ወደ ዋና ይዘት ዘለው ይሂዱ

ከሁሉም የህልውና አጀንዳዎች የቱ ይብስብሃል? ይብስብሻል?

የቱ አጀንዳ ይብስብሃል? ኢትዮጵያውያን ሁሉ በተለይ ኦርቶዶሳውያን አጀንዳ በዛብን። ፺፱ በ፻ ፈታኝ አጀንዳዎች የተሰጡን ከውጭ ነው። ነገር ግን ፩ በ፻ው የውስጡ ለውጭው ፺፱ኙ ጉዳት የማድረስ አቅም ምንጭ ናቸው። አጀንዳዎቹ በአብዝኃኛው ይቆዩ የማይባሉ ተጣማሪ፣ ተደጋጋፊና ተናባቢዎች ሆነው የህልውና አደጋ የጋረጡ ናቸው። እናም ካልፈታማቸው ያጠፉናል። እያጠፉንም ነው። ከብዛታቸው የተነሳ ምላሽ ለመስጠት (፩) በአንገብጋቢነት፣ (፪) በስልታዊነት፣ (፫) በወሳኝ ቁልፍነት፣ (፬) በአስቸኳይነታቸው ፣ እና (፭) የጥምር አጥፉዎቻችንን ትብብር በማዛባት ባለው ፋይዳ እየመዘንን ቅድመተከተል ማስያዝ ቢሞከር ከ፶ በ፻ው በላይ በ፩ኛ ደረጃ ሊቀመጡ የሚችሉ ይሆኑና ግራ ያጋቡናል። ጥቂቱን ልጥቀስና እናንተ ቅደምተከትል አውጡለት:- ፩) ከፋፋይ የዘር ፖለቲካን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ከህግነት፣ ከትምህርትና ከትውልድ አእምሮ መፋቅ፤ ፪) የጎሣ ክልልና አስተዳደር ማፍረስና በዜጎችገንቢ መስተጋብርና ሁለንተናዊ ሰላምና እድገት አመቺነት ብማደራጀት፤ ፫) በባውዳን ፈጣሪነትና ምሁርነትን የተቀቡና የተላላኩነት ሚናቸው ባረከሰው ሰብእናቸው የሐሰት ትርክት በማምረት ማኅበረሰባችንን የመረዙ ሰነዶች፣ በሰነዶቹና ትርክቶቹ አንጻር የተፈጠሩ አደረጃጀቶችና የአስተሳሰብ አሰላለፎችን ማፍረስ፤ ፬) ኦርቶዶክስ ክርስትናን በአሉታዊነት በመሳል የቆመውን ስሕተት በሁሉም ዘርፍ፣ በውስጥም በውጭም ያለውን ሰልፍ ማሸነፍ፤ ፭) በስሑት ርእዮት ሞተርነት፣ በሐሰተኛ ትርክት አቀጣጣይነት፣ በጎሣ ነጻ እውጭ ነን ባዮች፣ በጽንፈኛ ዉሀብያዎች፥ እና የናዚ የየጀርመን ክርስትና ዘር አጥፊ ፕሮቴስታንቶች ቀጥተኛ ፈጻሚነት፣ በብልጽግና ወንጌል የሃይማኖት መንግሥት አመራርና አስተባባሪነት በኦርቶዶክሳውያን ላይ የሚካሄደውን ዘር የማጥፋት ሁለገብ ጥቃት ማስቆም፤ ፮) ላለፉት ፶ ዓመታት በኦርቶዶክስ ክርስቲያን ዜጎች ላይ በመላ ኢትዮጵያ የደረሰውን ጥቃት ቆጥሮና መዝኖ መካስ፣ ማቋቋም፣ አጥቂዎችን ለይቶ ለፍትሕ አደባባይ ማብቃት፤ ፯) በተላላኪ የጌሣ መንግሥታት ተላላነትና ተላላኪነት ምክንያት የተፈረሙ ጎጅ እና አስገዳጅ ስምምነቴች፣ እዳዎች፣ የተፈጠሩ ሁለገብ ጥገኝነቴችን መሻርና ለአገር ዘለቄታዊ ጥቅም በሚውሉበት መንገድ ማስተካከል፤ ፯) የአገሪቷንብየግዛት አንድነትና ዳር ድንበር ዋስትና ባለው መንገድ ማስከበር፤ ፯) በስሑት የተውሶ ፖለቲካዊ ርእዮት እና ሐሰተኛ ትርክት ምክንያት የላላውን የሕዝብ መተማመንና አንድነት መመለስ፤ ፰) አንድ አገራዊ የጋራ ቋንቋ፥ አንድ ዓለም አቀፍ ቋንቋ ውንዲነገርና ትውልድ ሁሉ ሲገናኝ የሚግባባበት፣ የሚማማርበት፣ የሚናገድበት፣ የሚመራመርበት ወጥ ቋንቋ ማንበር፤ ፱) የንዑስ ማንነት ብዝኃነት ከፖለቲካ መሣሪያነት ተወግዶ የልዩ ልዩ ጸጋዎች መጋቢና ወደ ተዋሕዶ የሚያድግበት ሥርዓትና አስተሳሰብ መመለስ፤ ፲) የኢትዮጵያ ትምህርት ዩኒቨርሳል/ሉላዊነትን ከነባርነት ያዋሐደና ከሁለገብ ጥገኝነት በሚያላቅቅ መሠረት ላይ ማቆም፤ ፲፩) እምነቶች ከአገራቸው ወገን የሚገፋፉበትና ከውጭ የኢትዮጵያ አጽራራት ጋር የሚጎዳኙበት ልማድ ፈጽሞ እግድ የሚሆንበት፤ ፲፪) የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን፣ የባህል፣ የኢትዮጵያዊ ሙስሊም ልዩ አገር ፈለቅና ነባር በሁሉ የሕይወት ዘርፎች የሚገኙ ዕውቀቶች ለዘመናዊ ትምህርት ሁሉ በየደረጃው መሠረትና ተመጋጋቢንየሚሆኑበት መዋቅራዊና ሥርዓታዊ አሠራር፤ ፲፫) የአባይ ወንዝ ተጠቃሚ ቤተሰቦች ሁሉ ከሽሚያ የቅኝ ገዥዎች ማኅቀፈ-ዕሳቤ ወደ ስነ ምህዳራዊ የጋራ ልማት ውህደት ገብተው መገፋፋት እንዲያቆሙ ማድረግ ፲፬) የአፍሪቃ ቀንድ የኢኮኖሚና የፖለቲካ ውህደት፣ የአፍሪቃ የተባበረ መንግሥት ምሥረታና የሌሎች አህጉራት ያልተገባ ጣልቃገብነት ማብቃት፤ ፲፭) የአማራን ሕዝብ ለማሳነስ፣ ለመከፋፈል እና ብሎም ለማጥፋት የተተረከው ትርክት፣ የተፈጠረው ሁለገብ አሰላለፍ፣ እና የደረሰውን እየደረሰ የሚገኘው ሁለገብ ጥቃት ዋስትና በሚሰጥ መሠረት ላይ ተፈትቶ እንዲቆም ------ ≠============== በእነዚህ ማስፈንጠሪያዎች ሁሉ ለመወያየት አለሁ። ነገር ግን ዘመኑ የፈጠራችሁ ከሰው አንባ ወደ ጎሣ ቡድን ዕሳቤ እሥረኝነት ያልወረዳችሁ አትምጡ። ባለነጻ አእምሮ ወዳጆቼን ብቻ ነው የጋበዝኩት። ዘረኞችና ተላላኪዎች በነዚህ ገጾች ላይ ብትገኙ የእናንተ ድምጽ ዋጋ ስለማያወጣና ምላሽ ጨካኝ ስለሚሆን እንዳትጎዱ ራሳችሁን አርቁ። 👉 ትዊተር https://x.com/fwakie 👉 ቴሌግራም @Fantahun_Wakie 👉ዩቲዩብ https://www.youtube.com/@Orthodoxy-VS-Secularism 👉https://www.youtube.com/@finoteretuan-2 👉 ፌስ ቡክ. https://www.facebook.com/profile.php?id=61576051634449 👉 https://www.facebook.com/fwakie 👉 ቲክቶክ፡ https://www.tiktok.com/@fantahunwk?_t=8qLqoSRV9Ta&_r=1 👉ብሎግ፡ https://ethiopiaorthodoxchristian.blogspot.com/ ሰላመ እግዚአብሔር አይለየን።ue about the Orthodox Apolostic Church and the Holy Ethiopia

