የቱ አጀንዳ ይብስብሃል?
ኢትዮጵያውያን ሁሉ በተለይ ኦርቶዶሳውያን አጀንዳ በዛብን። ፺፱ በ፻ ፈታኝ አጀንዳዎች የተሰጡን ከውጭ ነው። ነገር ግን ፩ በ፻ው የውስጡ ለውጭው ፺፱ኙ ጉዳት የማድረስ አቅም ምንጭ ናቸው።
አጀንዳዎቹ በአብዝኃኛው ይቆዩ የማይባሉ ተጣማሪ፣ ተደጋጋፊና ተናባቢዎች ሆነው የህልውና አደጋ የጋረጡ ናቸው። እናም ካልፈታማቸው ያጠፉናል። እያጠፉንም ነው።
ከብዛታቸው የተነሳ ምላሽ ለመስጠት (፩) በአንገብጋቢነት፣ (፪) በስልታዊነት፣ (፫) በወሳኝ ቁልፍነት፣ (፬) በአስቸኳይነታቸው ፣ እና (፭) የጥምር አጥፉዎቻችንን ትብብር በማዛባት ባለው ፋይዳ እየመዘንን ቅድመተከተል ማስያዝ ቢሞከር ከ፶ በ፻ው በላይ በ፩ኛ ደረጃ ሊቀመጡ የሚችሉ ይሆኑና ግራ ያጋቡናል።
ጥቂቱን ልጥቀስና እናንተ ቅደምተከትል አውጡለት:-
፩) ከፋፋይ የዘር ፖለቲካን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ከህግነት፣ ከትምህርትና ከትውልድ አእምሮ መፋቅ፤
፪) የጎሣ ክልልና አስተዳደር ማፍረስና በዜጎችገንቢ መስተጋብርና ሁለንተናዊ ሰላምና እድገት አመቺነት ብማደራጀት፤
፫) በባውዳን ፈጣሪነትና ምሁርነትን የተቀቡና የተላላኩነት ሚናቸው ባረከሰው ሰብእናቸው የሐሰት ትርክት በማምረት ማኅበረሰባችንን የመረዙ ሰነዶች፣ በሰነዶቹና ትርክቶቹ አንጻር የተፈጠሩ አደረጃጀቶችና የአስተሳሰብ አሰላለፎችን ማፍረስ፤
፬) ኦርቶዶክስ ክርስትናን በአሉታዊነት በመሳል የቆመውን ስሕተት በሁሉም ዘርፍ፣ በውስጥም በውጭም ያለውን ሰልፍ ማሸነፍ፤
፭) በስሑት ርእዮት ሞተርነት፣ በሐሰተኛ ትርክት አቀጣጣይነት፣ በጎሣ ነጻ እውጭ ነን ባዮች፣ በጽንፈኛ ዉሀብያዎች፥ እና የናዚ የየጀርመን ክርስትና ዘር አጥፊ ፕሮቴስታንቶች ቀጥተኛ ፈጻሚነት፣ በብልጽግና ወንጌል የሃይማኖት መንግሥት አመራርና አስተባባሪነት በኦርቶዶክሳውያን ላይ የሚካሄደውን ዘር የማጥፋት ሁለገብ ጥቃት ማስቆም፤
፮) ላለፉት ፶ ዓመታት በኦርቶዶክስ ክርስቲያን ዜጎች ላይ በመላ ኢትዮጵያ የደረሰውን ጥቃት ቆጥሮና መዝኖ መካስ፣ ማቋቋም፣ አጥቂዎችን ለይቶ ለፍትሕ አደባባይ ማብቃት፤
፯) በተላላኪ የጌሣ መንግሥታት ተላላነትና ተላላኪነት ምክንያት የተፈረሙ ጎጅ እና አስገዳጅ ስምምነቴች፣ እዳዎች፣ የተፈጠሩ ሁለገብ ጥገኝነቴችን መሻርና ለአገር ዘለቄታዊ ጥቅም በሚውሉበት መንገድ ማስተካከል፤
፯) የአገሪቷንብየግዛት አንድነትና ዳር ድንበር ዋስትና ባለው መንገድ ማስከበር፤
፯) በስሑት የተውሶ ፖለቲካዊ ርእዮት እና ሐሰተኛ ትርክት ምክንያት የላላውን የሕዝብ መተማመንና አንድነት መመለስ፤
፰) አንድ አገራዊ የጋራ ቋንቋ፥ አንድ ዓለም አቀፍ ቋንቋ ውንዲነገርና ትውልድ ሁሉ ሲገናኝ የሚግባባበት፣ የሚማማርበት፣ የሚናገድበት፣ የሚመራመርበት ወጥ ቋንቋ ማንበር፤
፱) የንዑስ ማንነት ብዝኃነት ከፖለቲካ መሣሪያነት ተወግዶ የልዩ ልዩ ጸጋዎች መጋቢና ወደ ተዋሕዶ የሚያድግበት ሥርዓትና አስተሳሰብ መመለስ፤
፲) የኢትዮጵያ ትምህርት ዩኒቨርሳል/ሉላዊነትን ከነባርነት ያዋሐደና ከሁለገብ ጥገኝነት በሚያላቅቅ መሠረት ላይ ማቆም፤
፲፩) እምነቶች ከአገራቸው ወገን የሚገፋፉበትና ከውጭ የኢትዮጵያ አጽራራት ጋር የሚጎዳኙበት ልማድ ፈጽሞ እግድ የሚሆንበት፤
፲፪) የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን፣ የባህል፣ የኢትዮጵያዊ ሙስሊም ልዩ አገር ፈለቅና ነባር በሁሉ የሕይወት ዘርፎች የሚገኙ ዕውቀቶች ለዘመናዊ ትምህርት ሁሉ በየደረጃው መሠረትና ተመጋጋቢንየሚሆኑበት መዋቅራዊና ሥርዓታዊ አሠራር፤
