=========================================
ስማዕታቱ የዚህን የምክክር ኮሚሽንና የአብይን የምድር ላይ #ሽፍጥ ይታዘባሉ!! ወደ እግዚአብሔርም እንዲህ እያሉ ይካሰሳሉ፦
"ሁሉን የምትገዛ ቅዱስና እውነተኛ ጌታ ሆይ፤ እስከ መቼ አትፈርድም? እስከ መቼስ ደማችንን በምድር በሚኖሩት ላይ አትበቀልም?" (ራእይ ዮሓንስ 6፡10)
===============================================
ግልጽ መልስ የሚሆነው፦ የ50 ዓመታት መርዛማ የሐሰት ትርክትን ከፍ በማድረግ የሚከተሉትን የሕወሃትና የኦነግ፣ ኋላም ብልጽግና የተረከባቸውን ግቦች እንዲሳኩ ሕጋዊ ሽፋን መስጠት ነው፦
(1) በሕወሃት፣ በኦነግ፣ ብጽንፈኛ ዉሃብያዎች፣ በአድዋ ቁስለኛ ወራሪዎች ደብዛው እንዲጠፋ ከ50 ዓመታት በላይ የተዘተመበትን ኢትዮጵያዊነት፣ ነባር የስነ-መንግሥት እና የሕዝብ ታሪክ፣ በተለይ ኦርቶዶክሳዊነት እና አማራ የተባለውን ክፍለ-ሕዝብና የእርሱን እሤቶች የሚካሩ ነገዶች ሁሉ ላይ የሚካሄደውን ጥቃት ሕጋዊ ማድረግ፤
(2) የኢትዮጵያን ታሪክ በኦነጋዊ የ150 አመታት ትርክት፣ "የአገር ባለቤትነት" ጥያቄ በሚል ሽፋን ሌላውን አገርና ታሪካ የማሳጣት ነውረኛ እና ኢሰባዊ ፋሽስታዊ ዘመቻ፣ ዘር የማጽዳት ሙከራዎችን ሕጋዊ ማድረግ፤
(3) በአብይ አህመድ ስሌት፣ በሕወሃት የ50 ዓመታት ድካም፣ በሮማኖ ቻውስካን እና ሄንሪ ኪሲንጀር ኢትዮጵያን የማጥፋት ምክር መሠረት ኢትዮጵያን ወደ ትናንሽ አገር ለመክፋፈል ቀላል እንዲሆን ሕዝብን የምታስተሳስር፣ ታሪክን ሰንዳ ያኖረች፣ ኢትዮጵያዊ ስበናና ማኅበረሰብ የገንባት ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያንን አገራዊ ሚና ማሣጣት፤
(4) አማራን መምታት፣
(5) ጽንፈኞችን በነባር እስልምና ላይ ማንገሥ ኢትዮጵያን አረባዊ ማድረግ፣
(6) ታላላቅ የሚባሉ የትግራይና የኦሮምያ ሪፐብሊኮችን ለመመሥረት የጋራ ምልክቶችን "ከነጠላ ትርክት ወደ ህብረ-ትርክት" ማሻገር በሚል የጎሣ ፖለቲካኞች ስንኩል እና አፍራሽ የባዕድ ሤራ ማስፈጸሚያ ፖለቲካ ቀመር መሠረት ኢትዮጵያን የማጥፋቱን ሂደት ሕጋዊ ማድረግ፤
(7) ከ30 ዓመታት የወያኔ-ኦፒዲኦ/ኢሓዴግ የዘር ማጥፋት ፕሮጄክት ቀጣይ የሆነውን የብልጽግና መንግሥት ወንጀል ለማደባበስና ሂደቱን ሕጋዊ ለማድረግ --- ናቸው።
በአጭሩ፦
ምክክሩ ለኢትዮጵያ ሰላም፣ ልሕዝቦቿ ውሕደት፣ ለጠፋው ታሪክ እርምት፣ ለተፈጸምው ግፍና እልቂት ፍትሕና ካሳ፣ ለተፈናቀልው መልሶ መቋቋም አያመጣም። በአንጻሩ የሕወሃት እና የኦነጋውያንን አገር የማፍረስ ሂደታዊ እድገት አዲስ ደረጃ ነው። በአምጽና በየድርጅቱ የደረግ የነበረውን አገር አገር የማፍርስ ፕሮጄክ መንግሥታዊና ሕጋዊ ማኅቀፍ ከመሥጠት አያልፍም።
አጀንዳዎችን ስንመለከትና ተሳታፊዎቹን ራስ ገዝነትና በህሊና የመመራት ሁኔታ አጠራጣሪ መሆኑ፣ በአብይ ቁጥጥር ሥር መሆኑ የክርስቲያን ዘር የማጥፋት ግቡ አገር አፍርሶ የትግራይና የኦሮምያ ሪፐብሊኮችን የመፍጠር የሂደት አንጓ ነው።
አጀንዳዎቹ በሙሉ ያለንበትን መከራና የጎሣ ነጻ አውጭዎችን፣ የጽንፈኞችን ትርክትና ድምጽ የተሸክም እንጂ የኢትዮጵያን ሕዝብ በተለይ ኦርቶዶክሳውያንን አይመለከትም ብቻ ሳይሆን ጎጂሽቸው እንደሚሆን አያስጠርጥርም።