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

የሐሰት ትርክት ኦነጋውያንና የሕወሃታውያ የጋራ ስልት ከነግሥታት ወደ ተራ ግለሰቦች

✏️ እግዚአብሔር ይስጥልኝ።  እርሱ ይመስገን። ምድራችንን #በደም #ያጨቀየው $ህሊና #የነሳን ፣ #ልቦናችንን #ያጨለመን ፣ #ሰብእናችንን ያዋረደው:- 👉 የሕወሐታውያንናንየኦነጋውያን የንዑስ ማንነት የጎሣ ፖለቲካ የደንቆሮ ርእዮትና፣ 👉 መርዛማን ጥላቻን ለ፶ ዘመናት ያከፋፈሉት የሐሰት ትርክት ናቸው። ✏️እንደ ዳግማዊ #ምንልክ ያሉ   ከዋክብት መሪዎች፣ እንደራሴቻቸው፣ ደጃዝማቾችና ቀኝና ግራ አዝማቾቻቸው  ከትውልድ ትውልድ የሚሸጋገር ብዙ ውለታ ውለውልናል:- 👉 በዘመነ ኦቶማንና አውሮፓ፣ በዘመነ መሳፍንት የተበታተነውን እና የተቆነጻጸለውን፣ ጎሠኛ የአርብቶ አደሮች  መሬት ፍለጋ  የደመሰሱትን ክርስቲያናዊ የግዕዝ/የነፃነት ሥልጣኔ አሻራ እንዲያገግም ደክመውልናል፤ 👉 የጥንት አገርን እና ሕዝቦችን   በከፊልም ቢሆን በመሰብሰብ  ጠንካራና ብቸኛ የነጭ ቅኝነትንና ባርነትን በመከላከል፣ ከኦቶማን ቱርክ ወር ትናንት ውስጥ ጥረኛ  አህመድ ግራኝ በመጋደል  ልዩ የነጻነት ማንነት ያላትን አገር ብበቸኝነት በዓለም ካርታንላይ አቆይተዋል፤ 👉 የሬማ ግዛት በጎሣ ተብልቶ ፲ ትንንሽ ሲሆን ከበበባውን ተቋቁማ በዝኃነታችን በተመጋጋቢ አንድነት ከ፹ በላይብቋንቋ፣ ከዓለም ትልልቅ እምነቶች ክትስትናን ፣ ይሁዲን፣ እስልምናን፣ የእረማውያንን ቅሪት የሆኑ የባህል እምነቶችን ሁሉን ይዛ በአውሮፓ በአርብ አምሳል ሳትሠራ ለእኛ አቀብዋል፤ 👉 ወያኔና ኦነግ፣ ገንጣዩ ሻዕብያ፣ ከሃዲው የማርክሲስት የአእምሮ  ባሪያን ስብስብ  እስኪፈትናት ድረስ ራሷን የቻለች አገር እንድንፈጥር ያስተባበሩን ነገስታት የተመሰገኑ ናቸው። አገር ሲያረጅ ጃርት ያብቅላል እንዱሉ: መል...

ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን እና ቋንቋና ማንነት ተኮር እንቅስቃሴዎች

ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን እና ቋንቋና ማንነት ተኮር እንቅስቃሴዎች   ፩. ቋንቋን በተመለከተ ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮና ትውፊት ከሰው ልጅ መበደል በፊት ፍጥረት ሁሉ የሚግባባው በአንድ ቋንቋ ነበር፡፡ “ምድርም ሁሉ በአንድ ቋንቋና በአንድ ንግግር ነበረች” እንዲል፡፡ ዘፍ. 11፡1 በኃጢአት ምክንያት ግን ሰውና መላው ፍጥረት በአንድ ቋንቋ መግባባታቸው ቀረ፡፡ ኃጢአት እየበዛ ሲሄድ የሰው ልጅ ቋንቋም በባቢሎን ተደበላለቀ፣ አንዳቸው ከሌላቸው ጋር የማይግባቡ ብዙ ዓይነት ቋንቋዎችም ተፈጠሩ፡፡  በበደል የመጣውን ሁሉ ሊያስተካክልና ሊያድን በመጣው በአምላካችንና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አዳኝነት ያ የቀደመው ጸጋ ስለ ተመለሰልን በበዐለ ሃምሳ ሰዎች በልዩ ልዩ ቋንቋ አንድ ዐይነት የእግዚአብሔርን መልእክት ሰሙ፡፡ በዚህ ጸጋ የተጠቀሙና የበቁ ቅዱሳን የእንስሳትን ቋንቋ እስከ ማወቅ ደረጃ ይደርሳሉ፡፡   የክርስትና ጉዞ ወደ ቀደመው በአንድ ቋንቋ መግባባት መመለስ ነው፡፡ ወደዚያ ለመድረስ ደግሞ ሰው የእግዚአብሔርን ቃል በሚሰማው ቋንቋ መማር አለበት፡፡ በበዐለ ሃምሳ ጊዜ ለቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስ ብዙ ቋንቋ የገለጠላቸው ሰውን ሁሉ የእግዚአብሔርን የማዳን ጸጋ በሚሰማው ቋንቋ እንዲያስተምሩት ነው፡፡ ሆኖም ቋንቋ መልእክት ማድረሻና መግባቢያ እንጂ ከዚያ ያለፈ ሰዎችን በሆነ መደብ ለመመደብና የልዩነት አጥር ለመሥራት እንደ መሳሪያ ሊሆን አይገባውም፡፡ ይህ ከክርስትና ዐላማ ጋር ተቃራኒ ነው፡፡  ቅዱሳን ሐዋርያት ወደ ዐለም ሁሉ ሲልካቸው ሰዎች የሚቀበሏቸው በሚያስተምሩት ትምህርት መሠረት ነበር እንጂ በትውልድ፣ በብሔርና በመሳሰለው መስፈርት የእኛ ናቸው/አይደሉም በሚል አልነበረም፡፡ የቤተ ክርስቲያን አባቶችን በቋንቋ መ...

ገድሎና አስገድሎ ብፁዕ እየተባሉ መኖር የተፈቀደላቸው ጳጳሳትና ቆሞሳት እንዳይረሱ

ከጥር 27 ጀምሮ በተለያዩ የኦሮምያ ከተሞች በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቀኖና ውጭ የተሾሞና በቅዱስ ሲኖዶስ ተወግዘው የተለዩ አካላትን ወደ ቤተ ክርስቲያን እናስገባለን ባሉ የመንግስት የጽጥታ አካላት በተትኮሰ ጥይትና ሕገ ወጡ ቡድን ባደራጃቸው ወጣቶች ተደብድበው የተገደሉና የቆሰሉ  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ካህናትና ምእመናን።።   1)  ሻሸመኔ ከተማ   I.   የተገደሉ 1.  አያሌው ተረፈ ●   በሻሸመኔ የደብረ አስቦ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ማህደረ ፃድቃን ሰንበት ትምህርት ቤት አባል ●  ጥር 27 ዓ/ም በሻሸመኔ ከተማ በጸጥታ ሃይሉ በሚመራ የጨፍጫፊ ቡድን በደረሰበት ከፍተኛ ደብደባ ወደ ሆስፒታል ገባ ●  በአላቲዮን ሆስፒታል ሕክምና እየተደረገለት ሕይወቱን ማትረፍ አልተቻለም ●  በ ጥር 30 2015 ዓ/ም  ሰማዕትነትን ተቀብሏል       2.  ሊቀ ኅሩያን ቀሲስ ሐረገወይን ●  የሻሸመኔ ደብረ ስብሐት ቅዱስ ሚካኤል አገልጋይ የነበሩት ●  በሻሸመኔ በሕገወጦች በጸጥታ አካላት  በበግፍ በዱላ ተቀጥቅጠው በጭንቅላታቸው በእጅና በእግራቸው ላይ በደረሰባቸው ድብደባ በሀዋሳ ሕክምና እያሉ አርፈዋል። ●  ከመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች በተተኮሰ ጥይት ተመትተው  በያኔት ሆስፒታል ሕክምና ሲደረግላቸው ቢቆዩም ሕይወታቸውን ማትረፍ አልተቻለም። ●  በዛሬው ዕለት ጥር 30 2015 ዓ/ም  ሰማዕትነትን ተቀብለዋል።     3.  ዘማሪ ፍቃዱ ደጉ ●  የቅዱስ ሚካኤል ከሣቴ ብርሃን ሰ/ትቤት አገል...