ወደ ዋና ይዘት ዘለው ይሂዱ

የምመኛት ኢትዮጵያና ሕዝቧ

Let's dialogue about the Orthodox

ምን አይነት ኢትዮጵያ ትመኛለህ?

እኔ፦

1.       የሰው ልጅ ሰው በመሆኑ ብቻ የምከበርባት አገርና ይህን የሚያስከብር መንግሥት የሚመራት አገር፤  

2.      ሃይማኖት፥ ባህል፥ ጾታ፥ ቋንቋ፥ ያለፈ ታሪክ፥ አሠፋፈርና የኑሮ ዘይቤ ሁሉ የሰውነትና የዜግነት ማንነቴ ላይ ምንም ተጽእኖ የማያሳድሩብተ ሥርዓተ መንግሥትና ሥርዓተ ማኅበር የሚገለጽባት አገር፤

3.      የአገር አስተዳደር አከላለል ከቋንቋና ከፖለቲካ ነጻ ሆነው በልማት ቅልጥፍና፥ በንዑስ ማንነት መዋሃድ መሳለጥ ሚዛን ብቻ የሆነባት አገር፤

4.      ፖለቲካ መንግሥት ከሃይማኖት፥ ከጎሣ ቡድን፥ ከቋንቋ፥ ከፖለቲካ ሠራሽ ማንነትና አግላይ ትርክቶች ነጻ ሆኖ ለሰው ክብር፥ ለፍትሕና ለሕዝብ ሰላምና መዋሀድ የሚሠራ የሆነባት አገር፤

5.      ወታደር ትጥቅ ይዞ አገር ውስጥ የማይታይባት፥ ድንበር ብቻ በወታደር የሚጠበቅባት አገር፤

6.      ፖሊስ ሀብታምና መንግሥት ዱላ ሆኖ ከማገልገል ወጥቶ  ሕዝብ የሚጠብቅባት  አገር፤

7.      ፍትሕ በማሥበራዊ፥ በምንግሥታዊ፥ በሃይማኖታዊና ባህላዊ መዋቅራት ውስጥ ሁሉ እውቅና አግኝቶ የሚተበርበት አገር፤

8.      አገርና ሕዝብ ለምግብ፥ ለመድኃኒት፥ አገርን ከውጭ ወረራ ለመከላከል በሚያስችላቸው ግብአቶችና እውቀቶች ሁሉ ከጥገኝነት ነጻ የሆኑባት የሉዓላዊ ሕዝብ አገር

9.      ከባእዳን ጋር ተመሳጥረው አገራቸውን የሚወጉ፥ ሕዝባቸውን በሐሰተኛ ትርክትና በተውሶ የፖለቲካ ርእዮት የሚያምሱ አገር-ጠል እና ውጭ ናፋቂ “ምሁራን” ተብዬ የጠላት አገልጋዮች በአገር ክህደት የሚቀጡባት አገር

10.    የሐሰት ትርክት ከፍተኛ የአገር ወንጀል የሚደረግባት፥ የፖለቲካ ቁማርና ማጭበርበር በሚት የሚያስቀጣባት አገር።

ይህን አይነት አገር

ü  የብሔር ፖለቲካና ብሔርተኝነት አይሰጠነም።

ü  ብልጽግና ሕወሃት፥ ኦነግ አይሰጡንም።

ü  ከውጭ የምንዋሰው የፖለቲካ ርእዮትና ውጭ ናፋቂ ምሁራን አይሰጡንም

የዚህን አይነት አገር የምናገኘው፦ ሁላችንም ተነስተን

ü  ለክብረ-ሰብእ ስንቆም

ü  ከዘረኛ የቡድን ዕሳቤ ባርነት ራሳችንን ነጻ ስናወጣ

ü  ለፍትሕ ስንሟገትና እኛም በአቅማችን ፍትሓዊ ስንሆን

ü  ከስስት፥ ከቅሚያ፥ ከልዩ ማንነት የፋሽት ፖለቲካ መለየት ብቻ ሳይሆን ጠላታችን ነው ብለን ስነዋጋው

ü  አገራችንን በመስዋዕትነታችን እንደምንጠብቃት ከፋፋዮችን ጠላቶቻችን ናቸው ብለን ስንስማማ

ü  ዐመሓራነትን ከደምና አጥንት ስሌትና ቀመር አስወጥተን ለሁሉም የሰው ልጆች የሚመጥን እሤት ነው ብለን የራሳችን ስናደርገውና አብረን ስንቆም፥

