ወደ ዋና ይዘት ዘለው ይሂዱ

ተገፊዎች ግፍን ይቅርታ ጠየቋት

ተገፊዎች ግፍን ይቅርታ ጠየቋት

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ። አሜን።

17/11/2015

የኢትዮጵያ ክርስቲያኖች ክርስቶስን ዘንግተው በፖለቲካ ፕሮፓጋንዳ በተፈጠረ ቡድንና የቋንቋ ዘውግ ዘረኝነት ተከፋፍለው የየሰፈራቸው ጣዖት ፈጥረዋል። ይህን የሸክላ፥ የብረት፥ የመዳብ፥ የወርቅና የብር ጣዒት አይደለም። ዘመናዊው   ጣዖት የተፈጠረው ከተረፈ ማርክሲዝም፥ ከተረፈ ናዚ የተወለደው ዘረኝነት እምነቶችና በኦነግና በሕወሐት ፈጻሚነት፥ በኢትዮጵያዊነትና ኦርቶዶክሳዊነት ላይ ለ700 ዓመታት የተሰለፉ ታሪካዊ ጠላቶች አስፈጻሚነት የተመሠረተው የጎሣ ሕገ መንግሥት ነው።  

ይህ ሕገ መንግሥት መግቢያው  ብሔር ብሔረሰብና ሕዝብ የሚል ርዕስ አለው፤ ዝርዝሩ አማራና ኦርቶዶክስን መስበር ነው። ግቡና  የመጨረሻው የብሔርተኞች መንግሥተ ሰማይ በምድር ማስገኘት ነው፥ እርሱም ከኦርቶዶክስና ከአማራ ነፃ የሆነ ፓጋን ትግራይ፥ ፓጋን ኦሮሚያ ወይንም ፓጋን ኢትዮጵያን መፍጠር ነው፤ 

በዚህ አዲስ የዘረኞች “ሃይማኖት”  ዶግማው ትግራዋይነት (ሕወሐትነት) እና ኦሮሙማ ከነባር እምነቶችና ባህሎች ሁሉ በላይ ነው፥ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት፥ ኦርቶዶክሳዊነት እና ኦርቶዶክስ የሁለቱ አዳዲስ እምነቶች ጠላቶች ናቸው።  የአዳዲሶቹ “ሃይማኖቶች” የአምልኮ አፈጻጸም የሐሰት ትርክት፥ ስም ማጥፋት፥ ማፈናቀል፥ መግደል፥ ማደኸየት፥ ማምከን፥ ማሰደድ፥ ጦርነቶችን ጭሮ መፍጀት፥ ከእምነት ማስወጣት፥ በቁጥር ማሳነስ (ዲሞግራፊ መቀነስ)፥ ከውጭ ታሪካዊ ጠላቶች ጋር መሰለፍና በዓለም አቀፍ ደረጃ ኦርቶዶክሳዊነትን፥ ኢትዮጵያዊነትንና አማራን መክሰስ ናቸው።

 

የሕወሓትና የኦነግ/ኦሮሙማ/ ብልጽግና ማንነት የሚገለፀው በታሪክ ውስጥ በሚታወቁት ዘር አጥፊዎች በናዚዝም፥ በኦቶማን ቱርክ የአርመን ፍጅት፥ በቱትሲዎች የዘር ፍጅት፥ በአውሮፓዎች የአውስታራሊያና የአሜሮላ የነባር ሕዝቦች ፍጅት ነው።

ይህን ሁኔታ ወደ ጤናማ ለመመለስ፥ በሐሰት የተፈጠረውን ጥላቻና መለያየት ለማከም፥ ዜጎችን ወደ ሰብአዊ አእምሮአቸው መልሶ አንድ ቤተሰብነታቸውን ለማስታወስ ምክክር ይፈልጋል፤ እውነትን መናገር የጠይቃል፥ ተናጋሪው ጀግና በፍቅር የሚኖር መሆን ይገባዋል፥ ብልጣብልጦቸ ለሰላም ግንባታ አይሆኑም፤ ልበ-ንጹሐን ይፈለጋሉ፥ ራስወዳዶች ፍትሕ አይሰጡም፥ ራሳቸውን የናቁና ለሌለች የሚያስቡ ያስፈልገፉናል፤ የተደራጁ ሐተኞችና ቁማርተኞች አያዳምጡም፥ በኃይል የሚበልጣቸውና ለማዳመጥ እንዲቀመጡ የሚያስገድዳቸው አሸናፊ ያስፈልጋል።

