የድንቁርናና ሕሊና-ቢነስት ያነገሣቸው የጎሣ ልሂቃን "የምሥራች" ትርጉም
አምባገነን፥ ቁማርተኛና የወሮበሎች መንግሥት የሚመራውን ሕዝብ መከራ "የምሥራች" እያለ ያለማምደዋል። የሕወሃት/ኢሕአዴግና ብልጽግና በዚህ ሞትና መከራን ድልና እድገት አድርገው በማቅረደብ አንድ አይነት ናቸው።
ስዩም መስፍንና አሊ አብዶ የሕወሃትና የሻዕብያ የዘረፋ ሀበት ክፍፍል ግጭት በባድሜ እንደ ምክንያት ትርጉም-የለሽ ከ120 ሺህ ሕዝብ በላይ ወገን አስፈጅተው፥ ይግባኝ በሌለው የአልጀርስ ስምምነት "የምሥራች፥ እንኳን ደስ ያላችሁ" ብለው ሕዝቡን አስጨፍረዉታል።
የፈረደበትን ዐመሓራና ኦርቶዶክስ ክርስትናን በማጠፋት አጀንዳ ላይ ቢስማሙም ነገር ግን በተለመደው የሀብት፥ የብሔር ግዛት በሰስፋት፥ ዲሞግራፊ በመቀየር፥ አሰስ አገር የመፍጠር እና የበላይነት ለማስፈን ባደረጉት ግጭት ሕወሃትና ብልጽግና በየበኩላቸው ወደ ጦርነት የመሩትን ወገን ድል አግኝተናል፥ የባሰ አደጋ እንዳይመጣ አድርገናል ብለው "የምሥራች" ብለዋል።
ብልገግና የአባይ ግድብ ከደ ጋየወረደው የክረምት ጎርፍ ስለ ሞላ የምሥራች በሚ ልሕበቡን በተለይ አሰስ አበባ ውስጥ አስጨፈሩ ፥ ግን የኢትዮጵያን ባንዲራ ያውለበለቡ ወጣቶችን የኦሮሙማው ፖሊስ ሠራዊት ቀጠቀጠው፤
አብይ አህመድ የአዲስ አበባ፥ የደብረ ዘይት፥ የናዝሬትና ሌሎች ከተሞች ነዋሪችን የሕዝብ አሠፋፈር ለመቀየር ኦርቶዶክስ ክርስቶያቸኖችን፥ ጉራጌዎች፥ ኮንሶዎች፥ ወላይታና ጋሞዎች ወዘተ ዒላማ ያደረገ ማፈናቀል እያካሄደ "ከተሞቻችን እያማሩ ነውና የምሥራች" ብሏል።
የአማራን ሕዝብ በምድርና በረር ኃይል ሕዓናትን፥ ካህናትን፥ ገዳማውያንን፥ ገበሬዎችን በመጨፍጨፍ ላይ የሚገኘው የአብይ አህመድ አስተዳደር "ጽንፈኛው ፋኖ እየተመታ ለስሆነ የምሥራች" የሚሉ በበሉበት የሚጮኹ ሕሊና ቢስ ሰዎችና የጎሣ አደረጃጀቶች እንዲጮኹ ታዘው እያደረጉት ነው።
የአፍሪካ አንድነ ትድርጀት የግዛት አንነድትን የሚመለከት የቻርተሩን አንቀጽ የሚጥስ የእውር ድንብር ውሳኔ በመወሰን ከሶማሌ ላንድ ጋር የቀጠናውን አጠቃላይ ሰላም ያወከ፥ ቱርክ ናግብጽን ወደ ምሥራቅ አፍሪካ በመጎተት ኢትዮጵያን ባመስከበብ አደጋ የደቀነው የአብይን እብደት "የባህር በር አገኘሁላችሁ – የምሥራች" ብሏል።
ሕዝቡ ፈዝዞና ደንዝዞ እየገደለው፥ አገሩን እያፈረሰበት፥ እያፈናቀለውና እያሳደደው "የምሥራች" እያለ ከቀሚልድበት ድንቁርናና ሕሊና-ቢስነት ካነገሣቸው የጎሣ ቁማርተኛ ልሂቃን ራሱን ነጻ ማውጣት ይኖርበታል።
አንድ ሕዝብ በመተማመን አንድ ሆኖና ጠንክሮ ከግፈኛ ሥርዓት ነጻ እንዳይወጣ እንቅፋት የሚሆኑት ጆሮ ጠቢ፥ ዘረኛ፥ ጉበኛ፥ ሳይሠራ ለመበልጸግ የሚሰለፍ፥ ባንዳ፥ ሆድ አደርና ፈሪሃ እግዚአብሔር የሌላቸው አድርባዮች በመካከሉ ሲንሰራፉ ነው። እናም እነዚህ አይነት ሰዎች መራቅ ብቻ ሳይሆን በመቅጣት ራሱን እያጸዳ ሕዝቡ ለክፉ ሥርዓት መወገድ የሚቻለውን በግልና በወል ማድረግ አሁን፥ ዛሬ የሚጀመር ጉዳይ ነውና ---- ነጻ አውጭና መፍትሔ ሰጭ ከመጠበቅ ተላቅቆ ወደ ትግል ይግባ!!!
አስተያየቶች