ወደ ዋና ይዘት ዘለው ይሂዱ

ፖልቲካ-ሠራሽ ከሰውነት ከሚያሳንስ ኑዑስ-ጎሣዊ-ማንነት መገላገል መከራችንን ይቀንሳል

 የጎሣ ልሂቃንና ጭፍን ተክታዮቻቸውን የምመክርው ነገር አለኝ፦

በቋንቋ፣ በትርክትና ፖልቲካ-ሠራሽ ከሰውነት በሚያሳንስ ኑዑስ-ጎሣዊ-ማንነት የአእምሮ መዛባት ራሳችሁን ማዳን ጥቅሙ ለራሳችሁ ነው!

ክርስቶስን በመዘንጋት ጎሣቸውን እንደ ጣዖት የሚያገልግሉ የፓርቲ አገልጋየ አባት መሰል ግለሰቦች ሲገኙና ሲወቀሱ እጅግ የሚያማቸው የኦነግ ኦሮሙማ   የፋሺዝም አእምሮዎች እጅግ ይንጫጫሉ።

ስሞኑን አቡነ ገብርኤል በሚያሠራጩት ኑፋቄ ምክንያት መወቀሳቸውን ከሚመለከታቸው ከሊቃውንት ጉባኤ፣ ምሥጢር ካደላድሉ መምህራን፣ ከሲኖዶስ ቀድመው   ተቆጭተው የሚይውለበለቡት ኦነጋውያንና የብልጽግና ወንጌል አራማጆችና  ጸረ-ነባር እሤት እንዳላቸው ላልፉት 50 ዓመታት ሀገር በማመስ የሚታወቁት ናቸው።

#OMN የተባለው ቀንደኛ የዘ*ር ማ*ጥ**ፋት  አዋጅን ያለ ድካም የሚለፍፈው ሚዲያ ይህንኑ የተለመደ አሉታዊ ጣልቃ ገብነቱን ቀጥሎበት የሃይማኖትን ጉዳይ ለኦሮሞ ፖለቲካ ማድመቂያ ተጥቅሞበት ታይቷል። 

በዚህ ሚዲያ "አማራን ከ30 ሚሊዮነ ውድ 120 ሺ መቀንስ፣ manegable በማድረግ ሰሜን ሸዋ  መንዝ ማስቀመጥ"  የሚል ፕሮፓጋንዳ ጋዚጠኛ ደጀኔ በሚባል ግለሰብ አቅራቢነት የቀረብ ተወያይ ለተከታዮቹ ሲመክር  የሚዲያው ባለቤቶች ስለተስማማቸው እርምት አልወስዱም፣ ይቅርታም አልጠየቁበትም።  በተግባር ድግሞ በአማራ ስም ኦርቶዶክሳውያንን፣ ኦሮሞ ኦረቶዶክስ ክርስቲያኖችን ጨምሮ ማጽዳቱ በአርሲና ወለጋ ቀጥሏል። ይህ ሚዲያ ስለዚህ አይዘግብም።

በታሪክ እንደምናውቀው፦-
የጎሣ ፖለቲካ ከፋሺዝም አምልጦ አያውቅም። 

በሀገራችን ኦነግና ሕወሃት የተከሉት የፋሽዝምና አፓርታይድ  ርእዮት እውር ድንብሩን 50 ዓመት ሙሉ ቋንቋን፣ መልካዐ ምድርን፣ ትርክትን፣ ፊደልን፣ የድንጋይ ሀውልትን፣ የነገሥታት ዜና መዋዕልን ወዘተ የፖለቲካ ፍልስፍና ደም ማነሳቸውን የሚያሟሉበት የድሁራን ስልት ሆኖ በመተግበሩ የሕዝብ ደም መፍሰሱ ቀጥሏል። 

በዚህ የተዛባ እሳቤ መሠረትነት እየተካሄደ ያለው አስተዳደር   ዛሬ ያለውን የዘር ማጥፋት ዘመቻ ማካሄድ ብቻ ሳይሆን ለጎሣ ፖለቲካ የፋሽዚም ግብ የሚያገልግሉ ኦርቶዶክስ መሰል "አባት" ተብዬዎች እንደ አሸን ፈልተዋል።  እንዚህ አዳዲስ ፍሎች እንዲስተካከል ወቀሳ ሲሰነዘር የኦነግ ኦሮሙማውና የኦሮ-ዉሃቢዝም ቡድን በኦሮሞ ሕዝብ ስም ተሯሩጠው ይንጫጫሉ።

