በቤተ ክርሲያን ላይ ቅሬታ አለኝ የሚል ሰው ማነው?
ስድቡ ይገባዋል? አምላክ ላይ መቂጣቱን ይረዳል?
አንድ ሰው #ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያንን ላይ ጥላቻ ቀርቶ #"ቅሬታ አለኝ" ከአለ፣ "በእግዚአብሔር በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ ቅሬታ አለኝ" ማለቱ ነው።
ቤተ ክርስቲያን ሰማያዊው አምላክ የክርስቶስ ሰማያዊ መንግሥቱን በመስቀል ላይ በፈቃዱና በፍቅረ-ስብእ በፈጸመው ሞቱ ለምድራውያን ገልጠ። ይህ መገለጥ ለተቀበሉትና ወደፊትም እስከ ዳግም ምጽዐቱ ለሚቀበሉት ምድራውያንን ከሰማያውያን ያወሐደባት፣ እርሱ ክርስቶስ ራስ በሆነላት በአካሉ በቤተ ክርስቲያን (በከርስቲያን አንድነት) የአካሉ ብልቶች ያደረገባት ናት።
ቤተ ክርስቲያን በክርስቶስ ራስነት እና በተቀበሉት ብልቶቹ አንድነት ምክንያት መጉደል፣ መወየብ፣ ማነስ፣ መለዋወጥ፣ መወሰን የላባትም።
ለውጥ፣ መጉደል፣ ማነስ፣ መወይብ፣ መጥቆር ከታየ፣ የእርሷ አይደለም። በስሟ የሚጠሩ፣ በስሟ የተካኑ ነገር ግን ከማይለወጠው ራስ ተለይተው የተቆርጡና በሌላ ሙት ራስ ስር የተኮለኮሉ ሙታን ጉባኤ ነው።
በርግጥ በዚህ ምድር ያለን የአካላቱ ብልቶች ከታላቁ ሰማያዊ ማኅበር አንጻር ስንታይ ጥቂቶችና በእንድ የግዙፍ ሰው አካል ላይ ከሚገኙ ብልቶች እንደ እንድ ጣት ልንቆጠር የምንችል ነን። እንደዚሁም ሆኖ በቁጥር የዚህ ማኅበር አባላት መቶ ሚሊዮኖች ነን። በአህጉረ ስብከት አሥራ ሙሊዮኖች፣ በአጥቢያ አሥራ ሺዎች እና አሥራ መቶዎች፣ ብሎም በስደት ስንበታተን መቶዎችና አሥራዎች እንሆናለን።
ከሕያው ግንድ ከክርስቶስ የአካል ብልትነት ቡድን ሆነን እንዳንከፈልና ለሕይወት ባእዳን ነገር ግን ለሞት ደቀ መዝሙር እንዳንሆን፣ ኢአማኒም ሆነን በግል ተቆርጠን እንዳንርቅ የሚጠብቁን ክርስቶስ ልዩ የሆነ ሥልጣን የሰጣቸው ግለሰቦች እና ስብስባቸው አለ። እርሱም ካህናትና ቆሞሳት ናቸው። ስልጣናቸውን የሰማያዊ አምላክ በትርና መሪ ብርሃን እንዲሁም ሕይወትና ሰይፍን ያጣመር ልዩ መገለገያ #ክህነት ነው።
ክህነት የዘላለም ሕይወት በትር ናት! የቤተ ክርስቲያን ህልውና መሠረት፣ የማኅበሩ መደምሪያና መዋሐጃ አማራጭ የማይገኝለት የመንፈስቅዱስ ጽጋ የሚናኝበት የክርስቶስ እጅ ናት።
በትሯን ሳይዙ የያዙ መስለው ሞትን በዓልም ያንሰራፉትም በዚሁ ስም የተጠሩና በዲያብሎስ የተውሰዱ ጥቂት መናፍቃን፣ ከሃዲዎች፣ ምንደኞች፣ ቅድስና የጎደላቸው ከንቱዎች ናቸው።
በአገራችን ብቻ ሳይሆን በመላው ዓለም፣ ዘንድሮና ድሮ በቻ ሳይሆን ከጥንት ጀምሮ ወደዚህ ልዩ አግልግሎት ከሚመጡት መካከል ጥቂት አጥፊዎች ሰረገው ገብተው ከይሁዳ እስከ ዛሬው ሠረቀ ብርሃንና ሳዊሮስን የመሰሉ የጎሣ ፖለቲካ ርእዮት ተልእኮ ተሽክመው ከታላቁ የዘልዓለም ሕይወት ግንድ ላይ እየቆረጡ ከሙት የጎሣ፣ የኑፋቄ፣ የፍቀረ ንዋይ ማኅበር ጋር የሚደምሩ ነበሩ። ዛሬም ተንሰራፈተዋል።
