ወደ ዋና ይዘት ዘለው ይሂዱ

ልጥፎች

ከ2025 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ኢትዮጵያን የሚመጥን መሪ ለመፍጠር መስፈርት ላይ ሀሳብ እናዋጣ!

ኢትዮጵያን የሚመጥን መሪ ለመፍጠር መስፈርት ላይ ሀሳብ እናዋጣ! በሰው ደም ካልታጠቡ፣ በዜጎች ዕንባ ካልዋኙ አየር የተነፈሱ የማይመስላቸው  ድውያነ አእምሮ፣ የክፋት አበጋዞች፣ የሐሰት ምንጮች፣ የሤራ መሀንዲሶች እና የቁማር ሱሰኞች ዳግም እንዳይነዱን ከፈለግን ከጭፍን መንጋነትንወጥተን እናስብ!!! እኔ ለማስጀመር እንዱህ ብያለሁ። እናንተስ? 👉 በነፍሱም በሥጋውም ርኲሰትን የሚጸየፍ፣ ውድቀት ሱያጋጥመው መልሶ በንስሐ የሚታደስብትሁት 👉 ሐቀኛ፦ ለፍትሕ እና ለእውነት የሚኖር፣ ሤራና ቁማርተኝነትን፣ በዜጎች መካከል እድልዎን የሚጸየፍ ደግ አባት/እናት 👉 የህፕገሩቷን የሺ ዘመናት ታሪክ አመዱን ከፍሙንለይቶ ለዛሬ ትውልድ ሙቀትና ከፍታ ወደ ሞተር የሚቀይት፣ የሐሰት ትርክትን፣ ታሪካዊ ጠባሳዎችን አጣምሮ እያጋነነ ለዜጎች ተዋህዶ እንቅፋት የማያኖር፣ የሚከላከል 👉 በሀገሩ ልጆች አእምሮ፣ ጥረትኔ ምክር የሚተማመን፣ የባዕዳን አሻንጉሊትና ተላላኪ ያልሆነ 👉 የቀጠናዊ፣ አህጉራዊና ዓለም ዐቀፋዊ አውዱ ንባብና በሀገሩ ላይ ያለውን  አዎንታዊና አሉታዊ ተጽእኖ ተረድቶ ለሀገር ጥቅም በሁሉም ደረጃ  አመራር እንዲኖረን ስልት መንደፍና መተግበር የሚችል አቅም ያለው፣ እንደ ስድ አደግ ባለጌ ጎሮምሳ ዘለቄታዊነትንየሌለው ግኑኝነት የማፕፈጥር 👉 በጎረቤት ሀገራት መካከል ሰላም ለምስፈን ክሂሎትና ጥበብ ያለው፣ ያሉትን መልካም አጋጣሚዎች የሚጠቀም ብቻ ሳይሆን የሚፈጥር 👉 በሀገር ውስጥ ያሉትን ብዝኃ እምነቶችና ባህሎች። የስነ ምህዳር ብዝኃነት፣ የትፈጥሮ ህብት ብዝኃነትን ሁሉ ለግጭትና ለሽሚያ ያይደለ ለጉድለት መሞላላትና ሕብረታዊንየሕይወት አንድነት እንደ ተቃራኒ ጾታ ተዋህዶ ለፍሬ መምራት የሚችል 👉  ከሀሉ በላይ ክንረ-ሰብእ፣ ክብረ-ሀገር፣ ክ...

በድለናል፣ እንመለስ!

