ወደ ዋና ይዘት ዘለው ይሂዱ

ታሞ ከመማቀቅ አስቀድሞ መጠንቀቅ የሚለው የሀገሬ ብሂል የወ/ሮ መዓዛን የኤል ቲቪ ቃለመጠየቅ ተከትሎ ተመላለሰብኝ



ታሞ ከመማቀቅ አስቀድሞ መጠንቀቅ የሚለው የሀገሬ ብሂል  የወ/ሮ መዓዛን የኤል ቲቪ ቃለመጠየቅ ተከትሎ ተመላለሰብኝ፡፡ እንዲሁም የቤተክርስቲያን እና ኢትጵያዊ ምነነትን  በሁሉመ ዘርፍ የመድፈር ሂደት ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱ ታየኝ፡፡ አንዴ በማርክሲዝም፣ ሌላ ጊዜ በፌሚኒዝም፣ ሌላ ጊዜ በካፒታሊዝም፣ ሌላ ጊዜ በተሐድሶ፣ አንዴ …. በስንቱ እንደፈራለን!!!  ይህ ሁለንተናዊ ድፍረት አሳሰበኝ -- እናንተስ?
----የሚያሳስባችሁ ሁሉ የዚህ መፍትሔው የክርስቲያኖች ከጥልቅ እንቅልፍ መንቃት ነውና !!!!  ነቅተን በትምህረትና በእውቀት ልዕልና፣ በህግ፣ በጸሎት፣ወዘተ መከላከል መጀመር ነው፡፡ ጊዜ የለንም፡፡
ይህ ካልሆነ ባዕድ አምልኮ፣ ሰዶማዊነት፣ የሰው ልጅ አካል እየበለቱ ለመለዋወጫ መጠቀም፣ አሁን በኢትዮጵየ የተፈቀደው ውረጃ ሰውን መብት ነው እያሉ ራሱን አንዲገድል መፍቀድ፣ ወዘተ ተማርን፣ ሠለለጠንን በሚሉ የሀገራችን ልጆች ጀርባ ተጭኖ  ከምዕራባዊያን  የሚፈሰው የርኩሰት ጎርፍ  ነገ አስገዳጅ ሐገራዊ ሕግ ሆኖ ይቀርብልናል፡፡ 
ቅድስት ቤተክርስቲያናችን የተደፈረችባቸው ዘርፎች፡ እና የሁላችንንም ጥረትና ተሳትፎ የሚጠይቁ ጉዳዮችን ከማንሳቴ አስቀድሞ በዚህ መልዕክቴ ቤተክርስቲያን ብዬ የምጠራው፡
----  ክርስቲያን ግለሰብ ሰው፣
---- የክርስቲያኖች ስብስብ፣
---ክርስቲያናዊ እምነት ያመነጫቸውና ክርስትና የሚገለጥባቸው  የግልና የማኅበራዊ ኑሮ ዘይቤዎች ማጠበቂያ ማኅበራዊ አደረጃጀት
--- ክርስቲያኖች አምልኮ የሚፈጽሙባቸው ቦታዎችና ለአገልግሎት ተለይተው የሚሠሩ ቁሳቁሶች፤
---የክርስቲያኖች መልዕክት የሚለዋወጡባቸውና አምልኮአቸውን ለመግለጽ የሚገለገሉባ ምልክቶች (symbols)፣ መንፈሳዊ ይዘትና ትርጉም ተሰጥቷቸው የኪነጥበብ ውጤቶች፣