ü  አንዲሁም ዐመሓራነትን  ከሕወሃትና ኦነጋዊነት ከብሔርተኝነት  መርዝ ስንጠብቀው

 

YOUTUBE:- https://www.youtube.com/@Orthodox_Secular_FantahunWakie/videos

ትዊተር፦ @fwakie
FB:- https://www.facebook.com/fwakie

Blog:- https://ethiopiaorthodoxchristian.blogspot.com

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ገድሎና አስገድሎ ብፁዕ እየተባሉ መኖር የተፈቀደላቸው ጳጳሳትና ቆሞሳት እንዳይረሱ

ከጥር 27 ጀምሮ በተለያዩ የኦሮምያ ከተሞች በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቀኖና ውጭ የተሾሞና በቅዱስ ሲኖዶስ ተወግዘው የተለዩ አካላትን ወደ ቤተ ክርስቲያን እናስገባለን ባሉ የመንግስት የጽጥታ አካላት በተትኮሰ ጥይትና ሕገ ወጡ ቡድን ባደራጃቸው ወጣቶች ተደብድበው የተገደሉና የቆሰሉ  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ካህናትና ምእመናን።።   1)  ሻሸመኔ ከተማ   I.   የተገደሉ 1.  አያሌው ተረፈ ●   በሻሸመኔ የደብረ አስቦ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ማህደረ ፃድቃን ሰንበት ትምህርት ቤት አባል ●  ጥር 27 ዓ/ም በሻሸመኔ ከተማ በጸጥታ ሃይሉ በሚመራ የጨፍጫፊ ቡድን በደረሰበት ከፍተኛ ደብደባ ወደ ሆስፒታል ገባ ●  በአላቲዮን ሆስፒታል ሕክምና እየተደረገለት ሕይወቱን ማትረፍ አልተቻለም ●  በ ጥር 30 2015 ዓ/ም  ሰማዕትነትን ተቀብሏል       2.  ሊቀ ኅሩያን ቀሲስ ሐረገወይን ●  የሻሸመኔ ደብረ ስብሐት ቅዱስ ሚካኤል አገልጋይ የነበሩት ●  በሻሸመኔ በሕገወጦች በጸጥታ አካላት  በበግፍ በዱላ ተቀጥቅጠው በጭንቅላታቸው በእጅና በእግራቸው ላይ በደረሰባቸው ድብደባ በሀዋሳ ሕክምና እያሉ አርፈዋል። ●  ከመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች በተተኮሰ ጥይት ተመትተው  በያኔት ሆስፒታል ሕክምና ሲደረግላቸው ቢቆዩም ሕይወታቸውን ማትረፍ አልተቻለም። ●  በዛሬው ዕለት ጥር 30 2015 ዓ/ም  ሰማዕትነትን ተቀብለዋል።     3.  ዘማሪ ፍቃዱ ደጉ ●  የቅዱስ ሚካኤል ከሣቴ ብርሃን ሰ/ትቤት አገል...

ኢትዮጵያ የተገዳደሯትን ሁሉ ቅኝ ገዥወች የተከላከለችባቸው፣ የተዋጋችባቸውና ነጽነቷን ያስከበረችባቸው እሴቶች; በቀሲስ አስተርአየ ጽጌ

