ወደ ዋና ይዘት ዘለው ይሂዱ

ልጥፎች

ናርሲሲስት መሪዎችን የሚከተል ታጋይ ደሙ ደመከልብ መስዋዕትነቱ ከንቱ ይሆናል! ለራስህ ዋጋ ስጥ!

#የናርሲሲስት የስብእና ቀውስ ያለባቸው ሰዎች የግድ-መሪዎች ለመሆንንበሚዋደቁበት አውድ ሁሉ የብዙኃን #የመስዋእትነት ዋጋ ይረክሳል፣ #ከዓላማ ውጭ ይባክናል፣ #የቁማርተኞች የግል መጠቀሚያንይሆናል። እና እንንቃ!!! የተማሪዎች ንቅናቄና መስዋእትነት በደርግ እና የውጭ ጠላት አጀንዳ ተሸካሚዎች በእነ ሻዕብያ፣ በሕወሃት በኦነግ ዋጋ አጣ፣ ኢሕአዴግን ለመጣል የተከፈለው መስዋእትነት በኦነጋዊ ኦሮሙማ የብልጽግና መንግሥት ረከሰ፣ --- አሁንም #የአማራ ህዝብ የህልውና ትግል የሚከፈልለትን ከፍተኛ ሁለገብ መስዋእትነት በውስጡ በበቀሉ ባንምዳዎች፣ ጎጠኞች፣ ናርሲሲስትና ተላላኪ እጅግ ጥቂት የፋኖ #መሪዎች እንዳይረክስ መጠበቅ የወቅቱ አንገብጋቢ ትኩረት መሆን ወለበት። ስለ ናርሲሲስቶች ወደገኛ ጠባይ ለዝርዝር ትንተና እንዚህንንቪዲዮዎች ይመልከቱ https://youtube.com/playlist?list=PLauOEW1Em0lKWjJqKDTjVZzJ0yeA3FqpN&si=rUDEQF07CcxRi7Um ታሪክብእንደሚያስተምረን በማንኛውም የወል ተሳትፎ በሚጠይቅ ትልቅ የህዝብ ትግል ውስጥ አንድነት አደጋ ላይ የሚወድቅባቸው ውስጣዊና ውጭአዊ ምክንያቶች አሉ። ከሁሉ በላይ ግን የአንድነት ጠላት ናርሲሲስት የስነ ልቦና ("ማን አኽሎኝ፣ እኔ ብቻ፣ ልዩ ፍጡር ነኝ፣ ሁሉ ክብር ይገባኛል፣ አተኬ ነኝ " የሚያሰኝ ስነ ልቦንና) ቀውስ ያለባቸው ሰዎች ያለንሀፍረት ተነስተው ---- " #ሥልጣን ፣ #መምራት ፣ ከሁሉ በላይ የግድ የሚገባው 'ለእኔ' ብቻ እና ብቻ ነው" በሚል ግብዝነት ሲነሱ፤ ይህንንም ለማስፈጸም የሚችሉትን ማንኛውንም ሤራ ሁሉ ስለሚጎነጉኑና ሌሎች የተሻሉ ጸጋዎች ያሏቸውን ጓዶቻቸውን በማወክ፣ በማጥፋትና በ...

