የነጻነታችን ጊዜ እንዲቀርብ ሁሉም ድርሻውን የወጣ!!
ኦነግና ሕወሃት በሜንጫና በመጥረቢያ፣ በማምከንና በማደኸየት፣ በማፈናቀልና በማሳደድ፣ ፍትሕ በመንፈግና በለከት የለሽ የሐሰት ትርክታቸው በማጠልሸት የጀመሩትን ጠፋት #የብልጽግና መንግሥት ወደ መደበኛ፣ ግልጽና በአዋጅ የተደገፈ የዘር ማጥፋት መንግሥታዊ መደበኛ ተግባርነት አሳደገው።
በዚህ ሰይጣናዊ ፕሮጄክት ዒላማ የተደርገው #የአማራ ሕዝብ ራሱን ለማዳን ተጋድሎውን ጀምሮታል። አማራ መነሳት ተፈጥራዊ ህልውናን የማስጠብቅ ተፈጥሮአዊ ንቅናቄ ነው!! ትግሉ ለሰብአዊ ክብር፣ ለፍትሕ፣ ለእውነት የሚደርግ ተጋድሎ በመሆኑ ያሸንፋል። አለማሸነፍ ከምድር መጥፋት ነውና አለማሸነፍ አይቻልም!!
ግን ግን ---- በዚህ ወቅት አራት አይነት ዜጎች ይታዩኛል፦
(1) እንደ ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች በድንዛዜ ፈዝዞ የሚጨፈጨፍና ከብዙነት ወደ አናሳነት እየወረደ የሚገኝ፤ እየሞተና እየተሰደደ ነጭ ልብስ ለብሶ ሜዳ ላይ እየዘመር ለዓለም ሚዲያ ሁሉ "እዩኝ በሰላም እየኖርኩ ነው" እንዲልና እልቂቱን እንዲደብቅ በሚያደርጉት ግብዝና አስመሳይ አገልጋዮች የሚታለል፤ የገዛ እረኞቹ አደንዝዘው ለእርድ የሚያቀርቡት፣ እንዳይተባበር የሥላሴ ልጅነቱን አስክደው በጎሣ የሚካፈሉት ጳጳስት ያለው--- በዙ ሆኖ እያለ እንደ አናሳ፣ ታሪካዊ ሆኖ እያለ እንደ እንግዳ፣ በዓለ ሀገር ሆኖ እያለ ስደተኛ፣ እውነት እያለው እንደ ዋሾ የሚሰቃይና ሰቃዩን ለማስቆም ለህልውናው ተጋድሎ ያልጀመር፣ ግራ የተጋባ ።
(2) እንደ ኦሮሞና ትግራይ ወጣት የጎሣ ነጻ አውጭዎች የ50 ዓመታት የስሁት ርእዮትና ሐሰተኛ ትርክት ፕሮፓጋንዳ እውነቱን ሐሰት-ሐሰቱን እውነት አድርጎ እንዲመልክት አእምሮውን አጥቦ ሃይማኖቱን ክዶ፣ ዘሩን በጣዖትነት የሚያመልክ፤ ትልቋን ሀገሩን ክዶ ሕወሃትና ኦነግ በጻፉት የድንቁርናና የክፋት ሕገ-መንግሥት የከለለትን ቦታ ወደ ሀገር ለመለወጥ የሚገድልና የሚሞት፤ ለዚህ ዓላማዊ ሌሎች ጎርቤት ማኅበረስቦችን ወደ ጠላትነት የፈረጀና የነጻ አውጭዎቹ የአእምሮ ባሪያ፣ የጦርነት ማካሄጃ መሣሪያ የሆነ፤ ለእልቂትና መከራ መቀጠል መሣሪ መሆኑን ያላቆመ ወገን፣
(3) አማራ ነጻ ሲወጣ እኛም አብረን ከዚህ ከሕውሃትና ኦነግ የዘረኝነት ዲቃላ ከብልጽግና መንግሥት፣ ከእልቂትና ስደት ነጻ እንሆናለን ብሎ በዝምታ መከራ እየተቀበል፣ አንዳንዴም እንደ ሲዳማ የ2011 ነሐሴ አይነት በኦሮምያ ማፍያዎች እየተመራ ወንጀል እየፈጸመ፣ ኦርቶዶከሳውያንና አማሮችን እያጠቃ፣ እንደ አብዲ ኢሌ ዩጎና በሕወሃት ሤራ ክርስቲያን እያረደና በእሣት እየጠበሰ፣ አቢያተ ክርስቲያናትን እያጋየ የሚያደፍጥ፤ ለእውነት፣ ለፍትሕና ለሰባዊነት፣ ለሀገር ሰላም መከፈል የሚገባውን ዋጋ ሳይከፍል እይተሽሎከሎከ ቁሳዊ ሀብት ለማካበት የሚኖር አድርባይ ዜጋ አለ።
(4) የሀገር ሥልጣንን ይዞ በኦነግ-ኦሮሙማ፣ በኦሮ-ውሃቢዝም እና በናዚ-ፕሮቴስታንቲዝም ጥምረት፣ በኦሮምያ መንግሥትና አብይ አህመድ መዋቀራዊ ቅንጅት የሚካሄደውን የጥፋት ስፋትና ጥልቀት የተገንዘቡ፣ ነገር ግን መውጫ መንገዱ ርቋቸው በሀዘን፣ በጸሎት፣ ታጋዮችን በህቡዕ በማበረታት ወይንም ደንዝዘው ገዕዛን እንደሌለው ያበደ ሰው እየቆዘሙ የሚኖሩ ናቸው።