፲፫) የአባይ ወንዝ ተጠቃሚ ቤተሰቦች ሁሉ ከሽሚያ የቅኝ ገዥዎች ማኅቀፈ-ዕሳቤ ወደ ስነ ምህዳራዊ የጋራ ልማት ውህደት ገብተው መገፋፋት እንዲያቆሙ ማድረግ
፲፬) የአፍሪቃ ቀንድ የኢኮኖሚና የፖለቲካ ውህደት፣ የአፍሪቃ የተባበረ መንግሥት ምሥረታና የሌሎች አህጉራት ያልተገባ ጣልቃገብነት ማብቃት፤
፲፭) የአማራን ሕዝብ ለማሳነስ፣ ለመከፋፈል እና ብሎም ለማጥፋት የተተረከው ትርክት፣ የተፈጠረው ሁለገብ አሰላለፍ፣ እና የደረሰውን እየደረሰ የሚገኘው ሁለገብ ጥቃት ዋስትና በሚሰጥ መሠረት ላይ ተፈትቶ እንዲቆም ------
≠==============
በእነዚህ ማስፈንጠሪያዎች ሁሉ ለመወያየት አለሁ። ነገር ግን ዘመኑ የፈጠራችሁ
ከሰው አንባ ወደ ጎሣ ቡድን ዕሳቤ እሥረኝነት ያልወረዳችሁ አትምጡ። ባለነጻ አእምሮ ወዳጆቼን ብቻ ነው የጋበዝኩት። ዘረኞችና ተላላኪዎች በነዚህ ገጾች ላይ ብትገኙ የእናንተ ድምጽ ዋጋ ስለማያወጣና ምላሽ ጨካኝ ስለሚሆን እንዳትጎዱ ራሳችሁን አርቁ።
👉 ትዊተር https://x.com/fwakie
👉 ቴሌግራም @Fantahun_Wakie
👉ዩቲዩብ https://www.youtube.com/@Orthodoxy-VS-Secularism
👉https://www.youtube.com/@finoteretuan-2
👉 ፌስ ቡክ. https://www.facebook.com/profile.php?id=61576051634449
👉 https://www.facebook.com/fwakie
👉 ቲክቶክ፡ https://www.tiktok.com/@fantahunwk?_t=8qLqoSRV9Ta&_r=1
👉ብሎግ፡ https://ethiopiaorthodoxchristian.blogspot.com/
ሰላመ እግዚአብሔር አይለየን።ue about the Orthodox Apolostic Church and the Holy Ethiopia
ከጥር 27 ጀምሮ በተለያዩ የኦሮምያ ከተሞች በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቀኖና ውጭ የተሾሞና በቅዱስ ሲኖዶስ ተወግዘው የተለዩ አካላትን ወደ ቤተ ክርስቲያን እናስገባለን ባሉ የመንግስት የጽጥታ አካላት በተትኮሰ ጥይትና ሕገ ወጡ ቡድን ባደራጃቸው ወጣቶች ተደብድበው የተገደሉና የቆሰሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ካህናትና ምእመናን።። 1) ሻሸመኔ ከተማ I. የተገደሉ 1. አያሌው ተረፈ ● በሻሸመኔ የደብረ አስቦ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ማህደረ ፃድቃን ሰንበት ትምህርት ቤት አባል ● ጥር 27 ዓ/ም በሻሸመኔ ከተማ በጸጥታ ሃይሉ በሚመራ የጨፍጫፊ ቡድን በደረሰበት ከፍተኛ ደብደባ ወደ ሆስፒታል ገባ ● በአላቲዮን ሆስፒታል ሕክምና እየተደረገለት ሕይወቱን ማትረፍ አልተቻለም ● በ ጥር 30 2015 ዓ/ም ሰማዕትነትን ተቀብሏል 2. ሊቀ ኅሩያን ቀሲስ ሐረገወይን ● የሻሸመኔ ደብረ ስብሐት ቅዱስ ሚካኤል አገልጋይ የነበሩት ● በሻሸመኔ በሕገወጦች በጸጥታ አካላት በበግፍ በዱላ ተቀጥቅጠው በጭንቅላታቸው በእጅና በእግራቸው ላይ በደረሰባቸው ድብደባ በሀዋሳ ሕክምና እያሉ አርፈዋል። ● ከመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች በተተኮሰ ጥይት ተመትተው በያኔት ሆስፒታል ሕክምና ሲደረግላቸው ቢቆዩም ሕይወታቸውን ማትረፍ አልተቻለም። ● በዛሬው ዕለት ጥር 30 2015 ዓ/ም ሰማዕትነትን ተቀብለዋል። 3. ዘማሪ ፍቃዱ ደጉ ● የቅዱስ ሚካኤል ከሣቴ ብርሃን ሰ/ትቤት አገል...
አስተያየቶች