የጎሣ ልሂቃንና ጭፍን ተክታዮቻቸውን የምመክርው ነገር አለኝ፦
በቋንቋ፣ በትርክትና ፖልቲካ-ሠራሽ ከሰውነት በሚያሳንስ ኑዑስ-ጎሣዊ-ማንነት የአእምሮ መዛባት ራሳችሁን ማዳን ጥቅሙ ለራሳችሁ ነው!
ክርስቶስን በመዘንጋት ጎሣቸውን እንደ ጣዖት የሚያገልግሉ የፓርቲ አገልጋየ አባት መሰል ግለሰቦች ሲገኙና ሲወቀሱ እጅግ የሚያማቸው የኦነግ ኦሮሙማ የፋሺዝም አእምሮዎች እጅግ ይንጫጫሉ።
ስሞኑን አቡነ ገብርኤል በሚያሠራጩት ኑፋቄ ምክንያት መወቀሳቸውን ከሚመለከታቸው ከሊቃውንት ጉባኤ፣ ምሥጢር ካደላድሉ መምህራን፣ ከሲኖዶስ ቀድመው ተቆጭተው የሚይውለበለቡት ኦነጋውያንና የብልጽግና ወንጌል አራማጆችና ጸረ-ነባር እሤት እንዳላቸው ላልፉት 50 ዓመታት ሀገር በማመስ የሚታወቁት ናቸው።
#OMN የተባለው ቀንደኛ የዘ*ር ማ*ጥ**ፋት አዋጅን ያለ ድካም የሚለፍፈው ሚዲያ ይህንኑ የተለመደ አሉታዊ ጣልቃ ገብነቱን ቀጥሎበት የሃይማኖትን ጉዳይ ለኦሮሞ ፖለቲካ ማድመቂያ ተጥቅሞበት ታይቷል።
በዚህ ሚዲያ "አማራን ከ30 ሚሊዮነ ውድ 120 ሺ መቀንስ፣ manegable በማድረግ ሰሜን ሸዋ መንዝ ማስቀመጥ" የሚል ፕሮፓጋንዳ ጋዚጠኛ ደጀኔ በሚባል ግለሰብ አቅራቢነት የቀረብ ተወያይ ለተከታዮቹ ሲመክር የሚዲያው ባለቤቶች ስለተስማማቸው እርምት አልወስዱም፣ ይቅርታም አልጠየቁበትም። በተግባር ድግሞ በአማራ ስም ኦርቶዶክሳውያንን፣ ኦሮሞ ኦረቶዶክስ ክርስቲያኖችን ጨምሮ ማጽዳቱ በአርሲና ወለጋ ቀጥሏል። ይህ ሚዲያ ስለዚህ አይዘግብም።
በታሪክ እንደምናውቀው፦-
የጎሣ ፖለቲካ ከፋሺዝም አምልጦ አያውቅም።
በሀገራችን ኦነግና ሕወሃት የተከሉት የፋሽዝምና አፓርታይድ ርእዮት እውር ድንብሩን 50 ዓመት ሙሉ ቋንቋን፣ መልካዐ ምድርን፣ ትርክትን፣ ፊደልን፣ የድንጋይ ሀውልትን፣ የነገሥታት ዜና መዋዕልን ወዘተ የፖለቲካ ፍልስፍና ደም ማነሳቸውን የሚያሟሉበት የድሁራን ስልት ሆኖ በመተግበሩ የሕዝብ ደም መፍሰሱ ቀጥሏል።
በዚህ የተዛባ እሳቤ መሠረትነት እየተካሄደ ያለው አስተዳደር ዛሬ ያለውን የዘር ማጥፋት ዘመቻ ማካሄድ ብቻ ሳይሆን ለጎሣ ፖለቲካ የፋሽዚም ግብ የሚያገልግሉ ኦርቶዶክስ መሰል "አባት" ተብዬዎች እንደ አሸን ፈልተዋል። እንዚህ አዳዲስ ፍሎች እንዲስተካከል ወቀሳ ሲሰነዘር የኦነግ ኦሮሙማውና የኦሮ-ዉሃቢዝም ቡድን በኦሮሞ ሕዝብ ስም ተሯሩጠው ይንጫጫሉ።
እንደኔ አስተሳሰብ ይህ መርዛማ ርእዮትና አዝሎት የሚሄድው ጥላቻ ላይ የተመሠረት የሐሰት ትርክት አስቀያሚ የሆነውን የፋሽዝም መልክ ዘ*ር በማ*ጥፋት ደሪጊቱ የበለጠ እየገለጠ ነው። ዜጎች በሃይማኖት፣ በቋንቋ፣ በትርክትና ፖልቲካ-ሠራሽ ከሰውነት በሚያሳንስ ኑዑስ-ጎሣዊ-ማንነት የአእምሮ መዛባት ወጥተው እንደ ሰው ብቻ ራሳቸውን እንዲመለከቱና ክፋትን እንዲዋጉ እመኛለሁ።
አስተያየቶች