የሐሰት ትርክትን የ የአብይ አህመድና የጽንፈኛ ዉሀብያን ፍላጎቶችን እንደ ድሪቶ ከምሮ "አገራዊ አጀንዳ" በሚል ከሰው ልጆች ውርደትና እልቂት፣ ከታሪክ ድለዛና ቀጣይ የመጠፋፋት ብልጽግናዊ ሴራ የከፋና ወንጀልን የመቀደስ፤ ፍተሕን የመቅበርና ወንጀለኛ ተቋማትን የማንጻት የክፋት ሁሉ ቁንጮ ነው።
ኦርቶዶክሳዊውን ማኅበረሰብ የሚወክል በሌለበት፣ በኦርቶዶክስ ስም በግል የሕይወት ስብራትና ነውር የሚሳቀቁ፣ መንግሥት መረጃ ይዞባቸው እንደ እቃ የሚጫወትባቸው፤ በጸራራ ፀሐይ በጅምላ የተጨፈጭፉ የጥምቀት ልጆችን እንኳ መረጃ ለመዘገብ እና ለዓለም ለማጋለጥ እምቢኝ ያሉ የወንጀለኛ ተባባሪ ሙሰኞች፣ እውነትን የሚፈሩ የሐሰት መኖኮሳትና ጳጳሳት በምክክሩ ውስጥ መጎለት ውጤቱ አደገኛ ነው።
እየተካሄደ ያለው ክርስቲያንን በሁለንተናው የማሳነስ ከተቻለ የማጥፋት መንግሥታዊ ወንጀል ሳይሞግትና አጀንዳ አድርጎ ሳያቀርብ ጠላቶቹ በቀመሩት አጀንዳ ዙሪያ እንደ ጥምብ አንሳ መሥፈር የካባና የወርቅ ሽልማት ለወንጀለኞችና ታሪክ ሸቃጭ ቁማርተኞች እያድለ ቅዱስ ገጽታ ሲሰጥ ከኖሩ ሰዎች ምን ይጠብቃል? መሳተፋቸው በግልጽ ሞታችንና ስደታችንን፣ የታሪካችን በሐሰት መጠልሸትና ከአንድ እንደ ጠላት ተፈርጆ ከሚጠቃው የማርኛ ተናጋሪ ክፍለ-ሕዝብ ጋር በማቆራኘት አብሮ ሁለቱንም ሲያጠቃ የኖረ ሥርዓት፣ ሕገ መንግሥቱን እከላከላልሁ በሎ ፕሪቶሪያ ድርስ አሜሪካንን ጋብዞ በአንድ አገር ሕዝቦች መካክለ ወርዳና አውራጃ የሚያቃርጥ፣ ሕግ አስከብራለሁ ብሎ ከአርበ መግደያ እየተዋሰ ፍጅት ከሚፈጽም መሪጋ ተባብሮ ቀኖና ሐዋርያትን ከሚሽር ቡድን የኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች አጀንዳ እና የቤተ ክርስቲያን ፍላጎት ውክልና ያገኛል ብሎ መጠበቅ አላዋቂነት ብቻ ሳይሆን ከቁም ሬሶች ብቻ የሚጠበቅ ነው።
ተሳትፎው እንደተለመደው በጅምላ የሚገደለውን ክስቲያን ለሚብስ እልቂት አደንዝዞ እና አፈሰዝዞ በባዶ ተስፋ ማቆየት ይሆናል።
ይህን የሁላችንንም ሽፍጥና አድርባይነት፦
እኛ በአካለ-ሥጋ የቆምነው ነገር ግን ከክርስትና ከመራቃችን የተነሳ ለእውነት ክርስቶስ፣ ለቤተ ክርስቲያን ልዕልና፣ ለፍተህ እና ለክብረ ሰብእ መሟገት ብንፈራም በእምነት ጸንተው ሰማዕት የሆኑት የአርሲ፣ የወለጋ፣ የከሚሴ፣ የሐረርጌ፣ የጅማ፣ የባሌ፣ የኦጋዴን፣ የጉምዝ ሰማዕታት ከላይ ሆነው ይፋረዳሉ።
እውነትን በድግስና በፕሮፓጋንዳ መቅበር አይቻልም።
እውነተኛ ምክክር እና እውነተኛ ተወካይ ቢኖረን ኖሮ የሚከተሉትን ቁልፍ አጀንዳዎች ከማያነሳ የምክክር ኮምሽንና ጉባኤ ጋር የሚተባበር ቤት ክህነትና ሲኖዶስ አይኖርም ነበር ብቻ ሳይሆን ኦርቶዶክሳውያን አንድ ሆነው እንዲቃወሙት ጥሪ ያስተላልፋል፣ ለዓለም ማኅበረ ስብም ይህንን አዲስ የአደጋ መንገድ ያጋልጣል፦
(1) ታሪከን የሚመልከት አጀንዳ፦
(2) ርስትን በሚመለከት፦
(3) ፍትሕን በሚመልከት፦
የአገራዊ ምክክር አጀንዳዎች ተጠቃለው የፒዲኦ/ብልጽግናና የጽንፈኛ ዉሃብያ የጋራ አጀንዳ አለምሆናቸውን፣ ሌላውንም ወገን ማካተታቸውን ይመስክር ነበር። አሁን ግን እኛ የለንበትም።
(ፋንታሁን ዋቄ)


አስተያየቶች
አስተያየት ይለጥፉ