በኢትዮጵያ ለሚፈጸመው የዘር ማጥፋት ሂድተ በሕግ መጠየቅ የሚገባቸው አካላት

በኢትዮጵያ ሲካሄድ በነበረውና እየተካሄደ በሚገኘው ፖለቲካዊ፣ ሃይማኖታዊ ፣ ዘውጋዊ #የዘ *ር ማጥፋት ሂድት ለፍትሕ አደባባይ ቀርበው መጠየቅ የሚገባቸው አካላት ላይ ከወዲሁ በመወያየትና አቋም በመያዝ ለወደፊቱ ያዘጋጁትን የክፋ ጥቃት መከላከል ይቻላል። ዘር አጥፊዎች በብዙኃን ጥላ ሥር የሚደበቁ ጥቂት አካላት በመሆናቸው ከጎሬአቸው አውጥተን ካጋለጥናቸው ሕዝብን እያታለሉ እርስ በርስ በማፋጀት ከደሙ ንጹሕ ነን ሊሉ አይችሉም. በመሆኑም እንደ እኔ ግምገማ የሚከተሉት በቀጥታ በመፈጸምና ሌሎች በተዘዋዋሪ በመተባበር ውይንን ተጽእኖ የማሳደር #ሃይማኖታዊ ፣ #ባህላዊ ፣ #ምሁራዊና #ዲፕሎማሳዊ አቅም እያላቸው በዝምታ በመተባበራቸው የወንጀሉ ተካፋዮች ናቸው ብዬ አምናለሁ። በዚህ ብያኔ መሠረት የሚከተሉትን ዘርዝሬዝለሁ። አናንተ ጨምሩበት ፦ የኢትዮጵያ እና የዓለም ሕዝብ ይወቀው!! በኢትዮጵያ ውስጥ አሁን ለሚካሄደው፣ ምናልባትም ውደፊት ሊፈጠር ለሚችለው የሕዝብ መተላለቅ ተጠያቂዎቹ የሚከተሉት ኃይሎች በብቸኝነት እና በቅደም ተከተል ይሆናል፦ ፩) አብይ አህመድ አሊ እና አማካሪዎቹ ፪) የሕወሃት መሥራቾችና እስከ መጨረሻው በአመራር፣ በትርክት ፈጠራና በወታደራዊ አመራር የሚገኙ ፫) የኦነግ መሥራቾችና እስከ መጨረሻው በአመራር፣ በትርክት ፈጠራና በወታደራዊ አመራር የሚገኙ ፬) የኦፒዲኦ ምሥራቾችና እስከ መጨረሻው በአመራር፣ በትርክት ፈጠራና በወታደራዊ አመራር የሚገኙ ፭) የኢሕአዴግ አባልና አጋር ፓርቲ አመራሮች ፮) የዉሀብያ ጽንፈኛ ዑስታዞች፣ የጥላቻ ትርክት አምራችና አከፋፋዮች ፯) የሕዝብን እልቂት በዝምታ ያስቀጠሉ ጳጳሳትና የመጅሊስ መሪዎች ፰) ዓለም ዐቀፍ ተሰሚነት ያላቸው በእልቁቱ ተቃውሞ ባለማሰማት የተባበሩ ኢትዮጵያውያን ምሁራን እና የኪነ ጥበብ ሰዎች፣ ጋ...

አጥፊዎቻችንና ቤታችን ውስጥ የሚኖሩ ረዳቶቻቸው

የውጭ #አጥፊ *ዎቻችንና ቤታችን ውስጥ የሚኖሩ ረዳቶቻቸው በአገራችን የሚካሄደው መንግሥታዊ የሃይማኖትና የቋንቋ ዘውግን የተከተለ ሁለገብ ዘ*ር የማጥፋት ተግባር አቅም ያገኘው በሚከትሉት አካላት ነው፡- 1) ኃላፊነት የጎደላቸው፣ ፈሪሃ እግዚአብሔር የተለያቸው የእምነት፣ የባህል፣ የምሁርነት ከፍታ እና ተሰሚነት እያላቸው እረኝነታቸውን ለግል ጥቅማቸው ባዋሉ አድርባዮች ምክንያት አጥፊው በረታ፣ ጠፊው ተበታትኖና ፈዝዞ እስኪጠፋ ጥቃት ሥር ይቀጥላል፤ 2) ክርስቲያን #ጨውና #ብርሃን የመሆን ግዴታ ያለበት የሰማዕትነት እና በምሥጢራት በኩል ክርስቶስን የመምሰል ሕይወት መሆኑ በመዘንጋት፤ በሰንበትና በበዓላት ከሥራ ድካም ማረፊያ መዝናኛ ወይንም ቴራፒ እንደሆነ የምንቆጥር፣ እንደ ቃየል "እኔ የወንድሜ ጠባቂ ነኝን" በሚል ትዕቢትና በኃጢአት የመጽናት መንፈስ ተጸናወትን እኛ ነጭ ለብሰን የወገኖቻችን መከራ መካከል እና በደማቸው ላይ ቆመን ምንም እንዳልተፈጠር የምንዘምር፣ ከንስሐ በመራቅ ለሰማእትነት ጀርባችንን የሰጠን አድርባይ ምእመናን መብዛታችን ለአጥፊዎች እንደ ልባቸው እንዲጋልቡ እድል ሰጠናቸው፤ 3) በአዘናጊና አደንዛዥ አባቶች፣ ሰባኪያን፣ የመንፈሳዊ አገልግሎት ጸጋቸውን ወደ ገቢ ምንጭነት የቀይሩ አገልጋዮች፣ --- አዘናጊነት --- ብዙኃን ሳለን አናሳ፣ እውነትኞችና ታሪካውያን ሳለን የምንነወር፣ አገር ሠርተን ከአጥፎዎቻችን የአምልኮ መፈጸሚያ ቦታ የምንለምን፣ ሕግን ለዓለም ሰጥተን ያለ ሕግ በየዕለቱ የምንገደል ሆነናል። #መፍተሔ -መነሻ ሀሳብ የቤተ ክርስቲያንና የአገርን #ትንሳኤ የሚሻ ሁሉ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድና እንደ አቅሙ ከቀላል ወደ ከባድ የሚያድግ አገልግሎት መጀመር፦ 1) ክርስቲያናዊ ኃላፊነታችን ደምቆ እንዲ...
ፋኖነት ለሰብአዊ ክብር የሚከፍሉት ሰማዕትነት እንጂ የሚገዙትና የሚሸጡት የቅጥረኝነት አገልግሎት አይደለም! ማስታወሻ ይህ ጽሑፍ ልክ የዛሬ ሁለት ዓመት ጥቅምት 4 ቅን ነበር fanovoic.org ላይ ተለጥፎ የነበረው። እስቲ ዛሬ የገጠመውን ውጣውረድና የፋኖን እምርታ እያገናዘባችሁ ምን ያህል አርቆ አስተዋይ ዜጎች አዘጋጅተው እንቅፋት ለመቀነስ ምልክት እንደሰጡ ገምግሙ  ፋኖነት ለክብረ-ሰብእ፥ ለበዓለ-አገርነት፥ ለፍትሕና ለእውነት የሚሰጥ ክቡር ሕዝባዊ ሰማዕትነት መሆኑን ወዳጅም ጠላትም ይወቅልን   ፫/፪/፳፻፲፮ ዓ/ም  የአገር ቤቱ ነባር ታሪክ፥ ሥነ ልቦና፥ እምነትና ትውፊት፥ ታሪክና የአገርና የሰብአዊነት ትርጉም የተለወጠብን እኛ የዘመኑ ምሁራን የፋኖን ትግል የምንረዳበት መንገድ፥ የምንደግፍበት ምክንያት፥ ተስፋ የምናደርገው ውጤት በጥንቃቄ መጤን ይኖርበታል።   ከአገራችን ነባር እሤቶች፥ እምነቶችና ረቂቅ የአገርና የሰውነት ትርጉም የራቅን ብዙዎች ነን። ሁላችንም አገራችንን እንወዳለን እንላለን። ይህ መውደድ በድምጽ ሲነገርና በጆሮ ሲሰማ አንድ ቢሆንም በልቦና ሲያድርና በተግባር ልንገልጠው ስንሞክር ተለያይቶ እናገኘዋለን።   ከ1960ዎቹ አብዮተኛ ትውልድ (በነባርነት ላይ ያመፀ ትውልድ) ዘመን ወዲህ በቃላትና በመዝገበ ቃላት አንድ ብንሆንም በልብ፥ በርእይ፥ በአገርና በሰው ትርጉም ላይ አያሌ ልዩነት ፈጥረናል። በዚህ ልዩነት ምክንያት የአማራን ሕዝብ የህልውና ተጋድሎ በተግባር ራሱን ከሚገልጠው በተለየ መንገድ ቅርብን ሆነ ሩቅ ያሉ ተመልካቾች የተለያዩ ግምቶችና መረዳቶችን ይዘው መቸገራቸውን እየተመለከትን ነው።  በተለይ በከተማና በውጭ ሆነን ትግሉን በቀናነት ለመደገፍ የምንሞክር፥ እን...

የቤተንክህነቱ ሚዲያ ለማን ይቆማል?