እንደኔ አስተሳሰብ ይህ መርዛማ ርእዮትና አዝሎት የሚሄድው ጥላቻ ላይ የተመሠረት የሐሰት ትርክት አስቀያሚ የሆነውን የፋሽዝም መልክ ዘ*ር በማ*ጥፋት ደሪጊቱ የበለጠ እየገለጠ ነው።  ዜጎች በሃይማኖት፣ በቋንቋ፣ በትርክትና ፖልቲካ-ሠራሽ ከሰውነት በሚያሳንስ ኑዑስ-ጎሣዊ-ማንነት የአእምሮ መዛባት ወጥተው እንደ ሰው ብቻ ራሳቸውን እንዲመለከቱና ክፋትን እንዲዋጉ እመኛለሁ።



አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ገድሎና አስገድሎ ብፁዕ እየተባሉ መኖር የተፈቀደላቸው ጳጳሳትና ቆሞሳት እንዳይረሱ

ከጥር 27 ጀምሮ በተለያዩ የኦሮምያ ከተሞች በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቀኖና ውጭ የተሾሞና በቅዱስ ሲኖዶስ ተወግዘው የተለዩ አካላትን ወደ ቤተ ክርስቲያን እናስገባለን ባሉ የመንግስት የጽጥታ አካላት በተትኮሰ ጥይትና ሕገ ወጡ ቡድን ባደራጃቸው ወጣቶች ተደብድበው የተገደሉና የቆሰሉ  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ካህናትና ምእመናን።።   1)  ሻሸመኔ ከተማ   I.   የተገደሉ 1.  አያሌው ተረፈ ●   በሻሸመኔ የደብረ አስቦ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ማህደረ ፃድቃን ሰንበት ትምህርት ቤት አባል ●  ጥር 27 ዓ/ም በሻሸመኔ ከተማ በጸጥታ ሃይሉ በሚመራ የጨፍጫፊ ቡድን በደረሰበት ከፍተኛ ደብደባ ወደ ሆስፒታል ገባ ●  በአላቲዮን ሆስፒታል ሕክምና እየተደረገለት ሕይወቱን ማትረፍ አልተቻለም ●  በ ጥር 30 2015 ዓ/ም  ሰማዕትነትን ተቀብሏል       2.  ሊቀ ኅሩያን ቀሲስ ሐረገወይን ●  የሻሸመኔ ደብረ ስብሐት ቅዱስ ሚካኤል አገልጋይ የነበሩት ●  በሻሸመኔ በሕገወጦች በጸጥታ አካላት  በበግፍ በዱላ ተቀጥቅጠው በጭንቅላታቸው በእጅና በእግራቸው ላይ በደረሰባቸው ድብደባ በሀዋሳ ሕክምና እያሉ አርፈዋል። ●  ከመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች በተተኮሰ ጥይት ተመትተው  በያኔት ሆስፒታል ሕክምና ሲደረግላቸው ቢቆዩም ሕይወታቸውን ማትረፍ አልተቻለም። ●  በዛሬው ዕለት ጥር 30 2015 ዓ/ም  ሰማዕትነትን ተቀብለዋል።     3.  ዘማሪ ፍቃዱ ደጉ ●  የቅዱስ ሚካኤል ከሣቴ ብርሃን ሰ/ትቤት አገል...

ኢትዮጵያ የተገዳደሯትን ሁሉ ቅኝ ገዥወች የተከላከለችባቸው፣ የተዋጋችባቸውና ነጽነቷን ያስከበረችባቸው እሴቶች; በቀሲስ አስተርአየ ጽጌ