----የክርስትና የተቀደሰ ተውፊትና ታሪክ ትርክት፣ የክርስቲያኖች አስተዳደራዊና አመራር ፍልስፍናዎች፣ የክርስትና ዶግማዊ አስተምህሮዎች፣  
---የክርስቲያኖች የክህነት ተዋረዳዊ ደረጃዎችና ቅብብሎሽ፣ ሲኖዶስ፣ የክርሰቲያን ትዳርና ልጅ አስተዳደግ ሥርአትና አስተምህሮ ወይንም ዳኝነት ሁሉ በሙሉ በአንድነት ተጠቃሎና ተተርጉሞ ሲታይ ነው፡፡ 
በዚህ ትርጉም መሠረት ቤተክርስቲያናችን የተደፈርባቸው (በስንፍናችን ያስደፈረናቸው) ዘርፎች፡-
(1)-- ክርስቲያን ግለሰብ ሰው ተለይቶ በስለት የመንግሥጥ ሠልጣን በያዙ መዋቅራት ንብረቱን ይነጠቃል፣ ሕይወቱንም ያጣል (ጅጅጋ፣ በሻሻን ያስታውሷል)
(2)--- የከርስቲያኖች ስብስብ ወይንም ማኅበር ሥልጣን ባላቸው ወይንም የራሳቸው ሌላ ስብስብ ባበጁ አካላት ያለ ፍርድ ቤት ብያኔ፣ ያለአንዳች ማስረጃ በአክራሪነት፣ በአትፊነት ይፈረጃል (በሀገሪቱ አንዳንድ ባለሥልጣናትና መሥሪያቤቶች የተሞከረውን የማኅበረቅዱሳን ፍረጃ ያስታውሷል)
(3)--- ክርስቲያናዊ እምነት ያመነጫቸውና ክርስትና የሚገለጥባቸው  የግልና የማኅበራዊ ኑሮ ዘይቤዎች ማጠበቂያ ማኅበራዊ አደረጃጀቶ በፈቀዱት መንገድ ራሳቸውን እንዳይመሩ ጫና ደረግባቸዋል (በኢትዮጵያ ዩኖቨርሲቲዎች የሚማሩ የኦርቶዶስ ወጣቶች እምነታቸው የሚፈቅደውን ልብስ (ነጠላ እነዳይለብሱ)፤ የከፈሉበትን የቁርስ ምግብ በጾም ወቅት አውጥተው እንዳይመፀውቱና ለማኅበራዊ አገልግሎት ወደ ገንዘብ ለውጠው እዳያውሉ በተቋማቱ አስተዳደር ክልክላ ደረግባቸዋል)
(4)---ክርስቲያኖች አምልኮ የሚፈጽሙባቸው ቦታዎችና ለአገልግሎት ተለይተው የሚሠሩ ቁሳቁሶች የእምነቱ አባላት ባልሆኑ ኢአማኒያን፣ ዘፋኞች፣ መናፍቃን መጫወቻ ሲሆኑ ምንም አይነት የሕግ ጠበቃ አያገኙም፤ ለዚህ አይነት ጥፋት እርምት የሚደረግበት መድረክ በሀገሪቷ አልተዘጋጀም
(5) ---የክርስቲያኖች መልዕክት የሚለዋወጡባቸውና አምልኮአቸውን ለመግለጽ የሚገለገሉባ ምልክቶች (symbols)፣ መንፈሳዊ ይዘትና ትርጉም ተሰጥቷቸው የኪነጥበብ ውጤቶችን ከዓላማቸው ውጭ በሌሎች አገልግሎት ላይ ሲውል ለማረም የሚዪስችል ምንም አይነት የመንግሥት፣ የማኅበረሰብና የቤተክህነት መዋቅር ተዘጋጅቶ አይሠራም፡፡