አሁን ባለንበት ሁኔታ በድሎ የሚያኮርፍ፥ ዋሽቶ ዋሽታችኋል የሚል፥ ገድሎ ሞትኩኝ በማለት ይቅርታ ጠይቁኝ የሚል፤ በተቃራኒው አገር የበለጠ ይጎዳል ብሎ ይሉኝታ ቢሱን፥ ኅሊና ቢሱን፥ ፈሪሐ እግዚአብሔር የተለየውን እየተከተለ የሚለማመጥ፥ ይቅርታ የሚጠይቅ አለ። 

ይቅርታ ተጠየቅሁ፥ ይቀረኛል፥ ጥፋቴን ልማት ነው በሉልኝ፥ አንግሡኝ የሚል አለ።

ክርስቲያኑ ሌላው ይሰናከላል ብሎ እየተበደለ መከራን ይሸከማል ያኛው ከክርስቶስ ይልቅ የቋንቋ ዘውጉንና ዘረኛ የፖለቲካ ድርጅቱን ያመልካል፤ ሌላኛው ከዘመዶቹ የሰማውን የቂም ትርክት፥ ያለፈውን ዘመን ወሬና ፕሮፓጋንዳን ከቅዱሳት መጽሐፍት አስበልጧል። 

ሁሉም ለራሱ አዋቂ ሆኖ የሐዋሪያትን ትምህርትና የክርስቶስን ነገር ትቶታል።  ሚሊዮኖችን ገድሎና አገዳድሎ ሲያበቃ ይቅርታ ጠይቀኝ ይልሃል። ንስሐን ፈጽሞ ዘንግቶታል፥ ይቅርታ መጠ'የቅን እንጂ መጠየቅን ነውር አድርጎታል። 

በዚህ ውስብስብ የፖለቲካ፥ የእምነት ጉድለት፥ የቡድን-እሳቤ እስረኝነት ባሮች ሆነን የምንገኝ እኛ ምክር ሳይሆን እንዴት እንደምናሸንፍና ሂሳሳብ እንደምናወራረድ ነው የምናሰላው።  

የትግራይና የኦሮሚያ ሕዝብ በዚህ አይነት የሐሰት ትርክትና የበቀል አዙሪት ውስጥ 50 ዓመታት ስብከት ተጠልፎ እሥረኛ የሆነ ነው። መቆጣት እንጂ ማዳመጥም ይገበሀል፥ እውነቱን ምርምር  ሲሉት የዘር ፓርቲከኛውና ሕዝቡ "እንድ ናቸው" በሚል አምልኮ ተይዟል።  የእኔ አይነቱ የእውቀት ሕፃን፥ ጎዶሎ ሰው ምን መምከር ቢችል ነው ይህን ውስብስብ የሚመክረው ነገር ቢኖረኝ፦

💠ሁላችንም ይሉኝታን በመተው በሐዋሪያት ቀኖና፥ በቀደምት አበው ተግባራዊ ትውፊት፥ በመቅዱሳት መጽሐፍት ብቻ እና ብቻ መሟገት፥ "ይመስለኛል፥ ደስ ይለኛል፥ እኛ እገሌዎች እንዲ እናስባለን ወዘተ" በሚል ከንቱ ልማድ አለመጠለፍ፤

💠የሳቱ ዘመዶቻችንን ከመሳሰል እና ነፍሳችንን የመንጋ እሥረኛ ከምናደርጋት ጨክነን በመሸሽ  ክርስቶስን ለመምሰል ብቻ መኖር—> በዚህ ምክኒያት የሚመጣ ፈተና  (መገለል፥ ሥራ ማጣት፥ ግብርና ሌሎች ጫናዎች ውስጥ መውደቅ፥ ባንዳ እና ከሀዲ መባል፥ በሐሰት መከሰስና መታሰር፥ አልፎም መገደል፥ ወዘተ) ስለሚኖር ለዚያ መዘጋጀት፤

💠በጊዜውም ያለጊዜዉም በፍቅር ሆኖ እውነትን መናገር፥ ማድረግ እና ከእውነተኞቹ የጥምቀት ልጆች ከሠፈርና ቋንቋ ወጥቶ በመተባበር የፖለቲካ ድንበርን ማፍረስ፥ የክርስትና አንድነትን ማሳየት (ጨው፥ ብርሃን፥ ምስክር መሆን)

💠ከላይ የተባለውን በተግባር ለመሞከር ለራስ ቃል መግባት፥ ከሚመስሉን ሰዎች ጋር መመካከርና አንድ አቋም ላይ መገኘት፥ አብሮ አቅዶ ከሐሰተኞችና ስሑታን ጋር ለመጋደል ማቀድ፥ የሚችሉትን መሞከር፤