ከ፫ ዓመት በፊት የተለጠፈ ነው። አሁንም እዚያው የውድቀት ደረጃን ላይ ስለምንገኝ እንድናስታውስ ደግሜ አጋራሁት። ========= እንመለስ!!! 💠 #ክርስቲያን መሆን ቢሳነን #ተፈጥሮአዊ ሰው ብቻ ለመሆን እንሞክር እንጂ። መምህራኑም ከማስጨብጨብና ከእልልታው ያለፈ ትምህርት አስተምሩንማ! #ክርስቲያን መሆን ቢሳነን #ተፈጥሮአዊ ሰው ብቻ ለመሆን እንሞክር:- በውርጃ ሕጻናትን ከመፍጀት ንስሐ መግባት፣ ወጣቶች ዝሙትን ማቆም፣ ከሰዶምነት መውጣት፣ ዘረኝነትን መጸየፍ፣ ሐሰትና ጥላቻን መጥላት፣ ትዳርን ከማፍረስና ከማርከስ ራሳችንን በክርስትና መጠበቅ   እንዴት ይሰወረናል?  አሁን የምንገኝበት በገዛ አገራችን መሰደድና መገድል፣ መዋረድና መሰደብ፣ ለምን ይመስላችኋል? እግዚብሔርን ስለማስቀየማችን የመጣ ቅጣት እይደለምን? 💠እኛ ክርስቲያን ነን ባዮች በዚህች በቅድስት አገር እየኖርን፣ በዚህ ክርስቲያን በተሰኘ ታላቅ ስም እየተጠራን  በእግዚአብሔር ፊት  ምን እየሰራን እንደሆነ በትክክል አውቀን ንስሐ እንግባ! ከዚያም የአጋንንት ማኅበርና መሣሪያ ሆነው ክርስቲያኖችን በሁለገብ ጥቃት ሥር እያጠፉ ያሉትን ፊትለፊት በአንድነት፣ በአንድ ልብና በእምነት ሆነን እንግጠማቸው!!! በክርስትና እየተጠራ ክፋትን የሚሠራ ሁሉ የአንድ አካለ-ክርስቶስ ብልት ነውና ያልበደለውን ሁሉ ያስቀጣናል!!!  ለሀጥአን የመጣ ለጻታድቃን አንዲሉ። ============ በጥፋታችን እንደንቀጣ  ሰውን ከሰውነት  ባዋረደ፣ ከዜግነትም ውጭ በሚያደርግ፣ ከሁሉም በላይ በጥምቀት የተገኘችዋን የክርስቶስ ልጅነት  ሁሉ አርክሶ፣ዘ ንግቶ በሌላ አይነት የማንነት መሥፈርት  በመሰብሰብ፤ ሌሎችን ለይቶ ለማዋረድና ብ...

ክትስቲያን ወደ ጠላቶችህ ለምረትብአታልቅስ?

ኤዲያ! ራስህን ተከላከል!  ምን የማይለቅ ጽኑ አዚም ነው ኦርቶዶክስ ክርስቲያኑን የተፀናወተው? አታልቅስ!  ሰሚ ወገን የለህም! ካለቀስክ ውድ እግዚአብሔር  ብቻ! እንዴት የሚገድልህ መንግሥት ሊታደግህ  ይደርስልሃል?  ነው መንግሥት ይድረስልኝ  እያልክ ፯ ዓመት ሙሉ ምን ሆንክ አላየኸውም?   ራስህን ተከላከል! ነፃ አውጭም መፍትሄ ሰጭም የለም። በቤተመንህሥትም ሆነ ብቤተ ክህነት የተካድክ፣ እረኞች ግድ ይህን እያወደሱና ካባ እያለበሱ "በርታልን፣ እኛን ብቻ ከድሎታችን አታፈናቅለን ብለው አላግጠውብሃል። መፍትሄው አንድ ሆኖ መነሳት ብቻ  ነው። ለነገሩ  የጎሣ ፖለቲካ ጭፍን መንጋ ለ፶ ዓመታት ያጠቃውን የሃይማኖትና የቋንቋ መለያ የለጠለፈለትን ክፍለ-ሕዝብ በግልፅ እና በመደበኛ ሠራዊት እየጨፈጨፈው  እንደተለመደው  "መንግሥት ይድረስልን" የምትል ድምጽ ከወደ ወለጋ ዛሬም ቀጥሏል።   አዚሙ ምንድነው? አጥፉውን ድረስልን የሚል እንደ ኦርቶዶክስ ክርስቲያን የደነዘዘ ዜጋንየለም!!! የባእዳኑ ተላላኪዎች ገብቷቸዋል፣ በጎሣ መንጋነት ከከፋፈልናቸው እንኳን ምእመኑ መነኩሴውና. ጳጳሱም ዳግም ተመልሶ የክርስቶስ አንድ መንጋ መሆን አይችሉም ብለው ሠርተዉበት አሁን የምናየውን ጎጠኛ፣ በደም ውስጥ ቆሞ የግል ፍተወቱን የሚያርካ፣ የአንድ እምነትና ቋንቋ ባለቤትና ተጠቂ የሆነውን አማራን ሕዝብ እንኳ የሚከፋፍል ሆኖ አገኙት። ፈነጩበት። ከዘረኛ ፖለቲካ የበለጠ የአማራ ጠላቱ ጎጠኛና ናርሲሱስት ባህርይ ያላቸው የፋኖና የዲያስፖራ ደጋፊያቸው ነው።  እነዚህ ቅርብ አዳሪ ጎጠኞች  ከህዝብ ሞይ፣ ስደት፣ መራብ፣ የሕፃናት ትምህርት ማጣት፣ የወጣት በጤርነት መጠበስ...