ጥፋትን በፍጥነት ለማስቆም ከተፈለገ፦
1) የመጀመሪያው ብቻ ሳይሆን ከህልውናና ፍትሕ የትጥቅ ትግል ጎን ለጎን የትግራይ ወጣትና ሕዝብ ከሕውሃት ስሑት ፖልቲካዊ ርእዮት፣ የሐሰት ትርክት፤ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን በመካድ ኢትዮጵያን የማጥፋት የውጭ አጀንዳ አግልጋይነት ሆኖ 50 ዓመታት ከመዋተት መላቀቅ፤ ሌሎች ጎረቤቶቹን በጠላትነት ከመመለከት፣ ግዛት ለማስፋፋት ከምቋመጥ፣ ከቅሚያና ግድያን እንደ ዓላማ ከሚያደርግ የአእምሮ ባርነት ነጻ መውጣት፤ እውነትን፣ ክብረ-ሀገርን፣ ፍትሕን፣ ክብረ-ሰብእን፣ መዋሀድን፣ ከአንድ ስሁት የዘር ፓርቲ ባርነት ወደ ሰዋዊና ኢትዮጵያዊ ላዕልና መመለስ እንዲችሉ የተዘፈቁበት የሕውሃት ትርክትና አስተሳሰብ ባርነት እንዲላቀቁ በሁሉ መንገድ መርዳት። የሰው ወይንም የብሔር ጠላት ሳይሆን የአስተሳስብና የርእዮት ጥመት የመክራው ምንጭ እንደሆነ እንዲረዳ መርዳት።
(2) የኦነግ-ኦሮሙማ፣ የኦሮ-ዉሀብያ፣ የናዚ-ፕሮተስታንትና የአስተባባሪያቸው የብልጽግና መንግሥትን ከሐውሃትና ኦነግ የተወርሰ ስሑት ፖልቲካዊ ርእዮት፣ የሐሰት ትርክት፣ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን መካድ፣ ሌሎች ጎረቤቶቹን በጠላትነት ከመምለከት፣ ግዛት ለማስፋፋት ቅሚያና ግድያን እንደ ዓላማ ከሚያደርግ የአእምሮ ባርነት ነጻ መውጣት። በ50 ዓመታት የኦነግ ትርክት፣ ከጀርባው ተሳፍሮ ደም የሚያፍሰውን ዉህቢዝምና ናዚያዊ-ፕሮቴስታንታዊ ክርስትና፣ መጽሐፍ ቅዱስ ሳይቀር ኤዲት የሚያደርገው ጸረ-ሴመቲኩን የኦነግ ፕሮቴስታንታዊ ክንፍ ስይጣናዊ ግብ በመረዳት ወደ እውነት፣ ክብረ-ሰብእ፣ ክብረ-ሀገር፣ ከናዚያዊ የዝረኝነት እይታና ድርጊት ወደ መዋሀድና አንድነት ማሰብ እንዲችሉ መርዳት።
(3) ሁልቱም የሕውሃትና የኦነግ መንፈስ ባሮች የሆኑ የየጎሣዎቹ ወጣቶች ከክልል አስተሳሰብ ወደ ሀገራዊ፣ ከጎሣ ትርክት ወደ ኢትዮጵያዊ ትርክት፣ ከሕወሃትና ኦርነጋዊ አስተሳሰብ አምልኮ ወድ ክርስትናና እስልምና፣ ከቅሚያና የመስፋፋት ዝንባሌ የሁላችንን አገርን ወደማጠናከር፣ ወደ በመወሐድና እኩል በጋራ ባለቤት የምንሆንባትን ሀገር ከዘርኛ ፖልቲካ ነጻ ወደ ማውጣት
ርእዮት መለወጥ።
(4) የሃይማኖት መሪዎች ነን ብለው ቦታው በምያዝ ለዘር ፖልቲካ የሚያገለግሉ ሙሰኛ አባቶችን፣ መምህራንን ከየቤተ እምነቶቻችን ማጽዳት።
(5) ግድ ሆኖበት ራሱን ከታወጀበት የ50 ዓመታት የዘር ማጥፋት ሂደት ለማዳን የተነሳውን የአማራ ሕዝብ የህልውናና የፍትሕ፣ የስባዊነትና የእውነት ተጋድሎ በሚቻል ሁሉ መደግፍ፡፡
(6) ከወዲሁ ምን አይነት ሰላማዊ፣ ከዘረኝነት የጸዳች፣ ሰብአዊ ክብር የገነነባት፤ ዜጎች በቦታና በቋንቋ፣ በእምነት የማይቧደኑባት የእኩልነት ምድር ለመሥራት የሚያስችል ሀገር-በቀል ፖልቲካዊ ርእዮት፣ አሰባሳቢ ሀገራዊ ትርክት፣ ከብረ-ሰብእና ፍትህ የሚነግሥበት የአስትዳደር ሥርዓትና መንግሥታዊ መዋቅር እንደምናበጅ መወያየት መጀመር።
ሌላ መፍትሔ ሰጭና ነጻ አውጭ መጠበቅ የባርነት ስነ-ለቦና ሰለባ ለሆኑ ሰዎች ብቻ የሚስማማ በሽታ ነው። ሁሉ ድርሻውን የወጣ!!
አስተያየቶች