💠በንስሐ፥ በጸሎት፥ በዕንባና በፍርሐት፥ በትሕትና በመሆን ሆነ ተብሎ የሚሠራ ክፋት፥ ፀረ-ክርስትና አቋም ያለው ፖለቲካና ባለሥልጣን፥ ካህንና ጳጳስን ፈጽሞ ከማክበርና ከማበረታታት ይልቅ ወደ ንሥሐ ሚመለሱበት፥ ወይንም በጥፋታቸው ከጸኑ የሚወገዱበትን  (ወደ ንስሐ የብአኝነት ገዳም የሚላኩበት) ማንኛውንም (ርኩሰትና ኃጢአት) ያልሆነ እርምጃ ሁሉ መውሰድ እና እንዲወሰድ ማስተባበር፥ ማድረግ የሚችሉት እንዲያደርጉ ግንዛቤና ጫና መፍጠር።

—— ይህ ሐሳብ በተግባር ከመሞከራችን አስቀድሞ በውይይት ቢዳብርና ሊቃውንት ቢመክሩበት መልካም ይመስለኛል።

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ገድሎና አስገድሎ ብፁዕ እየተባሉ መኖር የተፈቀደላቸው ጳጳሳትና ቆሞሳት እንዳይረሱ

ከጥር 27 ጀምሮ በተለያዩ የኦሮምያ ከተሞች በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቀኖና ውጭ የተሾሞና በቅዱስ ሲኖዶስ ተወግዘው የተለዩ አካላትን ወደ ቤተ ክርስቲያን እናስገባለን ባሉ የመንግስት የጽጥታ አካላት በተትኮሰ ጥይትና ሕገ ወጡ ቡድን ባደራጃቸው ወጣቶች ተደብድበው የተገደሉና የቆሰሉ  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ካህናትና ምእመናን።።   1)  ሻሸመኔ ከተማ   I.   የተገደሉ 1.  አያሌው ተረፈ ●   በሻሸመኔ የደብረ አስቦ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ማህደረ ፃድቃን ሰንበት ትምህርት ቤት አባል ●  ጥር 27 ዓ/ም በሻሸመኔ ከተማ በጸጥታ ሃይሉ በሚመራ የጨፍጫፊ ቡድን በደረሰበት ከፍተኛ ደብደባ ወደ ሆስፒታል ገባ ●  በአላቲዮን ሆስፒታል ሕክምና እየተደረገለት ሕይወቱን ማትረፍ አልተቻለም ●  በ ጥር 30 2015 ዓ/ም  ሰማዕትነትን ተቀብሏል       2.  ሊቀ ኅሩያን ቀሲስ ሐረገወይን ●  የሻሸመኔ ደብረ ስብሐት ቅዱስ ሚካኤል አገልጋይ የነበሩት ●  በሻሸመኔ በሕገወጦች በጸጥታ አካላት  በበግፍ በዱላ ተቀጥቅጠው በጭንቅላታቸው በእጅና በእግራቸው ላይ በደረሰባቸው ድብደባ በሀዋሳ ሕክምና እያሉ አርፈዋል። ●  ከመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች በተተኮሰ ጥይት ተመትተው  በያኔት ሆስፒታል ሕክምና ሲደረግላቸው ቢቆዩም ሕይወታቸውን ማትረፍ አልተቻለም። ●  በዛሬው ዕለት ጥር 30 2015 ዓ/ም  ሰማዕትነትን ተቀብለዋል።     3.  ዘማሪ ፍቃዱ ደጉ ●  የቅዱስ ሚካኤል ከሣቴ ብርሃን ሰ/ትቤት አገል...

ኢትዮጵያ የተገዳደሯትን ሁሉ ቅኝ ገዥወች የተከላከለችባቸው፣ የተዋጋችባቸውና ነጽነቷን ያስከበረችባቸው እሴቶች; በቀሲስ አስተርአየ ጽጌ