(6)---የክርስትና የተቀደሰ ተውፊትና ታሪክ ትርክትን በፖለቲካ ርዕዮተ ዓለም በመመራት፣ በአካባቢየዊ የፖለቲካ ትግል አሸናፊ ለመሆን ያለ ጥናትና ማረጃ በሀሰት ሲበላሽ፣ አፈራሽ በሆነ መንገድ ሲተረክ ማስረጃ እያመጣ የሚሞግት አካል ኤታይም፤ ወደ ሕግ የሚቀርበውን አጥንቶ የሚቂርብ የለም፡፡
(7)--- የክርስቲያኖች አስተዳደራዊና አመራር ፍልስፍናዎች፣ የክርስትና ዶግማዊ አስተምህሮዎችን በመቃረን ሀገራዊና ማኅበረሰባዊ ደንቦች ልዩ ፍስፍናና ፍላጎት ባላቸው አካላት መሪነት ሲሸረሸርና ሕግ ሆኖ በክርስቲያኖች ላይ ሲጫን እየተከታተል እያጠና በአውቀትና በህግ የሚሞግት አካል የለም፡፡
(8)---የክርስቲያኖች የክህነት ተዋረዳዊ ደረጃዎችና ቅብብሎሽ፣ ሲኖዶስ ልዩ ዓማ ባለቸውና እምነቱን ከውስጥ ለመሸርሸር በተሰለፉ ግለሰቦችና ቡድኖች ክብሩ ሲደፈር፣ አርያነቱ ሲጎድፍ የመከላከልና የማረም ሂደቱ እጅግ ደካማና ዘገምተኛ ነው፡፡
(9)--- የማኅበረሰብና የእምነት መሠረት የሆነው የክርሰቲያን ትዳርና ልጅ አስተዳደግ ሥርአትና አስተምህሮ ወይንም ዳኝነት በመደበኛ ትምህርት ይዘትና በመገናኛ ብዙሀን ሲወቀስ፣ ሲዋረድና በምትኩ ኢአመናያን የሚከተሉት ዘይቤ በሕግ በክርስቲያኖች ላይ ሲጫን፤ የልጅ አስተዳደግና የትዳር አመራር ሙሉ በሙሉ ወጭ-ገብ ባዕድ ሲሆን የዚህን ሂደት ጥቅምና ጉዳት ተንትኖ ለመሞገት የሚያስች መድረክ በሀገሪቱ የለም፡፡
ስለዚህ ቤተክርስቲያን በሁሉም ዘርፎች ተደፍለች፡፡ ልጆቿ ሙቸውን፣ አውቀታቸውንና መላ አቅማቸውን ተጠቅመው ይህን መደፈር የሚየሰቆሙበት አገልግሎት መስጠት ይጠበቅባቸዋል፡፡  አንዲያው የኖረ ውበቷን በሴኩላር ቱሪሰት ዓይን እያዩ ማድነቅ፣ መዐዛ እጠኗን በበዓላት ብቅ ብሎ ማሽተት፣ ሰማያዊ ዜማዋን ምሢር ዘንግቶ በመዝናኛና ሙዚቃ ደረጃ ማጣጣም፣ ያከማቸቻቸዋን የታረክና የጥብብ ብራና እየገላበጡ በመቆንጠተር አርቲክል ጽፎ ድግሪ  መውሰድ፣ ወዘተ ብቻ ኤበቃም አያዋጣምም፡፡  ተግባር!!! ተግባር!!! ተሳትፎ!!! ተሳትፎ!!!