የቤተ ክርስቱያን ሚዲያዎች የማንን ተልእኮ እያራመዱ ነው?? ‼️ #ለመከላከል ያይደለ ለመስተካከል ማድላት ትህትናና የንስሐ ልብ ላላቸው ነው። በተቃራኒው መቆም የአጥፉነትና የጥፊነት የአምባገነን ፖለቲከኞች ጌጅ ስነ ልቡና ነው።   ለቤተ ክርስቲያን የመረጃና ትምህርት ማሰራጫ ሚዲያዎች ወቀሳ አለኝ። ያሚጠቅም የቤተሰብ ውፕቀሳ ነው። በከንቱ በአድርባይነት እየተውፕዳደሱናንባዶ ክብር እየተቀባበሉ ከመስጠም መራራውን እውነት እየትጋቱ በንስሐ ትንሳኤ በምህረት ክንፎች መብረር ይበልጣል።   ያኛው ለአሁኑ ሆድ መሙያ ለኋላው የዘላለም ሞት ነው‼️ እንደ ቤተ ክርስቲያን አካል አንድ ብልት ህመሟ ህመሜ ነውና ወቀሳዬ እነሆ፦ #"የቤተ ክርስቲያን" የሚል ቅፅል ቀጽላችሁ ነገር ግን ቤተክርስቱያንን ቤተክርስቲያን የሚያሰኟትን በክርስቶስ መሠርትነት ላይ ስለተገነቡ ግድግዳዌችና ስለተዘረጉ ጣሪያዎች #አይመለከትንም ማለታችሁን ልመስክርባችሁ። ‼️ "የቤተ ክርስቲያን" የተቀጸለበት ሁሉ ምእመናንና ካህናትንም የሚያካትት ከሆነ ሚዲያው እኛን እንጂ አጥፊዎቻችንን ማገልገል ማቆም አለበት ‼️   በክርስትናችን ትውልዳዊ ቀጣይነት አንጻር ወሳኝ በሆኑት ጉዳዮች ስትመዘኑ የማጽናት፣ የማሳደግና የማስፋት ያይደለ #በማጥፋት መንገድ ላይ #ቆማችሁ ትታያላችሁ ‼️   በእንፃሩ በዚህ ዘመን ለቤተክርስቲያን ህልውና እንቅፋት በመሆናቸው ምእመናን እንኳን ዐውቀውት በአንድ ልብ ሆነው ሊከላከሉት የሚገባቸውን አደጋ #እንዳያውቁ ታደርጋላችሁ።    አውቀው ለማሳወቅ የሚጥሩትን ለማፈን እንደ አምባገንን ፖለቱካዊ ሥርዓት በቃላትና በጥቅስ በሚጀምር ነገር ግን ጥቅሱን በሚቃረን ፕሮፓጋንዳ ልትዋጉ ርሞክራላችሁ። #ጠላትን...
ናዚና ገዳ ጥቁርና ነጭ እንዴት ተመሳሰlu? እውነት ካልተነጋገርን እንጠፋለን! በተላላኪነት ኢትዮጵያ ላይ እንደ መቅሰፍት ከተጫኑ የጨለማ ዘመን መግቢያ መክፈቻ የሆነው በወያኔና ኦነግ የጋራ ፕሮጄክት ኢትዮጵያን ለማፍረስ ከተመረጡ ዘርፈ ብዙ ስልቶች መካከል አገራዊ የጋራ ትርክቶቿን መደምሰስ ዋንኛው ነው። በዚህ ዘርፍ ሕዝቡን በጎሣዎ፣ በእምነቶችና በባህሎች ተገዳዳሪ ተርክትና ፖለቲካዊ እምነቶች የጋራ ሀገራዊ ተርክትን ማዳከም ዋናው ነው። አስተሣሣሪ ትርክቶችን፣ ብዝኃነት ያላቸው አሐዳዊ አገራዊ እሤቶችና ዕይታዎችን በማዳከም ሕብር ተበትኖ በተለያየ በንዑስ ማንነት ላይ የተመሠረተ አሠፋፈሮች ለመፍጠር መሠረት መጣል ነው። ቀጥሎም የአገራችንን ዜጎቿን መክፋፈልና ማፋጀት የሚያስችል ሁኔታ በመፍጠር ደርጃውን ጠብቆ ከትርክት ወደ ሕግ፣ ከሕግ ወድ ፖሊሲ፣ ታጣቂነት፣ ቀጥተኛ ሁለ-ገብ ጥቃትመፈጸም አሁን የማየው ነው። ከውጭ የአራችን ልዩ የነጻነት እሤቶች ምንጭ የሆኖ እምነቶች፣ ባህሎች፣ ማኅበራዊ ሥሪትን ዒላማ ካደርጉት የውጭ ወራሪዎች ትምህርት፣ ምክርና ተላላኪነት ተቀብለው ከሚሠሩ የሕወሃትና የኦነግ እንዲሁም የሁለቱ የፖለቲካዊ ርእዮቶች ለዚህ ጥፋት የተመረጡ ባህሎችና እምነቶች መካከል የኦሮሞ ባህላዊ እመነት፣ የዉህብያ ጽንፈኛ ኢስላም፣ የጀርመን ናዚ ትራፊ በሆነውና ኦነግንን በወለደው በግንቢ ሆስፒታል ውስጥ የተዘራው ፕሮቴስታንት ሲሆን የሁሉም ዒላማቸው የማንኛዉም ጎሣ አባልና ቋንቋ ተናጋሪዎች የሆኑ ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ተከታይ ማኅበረሰቦች እና አማራ እንደ ብሔር ተፈርጆ በመለየት ናቸው። ኦሮሙማ የተባለው ፖለቲካ ሠራሽ አዲስ እምነትና የአምልኮ ሥራዓታት ከእስልምናና ክርስትና ሁሉ በላይ የሆነ ረእዮት ሆኖ ቀርቧል። ርእዮቱ ወደ ተ...