የጽዋዕ ማህበራትና ሰንበቴ ከቅድስት ድንግል ማርያም ጋራ የተሳሰሩት የጽዋ ማሕበራትና ሰንበቴወች ናቸው፡፡  ኢትዮጵያ የተገዳደሯትን ሁሉ ቅኝ ገዥወች የተከላከለችባቸው፣ የተዋጋችባቸውና ነጽነቷን ያስከበረችባቸው እሴቶች  ቀሲስ አስተርአየ ጽጌ  nigatuasteraye@gmail.com  ሚያዚያ ፳፩ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም.  (April 28, 2025)  መግቢያ  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያናችን ኩለንታዊት ቀዳማዊት ደኀራዊት፡ ዘመናዊት ናት ስትባል እም ኀበ አልቦ አይደለም፡፡ በብዙ እሴቶቿ ነው፡፡ ኩለንታዊት ከምታደርጋት ከብዙ እሴቶቿ መካከል የጽሑፌ መነሻ የሆኑት ከቅድስት ድንግል  ማርያም ጋራ የተሳሰሩት የጽዋ ማሕበራትና ሰንበቴወች ናቸው፡፡ ስንበቴ በቀጥታ ከእግዚአብሔር የታዘዘች ናት፡፡ የጽዋ ማኅበርም እንደ ሰንበቴው ቀጥታ ከግዚአብሔር ባይሆንም፡ በዮቶር በኩል ለሙሴ የደረሰው የግዚአብሔር ምሪት ናት፡፡ የጽዋ ማሕበርና ሰንበቴ የትርጉማቸው መነሻ፡ መድረሻና የመጨረሻ ዋና ዓላማቸው ሰባዊ ክብርና ነጻነት ነው፡፡   ኢትዮጵያ የተፈታተኗትን ሁሉ ቅኝ ገዥወች ከተከላከለችባቸው ከተዋጋችባቸውና ነጽነቷን ካስከበረችባቸው ዋናወቹ እሴቶቿ ውስጥ የጽዋ ማሕበራትና ሰንበቴወች ናቸው፡፡ በቅኝ ገዥወች ሲቀጠቀጡ ከኖሩት ካጎራባች አገሮች ልዩና የነጻነት ምሳሌ ያደርጓትም የጽዋ ማህበርና ሰንበቴ ናቸው፡፡ የጽዋ ማኅበራትና የሰንበቴ ድርጅቶች እንዴት ተመሰረቱ? ለኢትዮጵያ ምን ጠቀሙ? ትሩፋታቸው ምንድነው? የደርግንና የወያኔን ዘመናት እንዴት ተሻገሩ? በብልጽግና ዘመንስ እንዴት ናቸው? እንዴት ይቀጥሉ ? የሚሉትን ጥያቄወች ለመመለስ ከጽዋ ማኅበር እንጀምር፡፡   የጽዋ ማኅበር መነሻ...

ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን እና ቋንቋና ማንነት ተኮር እንቅስቃሴዎች

  ኦ ርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን እና ቋንቋና ማንነት ተኮር እንቅስቃሴዎች   ፩ . ቋንቋን በተመለከተ ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮና ትውፊት ከሰው ልጅ መበደል በፊት ፍጥረት ሁሉ የሚግባባው በአንድ ቋንቋ ነበር፡፡ “ ምድርም ሁሉ በአንድ ቋንቋና በአንድ ንግግር ነበረች” እንዲል፡፡ ዘፍ. 11፡1 በኃጢአት ምክንያት ግን ሰውና መላው ፍጥረት በአንድ ቋንቋ መግባባታቸው ቀረ፡፡ ኃጢአት እየበዛ ሲሄድ የሰው ልጅ ቋንቋም በባቢሎን ተደበላለቀ፣ አንዳቸው ከሌላቸው ጋር የማይግባቡ ብዙ ዓይነት ቋንቋዎችም ተፈጠሩ፡፡ በበደል የመጣውን ሁሉ ሊያስተካክልና ሊያድን በመጣው በአምላካችንና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አዳኝነት ያ የቀደመው ጸጋ ስለ ተመለሰልን በበዐለ ሃምሳ ሰዎች በልዩ ልዩ ቋንቋ አንድ ዐይነት የእግዚአብሔርን መልእክት ሰሙ፡፡ በዚህ ጸጋ የተጠቀሙና የበቁ ቅዱሳን የእንስሳትን ቋንቋ እስከ ማወቅ ደረጃ ይደርሳሉ፡፡   የክርስትና ጉዞ ወደ ቀደመው በአንድ ቋንቋ መግባባት መመለስ ነው፡፡ ወደዚያ ለመድረስ ደግሞ ሰው የእግዚአብሔርን ቃል በሚሰማው ቋንቋ መማር አለበት፡፡ በበዐለ ሃምሳ ጊዜ ለቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስ ብዙ ቋንቋ የገለጠላቸው ሰውን ሁሉ የእግዚአብሔርን የማዳን ጸጋ በሚሰማው ቋንቋ እንዲያስተምሩት ነው፡፡ ሆኖም ቋንቋ መልእክት ማድረሻና መግባቢያ እንጂ ከዚያ ያለፈ ሰዎችን በሆነ መደብ ለመመደብና የልዩነት አጥር ለመሥራት እንደ መሳሪያ ሊሆን አይገባውም፡፡ ይህ ከክርስትና ዐላማ ጋር ተቃራኒ ነው፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያት ወደ ዐለም ሁሉ ሲልካቸው ሰዎች የሚቀበሏቸው በሚያስተምሩት ትምህርት መሠረት ነበር እንጂ በትውልድ፣ በብሔርና በመሳሰለው መስፈርት የእኛ ናቸው/አይደሉም በሚል አልነበረም፡፡ የቤተ ክርስቲያ...