ወደ ዋና ይዘት ዘለው ይሂዱ

ልጥፎች

ታሞ ከመማቀቅ አስቀድሞ መጠንቀቅ የሚለው የሀገሬ ብሂል የወ/ሮ መዓዛን የኤል ቲቪ ቃለመጠየቅ ተከትሎ ተመላለሰብኝ

ታሞ ከመማቀቅ አስቀድሞ መጠንቀቅ የሚለው የሀገሬ ብሂል   የወ/ሮ መዓዛን የኤል ቲቪ ቃለመጠየቅ ተከትሎ ተመላለሰብኝ፡፡ እንዲሁም የቤተክርስቲያን እና ኢትጵያዊ ምነነትን   በሁሉመ ዘርፍ የመድፈር ሂደት ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱ ታየኝ፡፡ አንዴ በማርክሲዝም፣ ሌላ ጊዜ በፌሚኒዝም፣ ሌላ ጊዜ በካፒታሊዝም፣ ሌላ ጊዜ በተሐድሶ፣ አንዴ …. በስንቱ እንደፈራለን!!!   ይህ ሁለንተናዊ ድፍረት አሳሰበኝ -- እናንተስ? ----የሚያሳስባችሁ ሁሉ የ ዚህ መፍትሔው የክርስቲያኖች ከጥልቅ እንቅልፍ መንቃት ነውና !!!!   ነቅተን በትምህረትና በእውቀት ልዕልና፣ በህግ፣ በጸሎት፣ወዘተ መከላከል መጀመር ነው፡፡ ጊዜ የለንም፡፡ ይህ ካልሆነ ባዕድ አምልኮ፣ ሰዶማዊነት፣ የሰው ልጅ አካል እየበለቱ ለመለዋወጫ መጠቀም፣ አሁን በኢትዮጵየ የተፈቀደው ውረጃ ሰውን መብት ነው እያሉ ራሱን አንዲገድል መፍቀድ፣ ወዘተ ተማርን፣ ሠለለጠንን በሚሉ የሀገራችን ልጆች ጀርባ ተጭኖ   ከምዕራባዊያን   የሚፈሰው የርኩሰት ጎርፍ   ነገ አስገዳጅ ሐገራዊ ሕግ ሆኖ ይቀርብልናል፡፡   ቅድስት ቤተክርስቲያናችን የተደፈረችባቸው ዘርፎች፡ እና የሁላችንንም ጥረትና ተሳትፎ የሚጠይቁ ጉዳዮችን ከማንሳቴ አስቀድሞ በዚህ መልዕክቴ ቤተክርስቲያን ብዬ የምጠራው፡ ----   ክርስቲያን ግለሰብ ሰው፣ ---- የክርስቲያኖች ስብስብ፣ ---ክርስቲያናዊ እምነት ያመነጫቸውና ክርስትና የሚገለጥባቸው   የግልና የማኅበራዊ ኑሮ ዘይቤዎች ማጠበቂያ ማኅበራ ዊ አደረጃጀት ፤ --- ክርስቲያኖች አምልኮ የሚፈጽሙባቸው ቦታዎችና ለአገልግሎት ተለይተው የሚሠሩ ቁሳቁሶች፤ ---የክርስቲያኖች መልዕክት የሚለዋወጡባቸውና አምልኮአቸው...

