ክብር ለማን ይገባል? ጌትችን፣ አምላካችን፣ መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዮሐንስ ወንጌል ፲፪፣ ፵፫ "ከእግዚአብሔር ክብር ይልቅ የሰውን ክብር ወደዋልና።" ብሎ ፈሪሳውንን ሲወቅሳቸው ለተከተሉት እና የዚህን ክፉ ዓለም ቅጣት ሳይሰቀቁ መኖር ለተገባቸው ደግሞ በዚሁ መጽሐፍ ውስጥ ፲፯: ፳፪-፳፫ በተዋሐደው ሥጋ ለሚመለከቱትና ግራ ለተጋቡት ምሥጢር ሱገልጥ ወደ ሲጸልይ "እኛም አንድ እንደ ሆንን አንድ ይሆኑ ዘንድ፤ እኔም በእነርሱ አንተም በእኔ ስትሆን፥ በአንድ ፍጹማን እንዲሆኑ፥ የሰጠኸኝን ክብር እኔ ሰጥቻቸዋለሁ፤ እንዲሁም ዓለም አንተ እንደ ላክኸኝ በወደድኸኝም መጠን እነርሱን እንደ ወደድሃቸው ያውቃል።" ብሎ ክብር የሚገባቸው እግዚአብሔር አብ ፣ እግዚአብሔር ወልድን በወደደበት የባህርይ ተዋህዶ አንጻር በጸጋ የፍቅር ተዋህዶን ከእግዚአብሔር ለማግኘት የሚጋደሉትን ወገኖቹን፣ በዚህ ተጋድሎ ፍቅረ እግዚአብሔርን ቀምሰው በፍቅረ ቢፅ የሰጠሙትን፣ እነርሱ የቀመሱትን ደግሞ ሌሎችም አማኞች ሁሉም እንዲቀምሱላቸው፣ በክርስቶስ ሁሉም የጥምቀት ልጆች እንዲዋሀዱላቸው ሕይወታቸውን የሰጡትን ሐርያትንና የሚመስሏቸውን "አባቶች" ልንል፣ ከእግዚአብሔር በነሱት ክብር ልናከብራቸው ይገባል። ይህን የምናደርገው ስለታዘዝን ብቻ ሳሆን ክርስትናን ለመኖር የምግብ ጀመሪያ መግቢያ በርና ግዴታችን ስለሆነም ነው፤ ከባህርይ መድኀኒት ከክርስቶስ የሚያገናኙ ሰዎች የጸጋ መድኀኒት ናቸው እና መዳኛውን የማያከብር ኢአማኒ ብቻ ነው። በዚህ መልክ ለአባቶች ክብር ይገባቸዋል። ነገር ግን እውነተኛ አባቶች የወሰዱትን የክህነት ደ...
This is a spot where I post and share part of my daily reality. I would love to hear from others too to learn how differently we interpret daily encounters including our imaginations. ይህ ሥፍራ የየዕለት ገጠመኞቼን፣ እንዴት በዕለቱ እንተረደሁትና የማስበውን ለሌሎች ያማጋራበት ነው፡፡ የሌሎችን በመስማትና ምን ያህል ዓለማችንን በተለያየ መንገድ እንደምንመለከታት ለመማር እጓጓለሁ፡፡