ወደ ዋና ይዘት ዘለው ይሂዱ

መንግሥት የማይሳተፍበት የዘር ማጥፋት ሙከራ በዓለም ታሪክ አለተመዘገበም --- የኛም ጥፋት የሚመራው በአብይ መንግሥት ነው!

 የዘር ማጥፋት ሙከራዎችና ተግባራት 100% ለማለት በሚያስድፍር ደረጃ የሚካሄዱት በመንግሥት ነው!!!

(ክፍል 2)
በአንድ አገር ውስጥ መንግሥት፣ በተለይ ዋና መሪው የማይሳተፍበት የዘ ማጥፋት ድርጊት ተከናውኖ አያውቅም። ላለፉት 38 ዓመታት፣ በተለይ ባልፉት የብልጽግና አገዛዝ ተከታታይነት ያለው ጥፋት ሁሉ የ #አብይ #አህመድ ቀጥተኛና ተዘዋዋሪ ትዕዛዝ የተፈጸሙ ናቸው።
#ሕወሃት እንኳ የፈጸማቸው ወንጀሎች በአብይ አህመድ እወቅናና ሤራ የሐውሃትን ነባር ሰይጣናዊ ዝንባሌዎችን በማነቃቃት የተከናወኑ ናቸው።
ማስረጃ፦
ዘር ማጥፋት የመንግሥትን ቀጥተኛ እና ተዘዋዋሪ ተሳትፎ የሚፈለግባቸው ዋናዎቹ ምክንያቶች፣ ድርጊቱ በዕለት ታስቦ፣ ተደራጅቶ የሚፈጸም ሳይሆን ዓመታትን የሚፍጅ ዝግጅት የሚጠይቅ፣ ትርክት፣ ርእዮት፣ መዋቅርና አቅም የሚጠይቅ በምሆኑ ነው።
ግጭት ሲሆን በንድ ውቅትና ጉዳይ ዙሪያ የሚጋጩ ሁለት አካላት በመንደር ወይንም በቀበሌ ጊዜአዊ እና ስሜታዊ ጉዳይ ላይ ተጋጨተው በመንግሥት፣ በሃይማኖትና በባህል ጣልቃ ገብነት ያበቃል። የሐውሃትና የኦነግ ትርክትና ርእዮት መንግስታዊ ሕግና ፖሊሲ በመሆኑ በአንድ መንደር ሳይሆን በመላው አገሪቱ 38 ዓመታት ያልተቋረጠ በኦርቶዶክሳውያን ላይ እልቂት እየተፈጸመ ምሆኑ ድርጊቱ መንግሥታዊ መሆኑን ያረጋግጣል።
መፈናቀሉ፣ መገደሉና የታሪክ መጠልሽቱ፣ ዒላማ የተደረገውን ወገን በተለያዩ ስያሜዎች፣ በተልይ በማራና ነፍጠኛ ሽፍኖ ማጥፋቱ መንግሥታዊ መሆኑ የክልል ሕጎች፣ የባለሥልያናት ንግግሮች፣ መንግሥታዊ መዋቅን ሥልያን ድልድል፣ የፍትሕ መታጣትና የታቀደ ድኽነትን በዘውግ የመፍጠር ድርጊት ሙሉ በሙሉ መንግሥታዊ ነው።
ዘር ማጥፋት በጠባቡ ሲተረጎም ፡- በትከታታይነት በጅምላ መግደል እና ፍትሕ መንፈግ ፣ በተከታታይነት በጀምላ ማፈናቀልና መልሶ አለማቋቋም፣ በስልት ሴቶችን መድፈርና ተዳር መበተን፣ ቋንቋና ባህል ማዳከም፣ ከሃይማኖት ማፍልስ፣ ባህል መደምሰስ፣ በጅምላ ማሠር፣ ሕጻናታትን ከማንነታቸው አውጥቶ የሌሎች ማድረግ፣ ማምከን፣ ማደኸየት፣ በሥራ ስም በባርነት ሰዎችን ከአግር ማስወጣትን ሁሉ ይጨምራል።
ይህን ለማድረግ የግድ፡
1) የፍጅት መሣሪያና ሎጂስቲችስ ማሟላት (መንግሥት መሆንን የጠይቃል) ፤