ይድረስ ለተከበሩ ወ/ሮ መዐዛ አሸናፊ፣ ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት

ይድረስ ለተከበሩ ወ/ሮ መዐዛ አሸናፊ፣   ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት አዲስ አባባ በኤል ቲቪ ከጋዜጠኛ ቤተልሔም ታፈሰ   « የሴቶችን የእርስ በእርስ ጋብቻ ትደግፊያለሽ ?» ተብሎ ለቀረበልዎት ጥያቄ አርስዎ « የሰብአዊ መብት ተከራካሪ እንደመሆኔ ይህን በተመለከተ የራሴ የሆነ አመለካከት አለኝ፤ አሁን ባልመልስልሽ ደስ ይለኛል » ማለትዎን ሰምቼ ትልቅ ሥጋት ውስጥ ወድቅሁ፡፡ መሪዎቻችን ስለምን በእሴቶቻችን መተማመን አልቻሉም? ለምን ያፍሩብናል? ለምንስ የተውሶ ፍልስፍና ተሸክመው ሀገራዊ ማንነታችንን እየተቃወሙ ይመሩናል(ሊነዱን የሚሞክሩት)?   ካፈሩብን የፖለቲካ ሥልጣን የሚየይዙት በድብቅ የሚያምኑበትን ማንነታቸውን ሊያላብሱን ነውን? በሀገራቸው እውቀት፣ በሕዝባቸው እሴትና የሞራል ለከት፣ የእምነትና የባህል ሕግ መመራትን ስለምን ይጸየፉታል? የሚሉ ተከታታይ       ጥያቄዎች አእምሮዬን ወጠሩት፡፡   በእርግጥ የዚህ አይነት ጥያቄዎች ዛሬ በእርስዎ ቃለመጠይቅ ላይ ብቻ የማሰላስላቸውው አይደሉም፣ በአብዛኛው ፖለቲከኞቻችን ችግሮቻችንን ለመፍታት፣ ግቦቻችንን ለማሳካት፣ ርዕዮቻችንን አዉን ለማድረግ የሚመርጡልን መንገዶችን ባሰብሁ ጊዜ ሁሉ ነው፡፡ ግጭት ስለመፍታት፣ ምርት ስለማሳደግ፣ እርሻ ስለማዘመን፣ ትምህርት ስለማሻሻል፣ ፍትህና አስተዳደርን ስለማዘመን፣ ሕግ ስለመደንገግ፣ ስለ እስረኛ አያያዝ፣ ስለ ወታደራዊ ዶክትን፣ ሌብነትን ስለመዋጋት፣ የተፈጥሮ ሀብታችንን ስለመንከባከብ፣ አፈርን ስለማዳበር፣ የሰብልና የእንስሳት ዝርያን ስለመምረጥ፣ ስለመስኖ፣ ስለ ጎሣና ታሪክ፣ ስለ ስነልቡናና ማኅበራዊ ደኅንነት   ወዘተ ባነሱ ቁጥር የሚጠቅሱት የውጭ ሀገራትን...

ኢትዮጵያን እየመራችሁ ላላችሁና ወደፊት ለመምራት የምትፎካከሩ ሁሉ

ኢትዮጵያን እየመራችሁ ላላችሁና ወደፊት ለመምራት የምትፎካከሩ ሁሉ በፖሊሲና በሀሳባችሁ ሁሉ ውስጥ የሚከተለውን ሀሳቤን ብታጤኑ ሀገራችንን ለዘለቁታዊነት የሚጠቅም ይመስለኛል፡ -     አፍሪካን በተፈጥሮ ሀብትና በርካሽ የሰው ኃይል ምንጭነት የሚፈልጉ ሀገራት ሁሉ የኢትዮጵያን መነሳት እጅግ ይፈራሉ፡፡ ስለዚህ ኢትዮጵያና እትዮጵያዊነት   የሚል አስተሳሰብና ለእኛ ለእትዮጵያን ቢሰወርብንም   ታሪካችንን ሲያጠኑ፣ ብራና መጽሐፎቻችንን ሲበረብሩ፣ በእምነት ፍልስፍናችንን የነበረንን ልዕልናና መንፈሳዊ ኩራት ያወቁ፣ መድኃኒት፣ አስትሮኖሚ፣ አስተዳደር፣ ኪነ ጥበብ እንደነበረን የደረሱበት ሁሉ ይሰጋሉ፡፡ ሥጋታቸው አሁን ያለው ትውልድ ወደራሱ ማንነት ማየት ከጀመረ፣ የተሰወረበትን የአባቶቹን ጓዳ ለመመርመር ፊቱን ከጭፍን ግልበጣ ወደ ተረጋጋ ተመራማሪነት ከመለሰ   እስካሁን የሚዘርፉትን ያስቆማል፤ በስደት እየፈሰሰ ጠላቶቹን ከማገልገል ይቆጠባል፤ ከጊዜአዊ ስሜታዊ እርካታ ይልቅ ለትውልድ ማብ ይጀምራ፤ የምዕራባዊያን ጭራና ተከታይነቱን ለውጦ በእኩልን የመኖ አቀም ያዳብራ፤ ሌሎች አፍሪካን በልጠውና ተከታይ አድርገው የመቀጠል እድላቸው ይፈተናል፤ የኢትዮጵያኖ መንፈስ ወደ ሁሉም አፍሪካ ተጋብቶ ራን ለመቻልና ለመተባበር ሀገራትን ያነቃቃል፤ በመሆኑም   ---- ፈጂና ጨፋሪ፣ ገልባጭና አቋራጭ ብልጽግና ፈላጊ ትውልድ ስለሚያጡ ምዕራባዊያን ራዕይህን ለማምከን ሁሉንም ወጥመድ ይዘረጉብሃል፡፡   ሥለዚህ ትልቅ አደጋ ላይ ትወድቃለህ፤ የአንተን ሀሳብ የሚደግፉ ሰዎች፣ ፍልስፍናዎችና እምነቶ ሁሉ አደጋ ላይ ናቸው፡፡ በመሆኑ ጥበብ የተሞላበት አካሄድ ያሻል፡፡ የሰፈራችንን ራ ወዳድ የሆድ ሌ...

በትውልዱ ሥነ ምግባር ላይ የቤተክርስቲያን በዓላት

በትውልዱ ሥነ ምግባር ላይ የቤተክርስቲያን በዓላት ሰመኑን ተደጋግሞ ከጋዜጠኞችና ከፖለቲከኞች የሚነሳ ሁለት ጥያቄዎች አሉ፡፡ ምናልባትም ታላቁን የቤተክርስቲያን በአል የፈጣሪያችን፣የጌታችን፣ የመደድኀኒታችንን ልደት (ገና)ን ምክኒያት በማድረግ ጥያቄው የጎላና የተደጋገመ ይመስላል፡፡ በሌላ በኩል በሀገራችን ያለውን የግጭትና የሰላም መታጣት የሚያስብ ሰው ቤተክርስቲያን ጎልታና በንቃት ለምን አልተሳተፈጭም ከሚልም ይመስላል፡፡ መጠየቁ መልካም ነው፡፡ ነገር ግን ያለ ዳራውና ተጨባጭ ሁኔታውን ያላገናዘብ ምላሽ በመስጠት በቤተክርስቲያን ላይ አሉታዊ ጣት መቀሰር ጤናማ አካሄድ አይደለም፡፡ ስለዚህ የሚከተሉት ጥያቄዎች የሚጠየቁበትና የሚመለሱበትን ተጨባጭ ሁኔታ ማስገንዘብ አስፈላጊ ስለመሰለኝ የግል ምልከታዬን መስጠት ፈለግሁ፡- (1) የቤተክርስቲያን በዓላት አከባበርና አስተምህሮው ለትውልድ ሥነ ምግባር መታነጽ፣ ለሰላምና ለፍቅር መጎልበት ምን አስተዋጽኦ ያድርጋል? (2) የቤተክርስቲያን አባቶች ትውልዱ በሥነ-ምግባር እንዲህ ሲወድቅ ለምን ዘምታን መረጡ? ሥነ ምግባር ከሃይማት አንጻር ሲታይና እምነት የለሽ በሆነ መነጽር ሲታይ ምላሹም ሆነ ዓላማው ይለያያል፡፡ ሃይማኖት ያለው ሰው መልካም ሥራና ጠባይ እንዲኖው የሚፈልገውና የሚረው በዚህ ዓለም በምድር በሚገኝ ጠቀሜታን ብቻ አስልቶ አይደለም፡፡ በተለይ በክርስትና ሥነምግባር የእመነቱ ተግባራዊ መገለጫና ለሰማያዊ ዋጋ ፈለማ ወይንም ቀብድ ነው፡፡ የሥነ ምግባር ምንጩ እሴት ነው፡፡ የእሴት መሠረትና ማህቀፉ ደግሞ እምነት ነው፡፡ እምነት በአስተምህሮና ዶግማ ተቀንብቦ በቀኖና አትርነት የሚኖር፣ ዛሬን ተስፋ በሚያደርጉት ግብ ምክኒያት መወሰን ማለት ነው፡፡ የእምነት ትርጉም በፈጣሪና በፍጡር መካከል ያለውን አንድነት ማስጠበቂያ...