ተገፊዎች ግፍን ይቅርታ ጠየቋት በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ። አሜን። 17/11/2015 የኢትዮጵያ ክርስቲያኖች ክርስቶስን ዘንግተው በፖለቲካ ፕሮፓጋንዳ በተፈጠረ ቡድንና የቋንቋ ዘውግ ዘረኝነት ተከፋፍለው የየሰፈራቸው ጣዖት ፈጥረዋል። ይህን የሸክላ፥ የብረት፥ የመዳብ፥ የወርቅና የብር ጣዒት አይደለም። ዘመናዊው ጣዖት የተፈጠረው ከተረፈ ማርክሲዝም፥ ከተረፈ ናዚ የተወለደው ዘረኝነት እምነቶችና በኦነግና በሕወሐት ፈጻሚነት፥ በኢትዮጵያዊነትና ኦርቶዶክሳዊነት ላይ ለ700 ዓመታት የተሰለፉ ታሪካዊ ጠላቶች አስፈጻሚነት የተመሠረተው የጎሣ ሕገ መንግሥት ነው። ይህ ሕገ መንግሥት መግቢያው ብሔር ብሔረሰብና ሕዝብ የሚል ርዕስ አለው፤ ዝርዝሩ አማራና ኦርቶዶክስን መስበር ነው። ግቡና የመጨረሻው የብሔርተኞች መንግሥተ ሰማይ በምድር ማስገኘት ነው፥ እርሱም ከኦርቶዶክስና ከአማራ ነፃ የሆነ ፓጋን ትግራይ፥ ፓጋን ኦሮሚያ ወይንም ፓጋን ኢትዮጵያን መፍጠር ነው፤ በዚህ አዲስ የዘረኞች “ሃይማኖት” ዶግማው ትግራዋይነት (ሕወሐትነት) እና ኦሮሙማ ከነባር እምነቶችና ባህሎች ሁሉ በላይ ነው፥ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት፥ ኦርቶዶክሳዊነት እና ኦርቶዶክስ የሁለቱ አዳዲስ እምነቶች ጠላቶች ናቸው። የአዳዲሶቹ “ሃይማኖቶች” የአምልኮ አፈጻጸም የሐሰት ትርክት፥ ስም ማጥፋት፥ ማፈናቀል፥ መግደል፥ ማደኸየት፥ ማምከን፥ ማሰደድ፥ ጦርነቶችን ጭሮ መፍጀት፥ ከእምነት ማስወጣት፥ በቁጥር ማሳነስ (ዲሞግራፊ መቀነስ)፥ ከውጭ ታሪካዊ ጠላቶች ጋር መሰለፍና በዓለም አቀፍ ደረጃ ኦርቶዶክሳዊነትን፥ ኢትዮጵያዊነትንና አማራን መክሰስ ናቸው። የሕወሓትና የኦነግ/ኦሮሙማ/ ብልጽግና ማንነት የሚገለፀው በታሪ...
This is a spot where I post and share part of my daily reality. I would love to hear from others too to learn how differently we interpret daily encounters including our imaginations. ይህ ሥፍራ የየዕለት ገጠመኞቼን፣ እንዴት በዕለቱ እንተረደሁትና የማስበውን ለሌሎች ያማጋራበት ነው፡፡ የሌሎችን በመስማትና ምን ያህል ዓለማችንን በተለያየ መንገድ እንደምንመለከታት ለመማር እጓጓለሁ፡፡