ጳጳሳትና ቆሞሳት እንዳይረሱ

ከጥር 27 ጀምሮ በተለያዩ የኦሮምያ ከተሞች በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቀኖና ውጭ የተሾሞና በቅዱስ ሲኖዶስ ተወግዘው የተለዩ አካላትን ወደ ቤተ ክርስቲያን እናስገባለን ባሉ የመንግስት የጽጥታ አካላት በተትኮሰ ጥይትና ሕገ ወጡ ቡድን ባደራጃቸው ወጣቶች ተደብድበው የተገደሉና የቆሰሉ  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ካህናትና ምእመናን።።   1)  ሻሸመኔ ከተማ   I.   የተገደሉ 1.  አያሌው ተረፈ ●   በሻሸመኔ የደብረ አስቦ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ማህደረ ፃድቃን ሰንበት ትምህርት ቤት አባል ●  ጥር 27 ዓ/ም በሻሸመኔ ከተማ በጸጥታ ሃይሉ በሚመራ የጨፍጫፊ ቡድን በደረሰበት ከፍተኛ ደብደባ ወደ ሆስፒታል ገባ ●  በአላቲዮን ሆስፒታል ሕክምና እየተደረገለት ሕይወቱን ማትረፍ አልተቻለም ●  በ ጥር 30 2015 ዓ/ም  ሰማዕትነትን ተቀብሏል       2.  ሊቀ ኅሩያን ቀሲስ ሐረገወይን ●  የሻሸመኔ ደብረ ስብሐት ቅዱስ ሚካኤል አገልጋይ የነበሩት ●  በሻሸመኔ በሕገወጦች በጸጥታ አካላት  በበግፍ በዱላ ተቀጥቅጠው በጭንቅላታቸው በእጅና በእግራቸው ላይ በደረሰባቸው ድብደባ በሀዋሳ ሕክምና እያሉ አርፈዋል። ●  ከመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች በተተኮሰ ጥይት ተመትተው  በያኔት ሆስፒታል ሕክምና ሲደረግላቸው ቢቆዩም ሕይወታቸውን ማትረፍ አልተቻለም። ●  በዛሬው ዕለት ጥር 30 2015 ዓ/ም  ሰማዕትነትን ተቀብለዋል።     3.  ዘማሪ ፍቃዱ ደጉ ●  የቅዱስ ሚካኤል ከሣቴ ብርሃን ሰ/ትቤት አገል...

ኢትዮጵያ የተገዳደሯትን ሁሉ ቅኝ ገዥወች የተከላከለችባቸው፣ የተዋጋችባቸውና ነጽነቷን ያስከበረችባቸው እሴቶች; በቀሲስ አስተርአየ ጽጌ

የጽዋዕ ማህበራትና ሰንበቴ ከቅድስት ድንግል ማርያም ጋራ የተሳሰሩት የጽዋ ማሕበራትና ሰንበቴወች ናቸው፡፡  ኢትዮጵያ የተገዳደሯትን ሁሉ ቅኝ ገዥወች የተከላከለችባቸው፣ የተዋጋችባቸውና ነጽነቷን ያስከበረችባቸው እሴቶች  ቀሲስ አስተርአየ ጽጌ  nigatuasteraye@gmail.com  ሚያዚያ ፳፩ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም.  (April 28, 2025)  መግቢያ  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያናችን ኩለንታዊት ቀዳማዊት ደኀራዊት፡ ዘመናዊት ናት ስትባል እም ኀበ አልቦ አይደለም፡፡ በብዙ እሴቶቿ ነው፡፡ ኩለንታዊት ከምታደርጋት ከብዙ እሴቶቿ መካከል የጽሑፌ መነሻ የሆኑት ከቅድስት ድንግል  ማርያም ጋራ የተሳሰሩት የጽዋ ማሕበራትና ሰንበቴወች ናቸው፡፡ ስንበቴ በቀጥታ ከእግዚአብሔር የታዘዘች ናት፡፡ የጽዋ ማኅበርም እንደ ሰንበቴው ቀጥታ ከግዚአብሔር ባይሆንም፡ በዮቶር በኩል ለሙሴ የደረሰው የግዚአብሔር ምሪት ናት፡፡ የጽዋ ማሕበርና ሰንበቴ የትርጉማቸው መነሻ፡ መድረሻና የመጨረሻ ዋና ዓላማቸው ሰባዊ ክብርና ነጻነት ነው፡፡   ኢትዮጵያ የተፈታተኗትን ሁሉ ቅኝ ገዥወች ከተከላከለችባቸው ከተዋጋችባቸውና ነጽነቷን ካስከበረችባቸው ዋናወቹ እሴቶቿ ውስጥ የጽዋ ማሕበራትና ሰንበቴወች ናቸው፡፡ በቅኝ ገዥወች ሲቀጠቀጡ ከኖሩት ካጎራባች አገሮች ልዩና የነጻነት ምሳሌ ያደርጓትም የጽዋ ማህበርና ሰንበቴ ናቸው፡፡ የጽዋ ማኅበራትና የሰንበቴ ድርጅቶች እንዴት ተመሰረቱ? ለኢትዮጵያ ምን ጠቀሙ? ትሩፋታቸው ምንድነው? የደርግንና የወያኔን ዘመናት እንዴት ተሻገሩ? በብልጽግና ዘመንስ እንዴት ናቸው? እንዴት ይቀጥሉ ? የሚሉትን ጥያቄወች ለመመለስ ከጽዋ ማኅበር እንጀምር፡፡   የጽዋ ማኅበር መነሻ...

ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን እና ቋንቋና ማንነት ተኮር እንቅስቃሴዎች

  ኦ ርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን እና ቋንቋና ማንነት ተኮር እንቅስቃሴዎች   ፩ . ቋንቋን በተመለከተ ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮና ትውፊት ከሰው ልጅ መበደል በፊት ፍጥረት ሁሉ የሚግባባው በአንድ ቋንቋ ነበር፡፡ “ ምድርም ሁሉ በአንድ ቋንቋና በአንድ ንግግር ነበረች” እንዲል፡፡ ዘፍ. 11፡1 በኃጢአት ምክንያት ግን ሰውና መላው ፍጥረት በአንድ ቋንቋ መግባባታቸው ቀረ፡፡ ኃጢአት እየበዛ ሲሄድ የሰው ልጅ ቋንቋም በባቢሎን ተደበላለቀ፣ አንዳቸው ከሌላቸው ጋር የማይግባቡ ብዙ ዓይነት ቋንቋዎችም ተፈጠሩ፡፡ በበደል የመጣውን ሁሉ ሊያስተካክልና ሊያድን በመጣው በአምላካችንና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አዳኝነት ያ የቀደመው ጸጋ ስለ ተመለሰልን በበዐለ ሃምሳ ሰዎች በልዩ ልዩ ቋንቋ አንድ ዐይነት የእግዚአብሔርን መልእክት ሰሙ፡፡ በዚህ ጸጋ የተጠቀሙና የበቁ ቅዱሳን የእንስሳትን ቋንቋ እስከ ማወቅ ደረጃ ይደርሳሉ፡፡   የክርስትና ጉዞ ወደ ቀደመው በአንድ ቋንቋ መግባባት መመለስ ነው፡፡ ወደዚያ ለመድረስ ደግሞ ሰው የእግዚአብሔርን ቃል በሚሰማው ቋንቋ መማር አለበት፡፡ በበዐለ ሃምሳ ጊዜ ለቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስ ብዙ ቋንቋ የገለጠላቸው ሰውን ሁሉ የእግዚአብሔርን የማዳን ጸጋ በሚሰማው ቋንቋ እንዲያስተምሩት ነው፡፡ ሆኖም ቋንቋ መልእክት ማድረሻና መግባቢያ እንጂ ከዚያ ያለፈ ሰዎችን በሆነ መደብ ለመመደብና የልዩነት አጥር ለመሥራት እንደ መሳሪያ ሊሆን አይገባውም፡፡ ይህ ከክርስትና ዐላማ ጋር ተቃራኒ ነው፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያት ወደ ዐለም ሁሉ ሲልካቸው ሰዎች የሚቀበሏቸው በሚያስተምሩት ትምህርት መሠረት ነበር እንጂ በትውልድ፣ በብሔርና በመሳሰለው መስፈርት የእኛ ናቸው/አይደሉም በሚል አልነበረም፡፡ የቤተ ክርስቲያ...