በዚህ እይነት መንገድ የቤተ ክርስቲያን የውስጥ ጠላቶች ከሳቱ ሙታን የዓለማውያን የፖልቲካ መሪዎች ጋር በመጣመር ዓለምን አሠዝመዋል (እንደ ምሳሌ የቤዛንታይን ክርስትና ወደ ሮማ ካቶሊክ፣ ኑፋቄ፣ ክፍደት፣ ሴኩላር በማድረግ ለዳርዊን፣ ለማርክስ፣ ለፈረንሳይ አብዮተኞች፣ ለሜንሼቪክ እና ቮልሼቪክ) መፈጠር በቻ ሳይሆነ ዘረኝነትን፣ ቅኝ ገዥነትን፣ ባሪያ ፈንገላን፣ ዘር ማጥፋትን፣ ስግብግብነትን በዓለም እንዲሠራንፋ ምክንያት የሆኑ መንግሥታትና የፖለቲካ ርእዮቶችን እንዲነግሥ ያስቻሉት ወደክህነት ገብተው በትቃራኒ ሚና የተገኙት ናቸው። ይህ አውሮፓን አጥፍቶ ወደ ተረፈችዋ ኢትዮጵያ በስፊ እጁ የመጣው በዘመነ መሳፍንት እና ራሱን በመንግሥትነት የሰየመው በንፈሰ ገዳዩ ጄኔራል መንግሥቱ ንዋይና ወንዱም ግርማሜ ንዋይበር ከፋችነት እሰክ ዛሬ ለደረስንበት ነፈሰ ገዳዮችንና ዘረኞችን "ብፁዕ" የሚል ሲኖዶስ እና ክርስትናና በመዋቅር የሚያጠፋ የብልጽግና መንግሥት እደረሰን።
ሰይጣን ከሁሉ ተንኮሎቹ በላይ ወጤታማ የጥፋት መንግደ ሆኖ ያገኘው ሰዎች የቤተ ክርስቲያንን ብርሃን እንዳያዩ እንዳይረዱ "ቤተ ክርስቲያ፣ ክርስቲያን፣ ካህን፣ አባት፣ ዘማሪ፣ ሰባኪ" በሚሉ ሽፋኖች ወስጥ የሚኖሩ አስመሳይ ሙታንን ሕያዋን አስመስሎና ዝናቸውን ናኝቶ ምእመናንን በሚሊዮኖች በጭፍን መንጋነት መንዳት መቻሉ ነው።
አንዳዶች እውነትና ተናጋሪ አባቶች ሲታዩ ተስፋ ያጭራሉ። ያደፈጡት ወንጀለኞች ቢባሉ ክሱ አይበዛባቸዉም፤ ምክንያቱም እረኛ ሆኖ በጎቹን በማድፈጥ የሚያስበላ፣ መብራት ይዞ ብዙኃንን በጨለማ ውስጥ ጥሎ የሚደበቅ፣ እውነትን ይዞ ሐሰት ከግለ ሰቦች ስሕተትነት ወደ መንግሥታዊ ሥርዓት ስታድግ ያልሞገት፣ በጎቹን አሰልፎ በትኩላዊ ፊት ዘምሩ እያለ የሚያስበላ "ካህን" ነኝ ማለት አይችልም። ክህነቱ ክርስቶስን ሳይሆን የከርስቶሳውያንን ጠላት የሚያገለግል የሞት በትር ሆኗልና።
እስቲ ብዙ አስተራየ ጽጌዎችን እግዚአብሔር እንዲያስነሳልን እንጸልይ።
https://youtu.be/fAKXR9mdQLA?si=b0NX7CpysXtksG3H
ከጥር 27 ጀምሮ በተለያዩ የኦሮምያ ከተሞች በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቀኖና ውጭ የተሾሞና በቅዱስ ሲኖዶስ ተወግዘው የተለዩ አካላትን ወደ ቤተ ክርስቲያን እናስገባለን ባሉ የመንግስት የጽጥታ አካላት በተትኮሰ ጥይትና ሕገ ወጡ ቡድን ባደራጃቸው ወጣቶች ተደብድበው የተገደሉና የቆሰሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ካህናትና ምእመናን።። 1) ሻሸመኔ ከተማ I. የተገደሉ 1. አያሌው ተረፈ ● በሻሸመኔ የደብረ አስቦ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ማህደረ ፃድቃን ሰንበት ትምህርት ቤት አባል ● ጥር 27 ዓ/ም በሻሸመኔ ከተማ በጸጥታ ሃይሉ በሚመራ የጨፍጫፊ ቡድን በደረሰበት ከፍተኛ ደብደባ ወደ ሆስፒታል ገባ ● በአላቲዮን ሆስፒታል ሕክምና እየተደረገለት ሕይወቱን ማትረፍ አልተቻለም ● በ ጥር 30 2015 ዓ/ም ሰማዕትነትን ተቀብሏል 2. ሊቀ ኅሩያን ቀሲስ ሐረገወይን ● የሻሸመኔ ደብረ ስብሐት ቅዱስ ሚካኤል አገልጋይ የነበሩት ● በሻሸመኔ በሕገወጦች በጸጥታ አካላት በበግፍ በዱላ ተቀጥቅጠው በጭንቅላታቸው በእጅና በእግራቸው ላይ በደረሰባቸው ድብደባ በሀዋሳ ሕክምና እያሉ አርፈዋል። ● ከመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች በተተኮሰ ጥይት ተመትተው በያኔት ሆስፒታል ሕክምና ሲደረግላቸው ቢቆዩም ሕይወታቸውን ማትረፍ አልተቻለም። ● በዛሬው ዕለት ጥር 30 2015 ዓ/ም ሰማዕትነትን ተቀብለዋል። 3. ዘማሪ ፍቃዱ ደጉ ● የቅዱስ ሚካኤል ከሣቴ ብርሃን ሰ/ትቤት አገል...
አስተያየቶች