ወደ ዋና ይዘት ዘለው ይሂዱ

ኢትዮጵያን እየመራችሁ ላላችሁና ወደፊት ለመምራት የምትፎካከሩ ሁሉ


ኢትዮጵያን እየመራችሁ ላላችሁና ወደፊት ለመምራት የምትፎካከሩ ሁሉ


በፖሊሲና በሀሳባችሁ ሁሉ ውስጥ የሚከተለውን ሀሳቤን ብታጤኑ ሀገራችንን ለዘለቁታዊነት የሚጠቅም ይመስለኛል፡-   
አፍሪካን በተፈጥሮ ሀብትና በርካሽ የሰው ኃይል ምንጭነት የሚፈልጉ ሀገራት ሁሉ የኢትዮጵያን መነሳት እጅግ ይፈራሉ፡፡ ስለዚህ ኢትዮጵያና እትዮጵያዊነት  የሚል አስተሳሰብና ለእኛ ለእትዮጵያን ቢሰወርብንም  ታሪካችንን ሲያጠኑ፣ ብራና መጽሐፎቻችንን ሲበረብሩ፣ በእምነት ፍልስፍናችንን የነበረንን ልዕልናና መንፈሳዊ ኩራት ያወቁ፣ መድኃኒት፣ አስትሮኖሚ፣ አስተዳደር፣ ኪነ ጥበብ እንደነበረን የደረሱበት ሁሉ ይሰጋሉ፡፡ ሥጋታቸው አሁን ያለው ትውልድ ወደራሱ ማንነት ማየት ከጀመረ፣ የተሰወረበትን የአባቶቹን ጓዳ ለመመርመር ፊቱን ከጭፍን ግልበጣ ወደ ተረጋጋ ተመራማሪነት ከመለሰ  እስካሁን የሚዘርፉትን ያስቆማል፤ በስደት እየፈሰሰ ጠላቶቹን ከማገልገል ይቆጠባል፤ ከጊዜአዊ ስሜታዊ እርካታ ይልቅ ለትውልድ ማብ ይጀምራ፤ የምዕራባዊያን ጭራና ተከታይነቱን ለውጦ በእኩልን የመኖ አቀም ያዳብራ፤ ሌሎች አፍሪካን በልጠውና ተከታይ አድርገው የመቀጠል እድላቸው ይፈተናል፤ የኢትዮጵያኖ መንፈስ ወደ ሁሉም አፍሪካ ተጋብቶ ራን ለመቻልና ለመተባበር ሀገራትን ያነቃቃል፤ በመሆኑም  ---- ፈጂና ጨፋሪ፣ ገልባጭና አቋራጭ ብልጽግና ፈላጊ ትውልድ ስለሚያጡ ምዕራባዊያን ራዕይህን ለማምከን ሁሉንም ወጥመድ ይዘረጉብሃል፡፡  ሥለዚህ ትልቅ አደጋ ላይ ትወድቃለህ፤ የአንተን ሀሳብ የሚደግፉ ሰዎች፣ ፍልስፍናዎችና እምነቶ ሁሉ አደጋ ላይ ናቸው፡፡ በመሆኑ ጥበብ የተሞላበት አካሄድ ያሻል፡፡ የሰፈራችንን ራ ወዳድ የሆድ ሌሎ ፖለቲከኞችን ለማሸነፍ ብለህ ከባድ፣ ሩቅ ዓላሚና ሌሎችን የሚስነሳብህ ስልታዊ ንግግሮች ከማድረግ አንድተቆጠብ እመክርሀለሁ፡፡
ለስንኩሎቹና ለአኩራፊዎች መድኀኒት መስጠት ከፈለጋችሁ  በአደባባይ በሕዝብና በሽማግሌ ፊት ለፊት ማወያየትና የሚመለሱት እንዲመለሱ፣ ተንኮለኞች ከሕዘብ እንዲነጠሉና ማንንም እዳያሳስቱ መድረኮችን መዘርጋ ያስፈልጋል፡፡

ፈጣንና ስልታዊ እርምጃዎች፡-
1.  አርኪዮሎጂ ቁፋሮና ምርምር ከባዕዳን ጣል ገብነት ነፃ ሆኖ ሁሉም በኢትዮጵያዊያን ብቻ እንዲካሄዱ ማድረግ

2.  የኬሚካል ማዳበሪያን   በመተካት የኤትዮጵያን አፈር በሌሎች ፈቃድና ድጋፍ የሚያበቅልና የሚነሳ አንደይሆን  ነጻ የማውጣት አስቸኳይ ስተራትጂ መዘርጋት