የጽዋዕ ማህበራትና ሰንበቴ ከቅድስት ድንግል ማርያም ጋራ የተሳሰሩት የጽዋ ማሕበራትና ሰንበቴወች ናቸው፡፡  ኢትዮጵያ የተገዳደሯትን ሁሉ ቅኝ ገዥወች የተከላከለችባቸው፣ የተዋጋችባቸውና ነጽነቷን ያስከበረችባቸው እሴቶች  ቀሲስ አስተርአየ ጽጌ  nigatuasteraye@gmail.com  ሚያዚያ ፳፩ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም.  (April 28, 2025)  መግቢያ  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያናችን ኩለንታዊት ቀዳማዊት ደኀራዊት፡ ዘመናዊት ናት ስትባል እም ኀበ አልቦ አይደለም፡፡ በብዙ እሴቶቿ ነው፡፡ ኩለንታዊት ከምታደርጋት ከብዙ እሴቶቿ መካከል የጽሑፌ መነሻ የሆኑት ከቅድስት ድንግል  ማርያም ጋራ የተሳሰሩት የጽዋ ማሕበራትና ሰንበቴወች ናቸው፡፡ ስንበቴ በቀጥታ ከእግዚአብሔር የታዘዘች ናት፡፡ የጽዋ ማኅበርም እንደ ሰንበቴው ቀጥታ ከግዚአብሔር ባይሆንም፡ በዮቶር በኩል ለሙሴ የደረሰው የግዚአብሔር ምሪት ናት፡፡ የጽዋ ማሕበርና ሰንበቴ የትርጉማቸው መነሻ፡ መድረሻና የመጨረሻ ዋና ዓላማቸው ሰባዊ ክብርና ነጻነት ነው፡፡   ኢትዮጵያ የተፈታተኗትን ሁሉ ቅኝ ገዥወች ከተከላከለችባቸው ከተዋጋችባቸውና ነጽነቷን ካስከበረችባቸው ዋናወቹ እሴቶቿ ውስጥ የጽዋ ማሕበራትና ሰንበቴወች ናቸው፡፡ በቅኝ ገዥወች ሲቀጠቀጡ ከኖሩት ካጎራባች አገሮች ልዩና የነጻነት ምሳሌ ያደርጓትም የጽዋ ማህበርና ሰንበቴ ናቸው፡፡ የጽዋ ማኅበራትና የሰንበቴ ድርጅቶች እንዴት ተመሰረቱ? ለኢትዮጵያ ምን ጠቀሙ? ትሩፋታቸው ምንድነው? የደርግንና የወያኔን ዘመናት እንዴት ተሻገሩ? በብልጽግና ዘመንስ እንዴት ናቸው? እንዴት ይቀጥሉ ? የሚሉትን ጥያቄወች ለመመለስ ከጽዋ ማኅበር እንጀምር፡፡   የጽዋ ማኅበር መነሻ...

ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን እና ቋንቋና ማንነት ተኮር እንቅስቃሴዎች

  ኦ ርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን እና ቋንቋና ማንነት ተኮር እንቅስቃሴዎች   ፩ . ቋንቋን በተመለከተ ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮና ትውፊት ከሰው ልጅ መበደል በፊት ፍጥረት ሁሉ የሚግባባው በአንድ ቋንቋ ነበር፡፡ “ ምድርም ሁሉ በአንድ ቋንቋና በአንድ ንግግር ነበረች” እንዲል፡፡ ዘፍ. 11፡1 በኃጢአት ምክንያት ግን ሰውና መላው ፍጥረት በአንድ ቋንቋ መግባባታቸው ቀረ፡፡ ኃጢአት እየበዛ ሲሄድ የሰው ልጅ ቋንቋም በባቢሎን ተደበላለቀ፣ አንዳቸው ከሌላቸው ጋር የማይግባቡ ብዙ ዓይነት ቋንቋዎችም ተፈጠሩ፡፡ በበደል የመጣውን ሁሉ ሊያስተካክልና ሊያድን በመጣው በአምላካችንና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አዳኝነት ያ የቀደመው ጸጋ ስለ ተመለሰልን በበዐለ ሃምሳ ሰዎች በልዩ ልዩ ቋንቋ አንድ ዐይነት የእግዚአብሔርን መልእክት ሰሙ፡፡ በዚህ ጸጋ የተጠቀሙና የበቁ ቅዱሳን የእንስሳትን ቋንቋ እስከ ማወቅ ደረጃ ይደርሳሉ፡፡   የክርስትና ጉዞ ወደ ቀደመው በአንድ ቋንቋ መግባባት መመለስ ነው፡፡ ወደዚያ ለመድረስ ደግሞ ሰው የእግዚአብሔርን ቃል በሚሰማው ቋንቋ መማር አለበት፡፡ በበዐለ ሃምሳ ጊዜ ለቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስ ብዙ ቋንቋ የገለጠላቸው ሰውን ሁሉ የእግዚአብሔርን የማዳን ጸጋ በሚሰማው ቋንቋ እንዲያስተምሩት ነው፡፡ ሆኖም ቋንቋ መልእክት ማድረሻና መግባቢያ እንጂ ከዚያ ያለፈ ሰዎችን በሆነ መደብ ለመመደብና የልዩነት አጥር ለመሥራት እንደ መሳሪያ ሊሆን አይገባውም፡፡ ይህ ከክርስትና ዐላማ ጋር ተቃራኒ ነው፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያት ወደ ዐለም ሁሉ ሲልካቸው ሰዎች የሚቀበሏቸው በሚያስተምሩት ትምህርት መሠረት ነበር እንጂ በትውልድ፣ በብሔርና በመሳሰለው መስፈርት የእኛ ናቸው/አይደሉም በሚል አልነበረም፡፡ የቤተ ክርስቲያ...