ፋኖነትና ሐሰተኝነት አብረው አይሄዱምና ሐሰተኞች መጠሪያ ቀይሩ

#ፋኖነትን ከሽፍጠኝነትና ከሤራ ጋር ማን አጋባው? የዚህ በሽታ ተጠቂዎች በአመራር፣ በማኅበራዊ ሚዲያ፣ በማካሪነት እንዴት ተሰለፉ? ማንስ ላካቸው? ---- የታጋዮች መስዋዕትነትን ከሚያረክሱ ተላላኪዎች ትግሉን ጠብቁ!በጭፍን ተከታይነትና በጎጠኝነት፣ በምላስ መውለብለብ አትታለሉ!!! ፋኖነትን ወድ ተራ ሽፍትነት የሚያወርዱ አእምሮዎች ከጎንደር መብቀላቸው አማራም፣ ኢትዮጵያም ገና ብዙ መከራ እንደሚጠብቃቸው ይጠቁማል። ራሱን ደብቆ #Amanuel Z Gonder እያለ ቆሻሻውን ዕውቀትና መርጃ አስመስሎ እንዲያቀርብ ቡድን የተደራጀለትን አንድ ድውይ ሰው መንሻ አድርጌ መናገር ፈለጉሁ። ይህን እና መሳዩን ሰውና የኼ ነው የብሻሌ ራሱን የሚባሉ ሰዎችን ኑና በአደባባይ ሕዝብ እየሰማን እንከራክር ብላቸው አሻፈረኝ ብለው በሥርቻ ውስጥ ተወሽቀው የአማራን ሕዝብ የህልውና ትግል ብቻ ሳይሆን መሠረታዊ የእውነተኝነት፣ የሰባዊ ክብር፣ የካህንና የእምነት አባቶችን ማክበር፣ ወንድማማቾች መካክለ ጥል አለመዝራት፣ ዋሽቶ ማስታርቅ እንጂ ሐሰት አምርቶ አለማጋጨት የመሳሰሉትን ሁሉ የሚጎዱ መልእክቶችን በጭፍን ለሚከተላቸው፣ ከማገናዝብ ይልቅ ማዳነቅ ብቻ ለለመደው የኳስ ተመልካች ዘመን መንጋ ይመግቡታል። ምግቡ የመረዛቸው እንደ እቃ እየታዘዙ ከትግሉ ዓላማ በተቃራቂ እርስብርስ ይጠፋፋሉ። የአማራን ሕዝብ የህልውና አደጋ ላይ የጣለው የኼው #ሕወሃትና #ኦነግ በኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ተላላኪነት ሲደርሱትና ሲረጩት የኖሩት የሐሰት ትርክት፣ ቁማርተኝነትና ሕዝብን አሳስቶ የማፋጀት አባዜ ነው። #አማኗኤል ዘ ጎንደርና መሳዮቹ የዚሁ እንዋጋዋለን የሚሉት ቡድን ቀጥትኛ ነጸብራቅ ናቸው። በፋኖ መካከል #ፋኖነትን ወደ #ሽፍትነት የሚዘቅጥ መንገድ በመያዝ የትግል መነ...