2) በመንግሥት ቢሮክራሲ ቅንጅት ለመፈጠር አካባቢን በአስተዳድር ክልል አዋቅሮ ባለቤት የሆነ ዚጋና ያልሆነ፣ ልዩ ጥቅም የሚገባውና የማይገባው ብሎ መክፍለ (መንግሥታዊ ሥልጣን የጠይቃል)፤
3) እንዲጥፉ የተፈረደባቸው ወገኖችን ራስን የመከላከል አቅም መንሳት፣ ማምለጫና ለዓለም የሚናገሩበትን መንገዶች መዝጋት (ይህ መነግሥታዊ ሥልጣን የጠይቃል)፤
4) የውጭ ኃይሎች ጣልቃ ገብነትና መከላከልን የማገድ አቅም (ይህ መንግሥት መሆንን የጠይቃል)፤
5) ወንጀሉ በብዚኃን መገናኛ እንዳይነግር፣ ተቃዋሚዎች እና ፓርላማ አጀንዳ እንዳያደርጋቸው ማገደ (ይህ የምንግሥት ሥልጣንን መቆጣጠር የጠይቃል)
6) የአግሪቷ መከላከያ፣ ፖሊሲና የፍትሕ መዋቅሩ ስለሚጨፈጭፉና ስልሚጎዱ ወገኖች ተቃውሞ ሳይሆን ቀጥተኛ ተሳታፊ በመሆን የዘር ማጥፋት ማስፈጸሚያ መሆን አለባቸው (ይህም መንግሥት መሆንን የጠይቃል) ----
---- እንዚህ 6 ሁኔታዎች ሳይሟሉ እንኳንስ 30 + 8 ዓመታት ለ8 ሳምንታትም ሰውን መጨፍጨፍና ማፈናቀል አይቻልም።
--- ስለዚህ
ኢትዮጵያ ውስጥ በኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ላይ የሚካሄደው ሁለገብ የዘር ማጥፋት የሚካሄውደ ቀድሞ በሕወሃት/ኢሕአዴግ ነበር፣ አሁኑ ብ #አብይ #አህመድ አሊ መንግሥት ቀጥተኛ አመራር ነው ነው ለማለት የሚከለክል ምንም መከራከሪያ የለም።
ከዓለም ታሪካ የዘር ማጥፋት ሙከራዎች የሚጠቀሱ ማስረጃዎችን እንመልከት፦
1) በአይሁን ላይ በናዚ ጀርመን የተፈጸመው ዘር የማጥፋት ዘርፈ በዙ ሙከራዎቸ፦
የናዚዋ ጀርመን አይሁድን፣ ሮማዎችንና ሌሎችን ከሰውነት የወረዱ ዘርያዎች በለው የሰየሟቸውን ወገኖች ለማጥፋት የተጠቀሙት የሚሎታርይ፣ የፖሊስ፣ የደኅንነት፣ የባቡር ትራንስፖርት፣ የኬሚካል ካምፓኒዎችን፣ የፕሮፓጋንዳ ተቋሟትን በማቀናጀት ነው። ስለዚህ ዘር ማጥፋቱ መንግሥታዊ ነው።
2) በ1915 (እ.አ.አ) የተፈጸመውና ዛሬም ደርስ በረቂቅ መንገድና በፖልቲካ የሚካሄደው የአርመን ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ዘር የማጥፋት የኦቶማን ቱርክ ድርጊት የተከናወነው በእስላማዊ መንግሥት ነው። የኦቶማን መንግሥት የጅምላ ማፈናቀልና ማባረር፣ የጅምላ ግድያ ሰልፈኞችን ማዘጋጀትና አርመን ክርስቲያኖችን መጨፍጭፍ መርቷል። ስለዚህ ዘር ማጥፋቱ መንግሥታዊ ነው።
