ልማቱ በማን መቃብር ላይ፣ ለማን? ብሎ መጠየቅ ይገባል። ዝም ብለህ አታጨብጭብ!! ልማት ያስፈልገናል፣ ግን እኛን ቀብሮ አይደለም።
ኦርቶዶክሳውያን፣ አማሮች እና ሌሎችም ዒላማ የተደረጉ ማኅበረሰቦች ይጠይቁ።
ልማት ያስፈልገናል፣ ግን እኛን ቀብሮ አይደለም።
ኦርቶዶክሳውያን፣ አማሮች እና ሌሎችም ዒላማ የተደረጉ ማኅበረሰቦች ይጠይቁ።
ወገኔ ከሰው ክብርና ከህልውና መረጋገጥ ተጋድሎ የሚያዘናጋ ፕሮፓጋንዳ ሊፈጠር አይችልም። ከንቱ ልፋት ነው።
ከሁሉ በፊት ክብረ-ስብእ!!
ከሰው የሚበልጥልማት የለም!! ልማት ለሰው ነው እንጂ ሰው እንደ ግባት ሌላው ለሚጠቀምበት ለልማት አይደለም። ገልብጦ ማሰብ የዘረኞችና ይቅኝ ገዥዎች እንጂ የአንድ ሉዓላዊ አገር መንግሥት ፖልቲካና ፍልስፍና ሊሆን አይገባዉም ነበር።
ሰማይና ምድር የተፈጠሩት፣ አምላክ ሰው ሆኖ የተሰቀለውና ዛሬ መስቀልን የምናከብረው ሁሉም ለሰው ልጆች ከእግዚአብሔር የተሰጠ ጸጋና ጸጋውን የመጠበቅና የማመስገን ሕይወት ነው።
ታዲያ ሰውን ከሰውነቱ ያዋረደ፣ በቋንቋ፣ በእምነትና በጎሣ ከፋፍሎ የሚያጠፋ፣ ከሰው ነፍስ ይልቅ የማይጸድቀው የፕሮፓጋንዳ ችግኝ ይበልጥብኛል ያለን፣ ጦር ሠራዊት “ልምራህ ላበልጽግህ” በሚለው ዜጋ ላይ ያዘመተ መንግሥት፣ ፈጣሪዎቹ የውስጥ እና የውጭ ወዳጆቹ ሁሉ
#አብይ አህመድ #ግድብ፣ #ወደብ፣ #ኒውክለር፣ #ችግኝ፣ #መናፍሻ፣ #ሳተላይት ማምጠቅ ወዘተ ሁሉ ---- ለሚያጠፋቸው ኦርቶዶክሳውያንና አማሮች ሳይሆን --- መርጦ ልዩ ጥቅም፣ ልዩ ክልል፣ ልዩ ልማት፣ ልዩ ከተማ፣ ልዩ ተርክት፣ ልዩ --- ወዘተ የገባዋል ለሚባለውና የኦነግ የዘር ልሂቃን ለፈጠሩት “ኦሮሙማ” ለተባለ የፖልቲካ ፍጡር አይደለም ማለት ይቻላል። ቀይ ባሕር ወድብ ብቻ ሳይሆን የኢሬቻ ማክበሪያ የሌሎች መቀብሪያ እንደሆነ ሽመልስ አብዲሳ ነግሮናልና መጀመሪያ ህልውናችንን እናረጋግጥ።
ለሚያፈናቀለው፣ ለሚፈጀውና ለሚጠላው ወገን መቃብር እንጂ ግድብና ወደብ አይታሰብለትም።
ከጥር 27 ጀምሮ በተለያዩ የኦሮምያ ከተሞች በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቀኖና ውጭ የተሾሞና በቅዱስ ሲኖዶስ ተወግዘው የተለዩ አካላትን ወደ ቤተ ክርስቲያን እናስገባለን ባሉ የመንግስት የጽጥታ አካላት በተትኮሰ ጥይትና ሕገ ወጡ ቡድን ባደራጃቸው ወጣቶች ተደብድበው የተገደሉና የቆሰሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ካህናትና ምእመናን።። 1) ሻሸመኔ ከተማ I. የተገደሉ 1. አያሌው ተረፈ ● በሻሸመኔ የደብረ አስቦ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ማህደረ ፃድቃን ሰንበት ትምህርት ቤት አባል ● ጥር 27 ዓ/ም በሻሸመኔ ከተማ በጸጥታ ሃይሉ በሚመራ የጨፍጫፊ ቡድን በደረሰበት ከፍተኛ ደብደባ ወደ ሆስፒታል ገባ ● በአላቲዮን ሆስፒታል ሕክምና እየተደረገለት ሕይወቱን ማትረፍ አልተቻለም ● በ ጥር 30 2015 ዓ/ም ሰማዕትነትን ተቀብሏል 2. ሊቀ ኅሩያን ቀሲስ ሐረገወይን ● የሻሸመኔ ደብረ ስብሐት ቅዱስ ሚካኤል አገልጋይ የነበሩት ● በሻሸመኔ በሕገወጦች በጸጥታ አካላት በበግፍ በዱላ ተቀጥቅጠው በጭንቅላታቸው በእጅና በእግራቸው ላይ በደረሰባቸው ድብደባ በሀዋሳ ሕክምና እያሉ አርፈዋል። ● ከመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች በተተኮሰ ጥይት ተመትተው በያኔት ሆስፒታል ሕክምና ሲደረግላቸው ቢቆዩም ሕይወታቸውን ማትረፍ አልተቻለም። ● በዛሬው ዕለት ጥር 30 2015 ዓ/ም ሰማዕትነትን ተቀብለዋል። 3. ዘማሪ ፍቃዱ ደጉ ● የቅዱስ ሚካኤል ከሣቴ ብርሃን ሰ/ትቤት አገል...
አስተያየቶች