የጽዋዕ ማህበራትና ሰንበቴ ከቅድስት ድንግል ማርያም ጋራ የተሳሰሩት የጽዋ ማሕበራትና ሰንበቴወች ናቸው፡፡  ኢትዮጵያ የተገዳደሯትን ሁሉ ቅኝ ገዥወች የተከላከለችባቸው፣ የተዋጋችባቸውና ነጽነቷን ያስከበረችባቸው እሴቶች  ቀሲስ አስተርአየ ጽጌ  nigatuasteraye@gmail.com  ሚያዚያ ፳፩ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም.  (April 28, 2025)  መግቢያ  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያናችን ኩለንታዊት ቀዳማዊት ደኀራዊት፡ ዘመናዊት ናት ስትባል እም ኀበ አልቦ አይደለም፡፡ በብዙ እሴቶቿ ነው፡፡ ኩለንታዊት ከምታደርጋት ከብዙ እሴቶቿ መካከል የጽሑፌ መነሻ የሆኑት ከቅድስት ድንግል  ማርያም ጋራ የተሳሰሩት የጽዋ ማሕበራትና ሰንበቴወች ናቸው፡፡ ስንበቴ በቀጥታ ከእግዚአብሔር የታዘዘች ናት፡፡ የጽዋ ማኅበርም እንደ ሰንበቴው ቀጥታ ከግዚአብሔር ባይሆንም፡ በዮቶር በኩል ለሙሴ የደረሰው የግዚአብሔር ምሪት ናት፡፡ የጽዋ ማሕበርና ሰንበቴ የትርጉማቸው መነሻ፡ መድረሻና የመጨረሻ ዋና ዓላማቸው ሰባዊ ክብርና ነጻነት ነው፡፡   ኢትዮጵያ የተፈታተኗትን ሁሉ ቅኝ ገዥወች ከተከላከለችባቸው ከተዋጋችባቸውና ነጽነቷን ካስከበረችባቸው ዋናወቹ እሴቶቿ ውስጥ የጽዋ ማሕበራትና ሰንበቴወች ናቸው፡፡ በቅኝ ገዥወች ሲቀጠቀጡ ከኖሩት ካጎራባች አገሮች ልዩና የነጻነት ምሳሌ ያደርጓትም የጽዋ ማህበርና ሰንበቴ ናቸው፡፡ የጽዋ ማኅበራትና የሰንበቴ ድርጅቶች እንዴት ተመሰረቱ? ለኢትዮጵያ ምን ጠቀሙ? ትሩፋታቸው ምንድነው? የደርግንና የወያኔን ዘመናት እንዴት ተሻገሩ? በብልጽግና ዘመንስ እንዴት ናቸው? እንዴት ይቀጥሉ ? የሚሉትን ጥያቄወች ለመመለስ ከጽዋ ማኅበር እንጀምር፡፡   የጽዋ ማኅበር መነሻ...

የሐሰት ትርክት ኦነጋውያንና የሕወሃታውያ የጋራ ስልት ከነግሥታት ወደ ተራ ግለሰቦች

✏️ እግዚአብሔር ይስጥልኝ።  እርሱ ይመስገን። ምድራችንን #በደም #ያጨቀየው $ህሊና #የነሳን ፣ #ልቦናችንን #ያጨለመን ፣ #ሰብእናችንን ያዋረደው:- 👉 የሕወሐታውያንናንየኦነጋውያን የንዑስ ማንነት የጎሣ ፖለቲካ የደንቆሮ ርእዮትና፣ 👉 መርዛማን ጥላቻን ለ፶ ዘመናት ያከፋፈሉት የሐሰት ትርክት ናቸው። ✏️እንደ ዳግማዊ #ምንልክ ያሉ   ከዋክብት መሪዎች፣ እንደራሴቻቸው፣ ደጃዝማቾችና ቀኝና ግራ አዝማቾቻቸው  ከትውልድ ትውልድ የሚሸጋገር ብዙ ውለታ ውለውልናል:- 👉 በዘመነ ኦቶማንና አውሮፓ፣ በዘመነ መሳፍንት የተበታተነውን እና የተቆነጻጸለውን፣ ጎሠኛ የአርብቶ አደሮች  መሬት ፍለጋ  የደመሰሱትን ክርስቲያናዊ የግዕዝ/የነፃነት ሥልጣኔ አሻራ እንዲያገግም ደክመውልናል፤ 👉 የጥንት አገርን እና ሕዝቦችን   በከፊልም ቢሆን በመሰብሰብ  ጠንካራና ብቸኛ የነጭ ቅኝነትንና ባርነትን በመከላከል፣ ከኦቶማን ቱርክ ወር ትናንት ውስጥ ጥረኛ  አህመድ ግራኝ በመጋደል  ልዩ የነጻነት ማንነት ያላትን አገር ብበቸኝነት በዓለም ካርታንላይ አቆይተዋል፤ 👉 የሬማ ግዛት በጎሣ ተብልቶ ፲ ትንንሽ ሲሆን ከበበባውን ተቋቁማ በዝኃነታችን በተመጋጋቢ አንድነት ከ፹ በላይብቋንቋ፣ ከዓለም ትልልቅ እምነቶች ክትስትናን ፣ ይሁዲን፣ እስልምናን፣ የእረማውያንን ቅሪት የሆኑ የባህል እምነቶችን ሁሉን ይዛ በአውሮፓ በአርብ አምሳል ሳትሠራ ለእኛ አቀብዋል፤ 👉 ወያኔና ኦነግ፣ ገንጣዩ ሻዕብያ፣ ከሃዲው የማርክሲስት የአእምሮ  ባሪያን ስብስብ  እስኪፈትናት ድረስ ራሷን የቻለች አገር እንድንፈጥር ያስተባበሩን ነገስታት የተመሰገኑ ናቸው። አገር ሲያረጅ ጃርት ያብቅላል እንዱሉ: መል...