3.  መድኃኒቶች ከኢትዮጵያ ጥበብ ተመርተው አንዲተኩ በማድረግ ሀገሪቷን ከውጭ-ገብ መድኀኒት ቢያንስ ከ80 በመቶ በላይ መተካት፡፡ መተካት ባይቻል በስጠትና በመቀበል ደረጃ ከሌሎች ጋር የምንገዳደርበት ደረጃ ላይ አንድንገኝ የሚየስችሉ ምርምችን መጀመር፡፡ በኢትዮጵያ የኦርቶክስ ክፍርስትና፣ በሙስሌም፤ በጠረፋማ አካባቢ የሚኖሩ ማኅበረሰቦች ሰፊ የመድኀኒት አውቀቶች ምርምር አንዲጀምርባችቸው ማድረግ

4.  የእህልና የእንስሳት ዝርያ ሙሉ በሙሉ ኢትዮጵየዊያን ተመራማሪዎችና የገበሬ ባህል የዘር አቀማመጥና ማስተላለፍ ሥረዓት መመለስ፤ የጂን ባንክ ከውጭ አካላት ነጻ በማድረግ የትበቃና ማባዛት ቴክኖሎጂን ማሻሻል፡፡ በዚህ ዘርፍ ዓለም አቀፍ የሰው ልጆች ምግብን ቁጥጥር ሥር ለማዋል የሚሠሩ  ሀገራትና ካምፓኒዎች ድለላ የማያሸንፋቸው ምሁራንን መልምሎ  የቴክኖሎጂ ቀሰማ ስኮላርሺፕ መላክ፡፡

5.  ሀበትን ማከማቸት ሳይሆን ሀብት እንዲዋለድና አንዲባዛ ወደ ምርትና ኢዱስቲሪ፣ ትምህርትና ምርምር ትውልዱን የመምራት ስልት የሚዘረጉ ምሁራን ስብስብ ያለበት ተቋም መመሥረት

6.  ቱሪዝም ቁጥጥር የሚደረግበትና ለገቢ እንጂ ለባህልና እሴት  ብክለት እንዳይሆን መሥራት አግባብነት ያለው ፖሊሲና አመራር መስጠት

7.  ሁሉን ቅርስና እሳቤ ሴኩላራይዝ ለማድረግ ከሚሠራው ከዩኔስኮ ትምህርትንና የቱሪሰዝም መስህቦችን ነጻ ማውጣት

8.  ስኮላር ወደ ውጭ ለትምህርት የሚሄዱ ተማሪዎች ሁሉ ኢትዮጵያዊ ፍልስፍናና ራስን ከጥገኝነት ለማላቀቅና በማንነታችን ለመቆም የሚያስችለን ሚሥጥራችንን የሚገነዘቡ፣ ጠቃሚውን ትምህርት እንጂ አእመሮ አጣቢውን መቋቋም እንዲችሉ ማሠልጠን

9.  በማንም ሀገር የማይታወቅ፣ በእርዳታ የማይደገፍ ዝግ የኢትዮጵያዊያን የምርምርና የትምህረት ዩኒቭሲቶ መመስረት፤ ከሚለሙ ልዩ እውቀቶች በመነሳት ከውጭ ከምናገባው ጋር በማዋሀድና በማዋደድ፡፡

10. የአፍሪካ አህጉር-ፈለቅ እውቀት ስብሰባ፣ ምርምርና ልማት ተቋም በአፍሪካ አንድነት ሥር በኢትዮጵያዊያን መሪነት መመሥረትና አፍሪካዊ ሳይንስ ማዳበር፤ከምዕራባዊን እርዳታ ነጻ በሆነ መንገድ የሚካሔድ

11. ወደ አፍሪካ የሚገቡ ሸቀቶችን በበይነ መንግሥታት ደረጃ ተነጋግሮ ጥራታቸውን መወሰን፣ የሚተኩበትን የጋራ ፕሮዤዎች መመሥረት

12. ከቻይና ጋር ጠንካራ የእኩልነት ጥቅም ላይ የተመሠረተ፣ ከምዕራባዊያን  የብልጣብልጥነት  ግኑኝነትና ጣልቃገብነት የፀዳ የንግድ፣ የትምህርት፣ የዲፕሎማሲና የምርምር ፍኖተ ካርታ ለ20 ዓመት (በየ 2 ዓመቱ የሚመዘን ራስን ወደመቻልና ጥገኝነትን ወደመቀነስ በሚያመሩ መሥፍቶች ላይ መመሥረት)