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ገድሎና አስገድሎ ብፁዕ እየተባሉ መኖር የተፈቀደላቸው ጳጳሳትና ቆሞሳት እንዳይረሱ

ከጥር 27 ጀምሮ በተለያዩ የኦሮምያ ከተሞች በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቀኖና ውጭ የተሾሞና በቅዱስ ሲኖዶስ ተወግዘው የተለዩ አካላትን ወደ ቤተ ክርስቲያን እናስገባለን ባሉ የመንግስት የጽጥታ አካላት በተትኮሰ ጥይትና ሕገ ወጡ ቡድን ባደራጃቸው ወጣቶች ተደብድበው የተገደሉና የቆሰሉ  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ካህናትና ምእመናን።።   1)  ሻሸመኔ ከተማ   I.   የተገደሉ 1.  አያሌው ተረፈ ●   በሻሸመኔ የደብረ አስቦ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ማህደረ ፃድቃን ሰንበት ትምህርት ቤት አባል ●  ጥር 27 ዓ/ም በሻሸመኔ ከተማ በጸጥታ ሃይሉ በሚመራ የጨፍጫፊ ቡድን በደረሰበት ከፍተኛ ደብደባ ወደ ሆስፒታል ገባ ●  በአላቲዮን ሆስፒታል ሕክምና እየተደረገለት ሕይወቱን ማትረፍ አልተቻለም ●  በ ጥር 30 2015 ዓ/ም  ሰማዕትነትን ተቀብሏል       2.  ሊቀ ኅሩያን ቀሲስ ሐረገወይን ●  የሻሸመኔ ደብረ ስብሐት ቅዱስ ሚካኤል አገልጋይ የነበሩት ●  በሻሸመኔ በሕገወጦች በጸጥታ አካላት  በበግፍ በዱላ ተቀጥቅጠው በጭንቅላታቸው በእጅና በእግራቸው ላይ በደረሰባቸው ድብደባ በሀዋሳ ሕክምና እያሉ አርፈዋል። ●  ከመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች በተተኮሰ ጥይት ተመትተው  በያኔት ሆስፒታል ሕክምና ሲደረግላቸው ቢቆዩም ሕይወታቸውን ማትረፍ አልተቻለም። ●  በዛሬው ዕለት ጥር 30 2015 ዓ/ም  ሰማዕትነትን ተቀብለዋል።     3.  ዘማሪ ፍቃዱ ደጉ ●  የቅዱስ ሚካኤል ከሣቴ ብርሃን ሰ/ትቤት አገል...

ኢትዮጵያ የተገዳደሯትን ሁሉ ቅኝ ገዥወች የተከላከለችባቸው፣ የተዋጋችባቸውና ነጽነቷን ያስከበረችባቸው እሴቶች; በቀሲስ አስተርአየ ጽጌ

የጽዋዕ ማህበራትና ሰንበቴ ከቅድስት ድንግል ማርያም ጋራ የተሳሰሩት የጽዋ ማሕበራትና ሰንበቴወች ናቸው፡፡  ኢትዮጵያ የተገዳደሯትን ሁሉ ቅኝ ገዥወች የተከላከለችባቸው፣ የተዋጋችባቸውና ነጽነቷን ያስከበረችባቸው እሴቶች  ቀሲስ አስተርአየ ጽጌ  nigatuasteraye@gmail.com  ሚያዚያ ፳፩ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም.  (April 28, 2025)  መግቢያ  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያናችን ኩለንታዊት ቀዳማዊት ደኀራዊት፡ ዘመናዊት ናት ስትባል እም ኀበ አልቦ አይደለም፡፡ በብዙ እሴቶቿ ነው፡፡ ኩለንታዊት ከምታደርጋት ከብዙ እሴቶቿ መካከል የጽሑፌ መነሻ የሆኑት ከቅድስት ድንግል  ማርያም ጋራ የተሳሰሩት የጽዋ ማሕበራትና ሰንበቴወች ናቸው፡፡ ስንበቴ በቀጥታ ከእግዚአብሔር የታዘዘች ናት፡፡ የጽዋ ማኅበርም እንደ ሰንበቴው ቀጥታ ከግዚአብሔር ባይሆንም፡ በዮቶር በኩል ለሙሴ የደረሰው የግዚአብሔር ምሪት ናት፡፡ የጽዋ ማሕበርና ሰንበቴ የትርጉማቸው መነሻ፡ መድረሻና የመጨረሻ ዋና ዓላማቸው ሰባዊ ክብርና ነጻነት ነው፡፡   ኢትዮጵያ የተፈታተኗትን ሁሉ ቅኝ ገዥወች ከተከላከለችባቸው ከተዋጋችባቸውና ነጽነቷን ካስከበረችባቸው ዋናወቹ እሴቶቿ ውስጥ የጽዋ ማሕበራትና ሰንበቴወች ናቸው፡፡ በቅኝ ገዥወች ሲቀጠቀጡ ከኖሩት ካጎራባች አገሮች ልዩና የነጻነት ምሳሌ ያደርጓትም የጽዋ ማህበርና ሰንበቴ ናቸው፡፡ የጽዋ ማኅበራትና የሰንበቴ ድርጅቶች እንዴት ተመሰረቱ? ለኢትዮጵያ ምን ጠቀሙ? ትሩፋታቸው ምንድነው? የደርግንና የወያኔን ዘመናት እንዴት ተሻገሩ? በብልጽግና ዘመንስ እንዴት ናቸው? እንዴት ይቀጥሉ ? የሚሉትን ጥያቄወች ለመመለስ ከጽዋ ማኅበር እንጀምር፡፡   የጽዋ ማኅበር መነሻ...

ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን እና ቋንቋና ማንነት ተኮር እንቅስቃሴዎች

  ኦ ርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን እና ቋንቋና ማንነት ተኮር እንቅስቃሴዎች   ፩ . ቋንቋን በተመለከተ ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮና ትውፊት ከሰው ልጅ መበደል በፊት ፍጥረት ሁሉ የሚግባባው በአንድ ቋንቋ ነበር፡፡ “ ምድርም ሁሉ በአንድ ቋንቋና በአንድ ንግግር ነበረች” እንዲል፡፡ ዘፍ. 11፡1 በኃጢአት ምክንያት ግን ሰውና መላው ፍጥረት በአንድ ቋንቋ መግባባታቸው ቀረ፡፡ ኃጢአት እየበዛ ሲሄድ የሰው ልጅ ቋንቋም በባቢሎን ተደበላለቀ፣ አንዳቸው ከሌላቸው ጋር የማይግባቡ ብዙ ዓይነት ቋንቋዎችም ተፈጠሩ፡፡ በበደል የመጣውን ሁሉ ሊያስተካክልና ሊያድን በመጣው በአምላካችንና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አዳኝነት ያ የቀደመው ጸጋ ስለ ተመለሰልን በበዐለ ሃምሳ ሰዎች በልዩ ልዩ ቋንቋ አንድ ዐይነት የእግዚአብሔርን መልእክት ሰሙ፡፡ በዚህ ጸጋ የተጠቀሙና የበቁ ቅዱሳን የእንስሳትን ቋንቋ እስከ ማወቅ ደረጃ ይደርሳሉ፡፡   የክርስትና ጉዞ ወደ ቀደመው በአንድ ቋንቋ መግባባት መመለስ ነው፡፡ ወደዚያ ለመድረስ ደግሞ ሰው የእግዚአብሔርን ቃል በሚሰማው ቋንቋ መማር አለበት፡፡ በበዐለ ሃምሳ ጊዜ ለቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስ ብዙ ቋንቋ የገለጠላቸው ሰውን ሁሉ የእግዚአብሔርን የማዳን ጸጋ በሚሰማው ቋንቋ እንዲያስተምሩት ነው፡፡ ሆኖም ቋንቋ መልእክት ማድረሻና መግባቢያ እንጂ ከዚያ ያለፈ ሰዎችን በሆነ መደብ ለመመደብና የልዩነት አጥር ለመሥራት እንደ መሳሪያ ሊሆን አይገባውም፡፡ ይህ ከክርስትና ዐላማ ጋር ተቃራኒ ነው፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያት ወደ ዐለም ሁሉ ሲልካቸው ሰዎች የሚቀበሏቸው በሚያስተምሩት ትምህርት መሠረት ነበር እንጂ በትውልድ፣ በብሔርና በመሳሰለው መስፈርት የእኛ ናቸው/አይደሉም በሚል አልነበረም፡፡ የቤተ ክርስቲያ...