3) በ1994 (እ.አ.አ) በሩዋንዳ የተካሄደው ዘር የማጥፋት ሙከራ በሁቱዎች በሚመራ መንግሥታዊ ራዲዮ ቀስቃሽነትና በመንግሥት መዋቅር ድጋፍ ነበር። ሚሊሺያዎች፣ ሚዲያ፣ በየሽካባቢው (ወረዳና ቀበሌ) መዋቅራትን የሚመሩ ባለሥልጣናት (እንደ ኦሮምያ ምንግሥታዊ መዋቅር ማለት ነው) ቅንጅት ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ቱትሲዎች ተጭፍጭፍዋል። ሩዋናዳና ሰላም ከተመለሰ በኋላ ይህን የመሩ የመንግሥት ባለሥልጣናትን ለዓለም ዐቀፍ ቲሪዩቡናል አቅርባለች።
4) በ1995 ምዕራባውያን የተዛባ ጣልቃ ገብነትና በጽንፈኞቹ ፖለቲካዊ የአልቃይዳ መንፈስ ወራስ ሙስሊሞች በክርስቲያኖች ላይ በተጀምረ ጥቃት እና ምላሽ የቦስንያ ሰርብ 8,000 ቦስኒአክ ሰርቤኒካ እልቂት ተፍጥሟል። በሌላው በኩል መረጃ እንዳይኖር የሚፈልጉት የውጭ ጣልቃ ገቢ ተዋንያን ትርክቱን አዛብተው የአንዱን ወግን ብቻ ተረክዋል። ይህ በኢትዮጵያ በጣልያን የተፈጸመው የአማራና የኦርቶዶክስ ዘርን የማጥፋት ሙከራ እንዳይዘገ እንደሞከሩትና በእግዚአብሔር ፈቃድ በኢያን ካምፕቤል ባልፈው 5 ዓመት ቅንጭብ መርጃ ከታተመው ( https://a.co/d/0ezXTW79 ) ውጭ። በሰርቢያ ክርስቲያኖች ላይ የተደፈደፈው ክስ የሚያነሳው ስሎቦዳን ሚሎስቪች የመራው ሚሊታሪ ላይ ሲሆን ሌላውን ወገንና የውጭን ሚና ድብቆታል። ያም ሆን ይህ በጅምላ ያለቁት ሰርቦች በመዋቅር መሆኑ እንረዳለን።
ማጠቃለያ
ዘር ማጥፋት ያለ ምንግሥት ተሳትፎ ሊከወን ይችላልን? አገር ባልፈረሰብት፣ መንግሥት መዋቅራትን በሚቆጣጠርበት ሁኔታ ሁሉ ያለ መንግሥት ፈቃድ፣ ተሳትፎና መሪነት የዘር ማጥፋት ሙከራ ፈጽሞ ሊካሄድ አይችልም ነው።
በእርግጥ አንድ ግለሰብ፣ ወይንም ቡድን የዘር ማጥፋት ሀሳብና ሙከራ እንዲጀመር ቅስቀሳ ሊሠራ የችላል። በኢትዮጵያ ተጨባጭ ሁኔታ ሕወሃትና ኦነግ መንግሥት እንስኪሆኑ ድርስ ትርክትና ቅስቀሳ አድርገዋል።
መንግሥትነት እጃቸው ሲገባ ውለው ሳያድሩ ዘር ማጥፋቱን ከሐረርጌ እስከ አርሲ ብቻ ሳይሆን በማራ ክልል ውስጥም በመሠረተ ልማት አድልዎ፣ ወሊድን በመቅነስና በማምከን፣ የውባ ወረርሽኝና በሽታ እንዲስፋፋ በማድረግ፣ በጦርነቶች ሆን ብሎ ከፊት በመማገድ፣ በማደኸይት፣ ከትምህርትና ከኢኮኖሚ እደገት ውጭ በማደረግ፣ እርስ በርስ የሚያጋጩ ሁኔታዎችን በመፍጠር፣ ርስትን በጎሣ በመደልደልና አምራና ኦርቶዶክሳውያንን በሚጎዳ መንግደ በመከለል፣ የራሱ መሪዎች እንዳይኖሩት በማድረግ፣ የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያንን ከእውነተኛ የመነቱ አባቶች እጅ በማስወጣት በካድሬና ሕሰተኛ አባቶች በመሙላት፣ የጀመሩትን ሂድት የበልጽግና መንግሥት በቀጥታ በመደበኛ ሠራዊትና ታጣቂዎች የጅምላ ፍጅትና ማፈናቀል ውስጥ መግባቱ መንግሥታዊነቱን ያረጋግጣል።
ይህ ጠንካራ ማሰርጃና አሳማኝ እንዲሆን የሚያደርገው ዘር ማጥፋት ሂድት ተጀምሮ ከሳምንታት በላይ እንዲቀጥል የሚያደርገው አድራጊው፡
1) በመንግሥት ደርጃ ማቀደ ሲችል፤
2) የመንግሥት መከላከያ፣ የፖሊስ ፣ ሚሊሻና ልዩ ልዩ በምንግሥት መዋቅር ሥር የሚተዳደሩ እና በተዘዋዋሪ የሚደግፉ የተደራጁ አካላት ሲሳተፉበት፣
3) በጀትና ፕሮፓጋንዳዊ የማያቋርጥ ሆኖ ሲቅጥልና በተቃራኒዊ ያለው ተጠቂ ወገን መናገር፣ መጻፍና መደራጀት፣ መታጠቅና ለትርክቱ መቆም ሲከለክለ፣
4) መንግሥት ተጠቂዎችን ለመከላከልና ዋስትና ለምስጠት ዳተኛ ሲሆን (እንደ #አብይ #አህመድ በደባባይ "እኔ ሚኒሻ አይደለሁም ስለ ሞታችሁ አትጠይቁኝ፣ ገና ወደፊት ሞት የቀጥላል፣ በሬሳችሁ ላይ ችግኝ እተክላልሁ፣ ገዳማት የነፍሰ ገዳይ ማሰልጠኛ ናቸው፣ በአርሲ ኦርቶዶክስ ብቻ ስላልሞት ፍትሕ አትጠይቁኝ፣ በሰብሪን ቦታ ሰበርናቸው፣ የቀድሞ ሥራዓት ናፋቂዎች ናችሁ፣ ወዘተ." ግልጽ አቋም በመያዝ ከንግግር ወደ ተጋባራዊ ዘመቻ መግባት)፤
--- ሲተባብሩ ስለሆነ መንግሥት የማይሳተፍበት ዘር የማጥፋት ሙከራ በአንድ አገር ውስት ሊኖር አይችልም። በተለይ ሕወሃትና ኦነግ ኦሮሙማ ለ38 ዓመታት በኦርቶዶክስ ክርስትናና በአማርኛ ተናጋሪዎች ላይ የጀመሩት ዘር የማጥፋት ሙከራ ሙሉ በሙሉ መንግሥታዊ፣ መዋቅራዊና ሥርዓታዊ ነው።
ይህን አሁን በኢትዮጵያ የሚካሄደውን ሁለገብ የዘር ማጥፋት መንግሥታዊ ፕሮጄክት ለማስቆም ጤናም ሰብእና ያለን፣ ፈጣሪ በሌላ ፈጡር በሆነ ሰው እጅ ሰውን ያድናል እንጂ አይገድልም የሚለ የሃይማኖት አስተምህሮ ያለን፣ ፍትሕ ትርጉሙ የሚገባን፣ ነውርና አውሬነትን የምንጸየፍ፣ ሐሰትና ስግብግብነትን የመንጠላ ሁላችን --- በሃይማኖት፣ በቋንቋና በትርክት ከፋፍሎ ለሚያፋጀን መንግሥት መሣሪያ ሳንሆን ህልውናችንን፣ አገራችንን፣ ታሪካችንን፣ እውነታችንን፣ ሰባዊ ክብራችንን ለማስመለስ የድርሻችንን እንወጣ!!!



አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

የሐሰት ትርክት ኦነጋውያንና የሕወሃታውያ የጋራ ስልት ከነግሥታት ወደ ተራ ግለሰቦች

✏️ እግዚአብሔር ይስጥልኝ።  እርሱ ይመስገን። ምድራችንን #በደም #ያጨቀየው $ህሊና #የነሳን ፣ #ልቦናችንን #ያጨለመን ፣ #ሰብእናችንን ያዋረደው:- 👉 የሕወሐታውያንናንየኦነጋውያን የንዑስ ማንነት የጎሣ ፖለቲካ የደንቆሮ ርእዮትና፣ 👉 መርዛማን ጥላቻን ለ፶ ዘመናት ያከፋፈሉት የሐሰት ትርክት ናቸው። ✏️እንደ ዳግማዊ #ምንልክ ያሉ   ከዋክብት መሪዎች፣ እንደራሴቻቸው፣ ደጃዝማቾችና ቀኝና ግራ አዝማቾቻቸው  ከትውልድ ትውልድ የሚሸጋገር ብዙ ውለታ ውለውልናል:- 👉 በዘመነ ኦቶማንና አውሮፓ፣ በዘመነ መሳፍንት የተበታተነውን እና የተቆነጻጸለውን፣ ጎሠኛ የአርብቶ አደሮች  መሬት ፍለጋ  የደመሰሱትን ክርስቲያናዊ የግዕዝ/የነፃነት ሥልጣኔ አሻራ እንዲያገግም ደክመውልናል፤ 👉 የጥንት አገርን እና ሕዝቦችን   በከፊልም ቢሆን በመሰብሰብ  ጠንካራና ብቸኛ የነጭ ቅኝነትንና ባርነትን በመከላከል፣ ከኦቶማን ቱርክ ወር ትናንት ውስጥ ጥረኛ  አህመድ ግራኝ በመጋደል  ልዩ የነጻነት ማንነት ያላትን አገር ብበቸኝነት በዓለም ካርታንላይ አቆይተዋል፤ 👉 የሬማ ግዛት በጎሣ ተብልቶ ፲ ትንንሽ ሲሆን ከበበባውን ተቋቁማ በዝኃነታችን በተመጋጋቢ አንድነት ከ፹ በላይብቋንቋ፣ ከዓለም ትልልቅ እምነቶች ክትስትናን ፣ ይሁዲን፣ እስልምናን፣ የእረማውያንን ቅሪት የሆኑ የባህል እምነቶችን ሁሉን ይዛ በአውሮፓ በአርብ አምሳል ሳትሠራ ለእኛ አቀብዋል፤ 👉 ወያኔና ኦነግ፣ ገንጣዩ ሻዕብያ፣ ከሃዲው የማርክሲስት የአእምሮ  ባሪያን ስብስብ  እስኪፈትናት ድረስ ራሷን የቻለች አገር እንድንፈጥር ያስተባበሩን ነገስታት የተመሰገኑ ናቸው። አገር ሲያረጅ ጃርት ያብቅላል እንዱሉ: መል...

ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን እና ቋንቋና ማንነት ተኮር እንቅስቃሴዎች

ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን እና ቋንቋና ማንነት ተኮር እንቅስቃሴዎች   ፩. ቋንቋን በተመለከተ ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮና ትውፊት ከሰው ልጅ መበደል በፊት ፍጥረት ሁሉ የሚግባባው በአንድ ቋንቋ ነበር፡፡ “ምድርም ሁሉ በአንድ ቋንቋና በአንድ ንግግር ነበረች” እንዲል፡፡ ዘፍ. 11፡1 በኃጢአት ምክንያት ግን ሰውና መላው ፍጥረት በአንድ ቋንቋ መግባባታቸው ቀረ፡፡ ኃጢአት እየበዛ ሲሄድ የሰው ልጅ ቋንቋም በባቢሎን ተደበላለቀ፣ አንዳቸው ከሌላቸው ጋር የማይግባቡ ብዙ ዓይነት ቋንቋዎችም ተፈጠሩ፡፡  በበደል የመጣውን ሁሉ ሊያስተካክልና ሊያድን በመጣው በአምላካችንና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አዳኝነት ያ የቀደመው ጸጋ ስለ ተመለሰልን በበዐለ ሃምሳ ሰዎች በልዩ ልዩ ቋንቋ አንድ ዐይነት የእግዚአብሔርን መልእክት ሰሙ፡፡ በዚህ ጸጋ የተጠቀሙና የበቁ ቅዱሳን የእንስሳትን ቋንቋ እስከ ማወቅ ደረጃ ይደርሳሉ፡፡   የክርስትና ጉዞ ወደ ቀደመው በአንድ ቋንቋ መግባባት መመለስ ነው፡፡ ወደዚያ ለመድረስ ደግሞ ሰው የእግዚአብሔርን ቃል በሚሰማው ቋንቋ መማር አለበት፡፡ በበዐለ ሃምሳ ጊዜ ለቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስ ብዙ ቋንቋ የገለጠላቸው ሰውን ሁሉ የእግዚአብሔርን የማዳን ጸጋ በሚሰማው ቋንቋ እንዲያስተምሩት ነው፡፡ ሆኖም ቋንቋ መልእክት ማድረሻና መግባቢያ እንጂ ከዚያ ያለፈ ሰዎችን በሆነ መደብ ለመመደብና የልዩነት አጥር ለመሥራት እንደ መሳሪያ ሊሆን አይገባውም፡፡ ይህ ከክርስትና ዐላማ ጋር ተቃራኒ ነው፡፡  ቅዱሳን ሐዋርያት ወደ ዐለም ሁሉ ሲልካቸው ሰዎች የሚቀበሏቸው በሚያስተምሩት ትምህርት መሠረት ነበር እንጂ በትውልድ፣ በብሔርና በመሳሰለው መስፈርት የእኛ ናቸው/አይደሉም በሚል አልነበረም፡፡ የቤተ ክርስቲያን አባቶችን በቋንቋ መ...

ገድሎና አስገድሎ ብፁዕ እየተባሉ መኖር የተፈቀደላቸው ጳጳሳትና ቆሞሳት እንዳይረሱ

ከጥር 27 ጀምሮ በተለያዩ የኦሮምያ ከተሞች በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቀኖና ውጭ የተሾሞና በቅዱስ ሲኖዶስ ተወግዘው የተለዩ አካላትን ወደ ቤተ ክርስቲያን እናስገባለን ባሉ የመንግስት የጽጥታ አካላት በተትኮሰ ጥይትና ሕገ ወጡ ቡድን ባደራጃቸው ወጣቶች ተደብድበው የተገደሉና የቆሰሉ  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ካህናትና ምእመናን።።   1)  ሻሸመኔ ከተማ   I.   የተገደሉ 1.  አያሌው ተረፈ ●   በሻሸመኔ የደብረ አስቦ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ማህደረ ፃድቃን ሰንበት ትምህርት ቤት አባል ●  ጥር 27 ዓ/ም በሻሸመኔ ከተማ በጸጥታ ሃይሉ በሚመራ የጨፍጫፊ ቡድን በደረሰበት ከፍተኛ ደብደባ ወደ ሆስፒታል ገባ ●  በአላቲዮን ሆስፒታል ሕክምና እየተደረገለት ሕይወቱን ማትረፍ አልተቻለም ●  በ ጥር 30 2015 ዓ/ም  ሰማዕትነትን ተቀብሏል       2.  ሊቀ ኅሩያን ቀሲስ ሐረገወይን ●  የሻሸመኔ ደብረ ስብሐት ቅዱስ ሚካኤል አገልጋይ የነበሩት ●  በሻሸመኔ በሕገወጦች በጸጥታ አካላት  በበግፍ በዱላ ተቀጥቅጠው በጭንቅላታቸው በእጅና በእግራቸው ላይ በደረሰባቸው ድብደባ በሀዋሳ ሕክምና እያሉ አርፈዋል። ●  ከመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች በተተኮሰ ጥይት ተመትተው  በያኔት ሆስፒታል ሕክምና ሲደረግላቸው ቢቆዩም ሕይወታቸውን ማትረፍ አልተቻለም። ●  በዛሬው ዕለት ጥር 30 2015 ዓ/ም  ሰማዕትነትን ተቀብለዋል።     3.  ዘማሪ ፍቃዱ ደጉ ●  የቅዱስ ሚካኤል ከሣቴ ብርሃን ሰ/ትቤት አገል...