ፋንታሁን ዋቄ


አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ገድሎና አስገድሎ ብፁዕ እየተባሉ መኖር የተፈቀደላቸው ጳጳሳትና ቆሞሳት እንዳይረሱ

ከጥር 27 ጀምሮ በተለያዩ የኦሮምያ ከተሞች በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቀኖና ውጭ የተሾሞና በቅዱስ ሲኖዶስ ተወግዘው የተለዩ አካላትን ወደ ቤተ ክርስቲያን እናስገባለን ባሉ የመንግስት የጽጥታ አካላት በተትኮሰ ጥይትና ሕገ ወጡ ቡድን ባደራጃቸው ወጣቶች ተደብድበው የተገደሉና የቆሰሉ  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ካህናትና ምእመናን።።   1)  ሻሸመኔ ከተማ   I.   የተገደሉ 1.  አያሌው ተረፈ ●   በሻሸመኔ የደብረ አስቦ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ማህደረ ፃድቃን ሰንበት ትምህርት ቤት አባል ●  ጥር 27 ዓ/ም በሻሸመኔ ከተማ በጸጥታ ሃይሉ በሚመራ የጨፍጫፊ ቡድን በደረሰበት ከፍተኛ ደብደባ ወደ ሆስፒታል ገባ ●  በአላቲዮን ሆስፒታል ሕክምና እየተደረገለት ሕይወቱን ማትረፍ አልተቻለም ●  በ ጥር 30 2015 ዓ/ም  ሰማዕትነትን ተቀብሏል       2.  ሊቀ ኅሩያን ቀሲስ ሐረገወይን ●  የሻሸመኔ ደብረ ስብሐት ቅዱስ ሚካኤል አገልጋይ የነበሩት ●  በሻሸመኔ በሕገወጦች በጸጥታ አካላት  በበግፍ በዱላ ተቀጥቅጠው በጭንቅላታቸው በእጅና በእግራቸው ላይ በደረሰባቸው ድብደባ በሀዋሳ ሕክምና እያሉ አርፈዋል። ●  ከመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች በተተኮሰ ጥይት ተመትተው  በያኔት ሆስፒታል ሕክምና ሲደረግላቸው ቢቆዩም ሕይወታቸውን ማትረፍ አልተቻለም። ●  በዛሬው ዕለት ጥር 30 2015 ዓ/ም  ሰማዕትነትን ተቀብለዋል።     3.  ዘማሪ ፍቃዱ ደጉ ●  የቅዱስ ሚካኤል ከሣቴ ብርሃን ሰ/ትቤት አገል...

ኢትዮጵያ የተገዳደሯትን ሁሉ ቅኝ ገዥወች የተከላከለችባቸው፣ የተዋጋችባቸውና ነጽነቷን ያስከበረችባቸው እሴቶች; በቀሲስ አስተርአየ ጽጌ

የጽዋዕ ማህበራትና ሰንበቴ ከቅድስት ድንግል ማርያም ጋራ የተሳሰሩት የጽዋ ማሕበራትና ሰንበቴወች ናቸው፡፡  ኢትዮጵያ የተገዳደሯትን ሁሉ ቅኝ ገዥወች የተከላከለችባቸው፣ የተዋጋችባቸውና ነጽነቷን ያስከበረችባቸው እሴቶች  ቀሲስ አስተርአየ ጽጌ  nigatuasteraye@gmail.com  ሚያዚያ ፳፩ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም.  (April 28, 2025)  መግቢያ  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያናችን ኩለንታዊት ቀዳማዊት ደኀራዊት፡ ዘመናዊት ናት ስትባል እም ኀበ አልቦ አይደለም፡፡ በብዙ እሴቶቿ ነው፡፡ ኩለንታዊት ከምታደርጋት ከብዙ እሴቶቿ መካከል የጽሑፌ መነሻ የሆኑት ከቅድስት ድንግል  ማርያም ጋራ የተሳሰሩት የጽዋ ማሕበራትና ሰንበቴወች ናቸው፡፡ ስንበቴ በቀጥታ ከእግዚአብሔር የታዘዘች ናት፡፡ የጽዋ ማኅበርም እንደ ሰንበቴው ቀጥታ ከግዚአብሔር ባይሆንም፡ በዮቶር በኩል ለሙሴ የደረሰው የግዚአብሔር ምሪት ናት፡፡ የጽዋ ማሕበርና ሰንበቴ የትርጉማቸው መነሻ፡ መድረሻና የመጨረሻ ዋና ዓላማቸው ሰባዊ ክብርና ነጻነት ነው፡፡   ኢትዮጵያ የተፈታተኗትን ሁሉ ቅኝ ገዥወች ከተከላከለችባቸው ከተዋጋችባቸውና ነጽነቷን ካስከበረችባቸው ዋናወቹ እሴቶቿ ውስጥ የጽዋ ማሕበራትና ሰንበቴወች ናቸው፡፡ በቅኝ ገዥወች ሲቀጠቀጡ ከኖሩት ካጎራባች አገሮች ልዩና የነጻነት ምሳሌ ያደርጓትም የጽዋ ማህበርና ሰንበቴ ናቸው፡፡ የጽዋ ማኅበራትና የሰንበቴ ድርጅቶች እንዴት ተመሰረቱ? ለኢትዮጵያ ምን ጠቀሙ? ትሩፋታቸው ምንድነው? የደርግንና የወያኔን ዘመናት እንዴት ተሻገሩ? በብልጽግና ዘመንስ እንዴት ናቸው? እንዴት ይቀጥሉ ? የሚሉትን ጥያቄወች ለመመለስ ከጽዋ ማኅበር እንጀምር፡፡   የጽዋ ማኅበር መነሻ...

ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን እና ቋንቋና ማንነት ተኮር እንቅስቃሴዎች

  ኦ ርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን እና ቋንቋና ማንነት ተኮር እንቅስቃሴዎች   ፩ . ቋንቋን በተመለከተ ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮና ትውፊት ከሰው ልጅ መበደል በፊት ፍጥረት ሁሉ የሚግባባው በአንድ ቋንቋ ነበር፡፡ “ ምድርም ሁሉ በአንድ ቋንቋና በአንድ ንግግር ነበረች” እንዲል፡፡ ዘፍ. 11፡1 በኃጢአት ምክንያት ግን ሰውና መላው ፍጥረት በአንድ ቋንቋ መግባባታቸው ቀረ፡፡ ኃጢአት እየበዛ ሲሄድ የሰው ልጅ ቋንቋም በባቢሎን ተደበላለቀ፣ አንዳቸው ከሌላቸው ጋር የማይግባቡ ብዙ ዓይነት ቋንቋዎችም ተፈጠሩ፡፡ በበደል የመጣውን ሁሉ ሊያስተካክልና ሊያድን በመጣው በአምላካችንና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አዳኝነት ያ የቀደመው ጸጋ ስለ ተመለሰልን በበዐለ ሃምሳ ሰዎች በልዩ ልዩ ቋንቋ አንድ ዐይነት የእግዚአብሔርን መልእክት ሰሙ፡፡ በዚህ ጸጋ የተጠቀሙና የበቁ ቅዱሳን የእንስሳትን ቋንቋ እስከ ማወቅ ደረጃ ይደርሳሉ፡፡   የክርስትና ጉዞ ወደ ቀደመው በአንድ ቋንቋ መግባባት መመለስ ነው፡፡ ወደዚያ ለመድረስ ደግሞ ሰው የእግዚአብሔርን ቃል በሚሰማው ቋንቋ መማር አለበት፡፡ በበዐለ ሃምሳ ጊዜ ለቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስ ብዙ ቋንቋ የገለጠላቸው ሰውን ሁሉ የእግዚአብሔርን የማዳን ጸጋ በሚሰማው ቋንቋ እንዲያስተምሩት ነው፡፡ ሆኖም ቋንቋ መልእክት ማድረሻና መግባቢያ እንጂ ከዚያ ያለፈ ሰዎችን በሆነ መደብ ለመመደብና የልዩነት አጥር ለመሥራት እንደ መሳሪያ ሊሆን አይገባውም፡፡ ይህ ከክርስትና ዐላማ ጋር ተቃራኒ ነው፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያት ወደ ዐለም ሁሉ ሲልካቸው ሰዎች የሚቀበሏቸው በሚያስተምሩት ትምህርት መሠረት ነበር እንጂ በትውልድ፣ በብሔርና በመሳሰለው መስፈርት የእኛ ናቸው/አይደሉም በሚል አልነበረም፡፡ የቤተ ክርስቲያ...