የብሔር ፖለቲካ ነጋዴዎች የሚጠቀሙት ስልት ሁሉ ይመሳሰላል ልበል?

"አሥር ጊዜ ደጋግመህ  ለካ፣ አንድ ጊዜ ቁርጥ" ለአናፂ ከተነገረ ለሕዝብ ሕልውና ተጋድሎ "መቶ ጊዜ ምከር አንዴ ወስንና ፈጽም" የምትል ብሂል ብናቀንቅን ስህተት  አይመስኝም። ========== እንደምታዘበው ከሄነ የብሔር ፖለቲካ ነጋዴዎች የሚጠቀሙት ስልት ሁሉ ይመሳሰላል ልበል?  * በሕዝብ ስም መማል፣ ግን ሕዝቡን እቃቸው ማድረግ  * ደም፣ አጥንት፣ ቋንቋ፣ ትርክትን መሣሪያ አድርጎ ክብረ-      ሰብእን፣ እውነትን ሰብአዊነትን መድፈቅ፣ * ሤራ * የሚመለኩ ጥቂት ሰዎችን ግን በብዙ  መስዋእትነት መፍጠር * ጎጠኝነት * በሕዝብ ጀርባ ከባዕዳን ተወዳጅቶ ለሥልጣን መሥራት * ሐሰተኝነት ወዘተ ህወሃትን ኦነግ፣ ብልጽግና ወዘተ ነውር የሚፈጽሙት የቡድን ጠባብ ፍላጎታቸውን በኦሮሞ በትግራይ ሕዝብ "ጥያቄ" ስም ነው። ሙስናቸውንም በልማትና በሕዝብ ሀብት የማፍራት ስም ራሳቸውን ያበለጽጋሉ። ይህን የመሰለ ክህደት በፋኖ መሪዎች ምልክት ከታየ የህልውናንታጋዮች ሳይሆኑ ጸረ-አማራ ሊባሉ ይገባል።   አማራ ይህ ሁሉ የጠላቶቹ ርኩስ ልማድ አይስማማውም ባይ ነኝ። ምክንያቱም ሤረኞች ትርክትብፈጥረው፣ ማኒፌስቶ ጽፈው፣ የሰውን ጠላት አበጅተው፣ ከባእዳን መክረው ያስጀመሩት የሕወሃትና የኦነግንአምሳል አይደለም። ራስን የማዳን የትቀደሰ የሰብአዊነትና የፍትህ ተጋድሎ ነው። ተፈጥሮአዊ ነው። ይህን ጠልፎ የጥቂት በሽተኞች መገልገያንለማድረግ መሞከር የወንጀሎች ሁሉ ወንጀል ነው። =========== እሁን አሁን መሬት ላይ ከተንሠራፋው የባንዳነት ስነልቦና የተነሳ   በአንድ ወጥ አስተሳሰብም  የእማራን ትግል እንኳ ለመምራት አልተቻለም። ይህን ጉድለት ያመጣው በአብሮነት ከማሰብ ይልቅ  ...

ሰው የማይታወቅበት አመራርና አስተዳደር በኢትዮጵያ

"ሰው ሳትሆን ሰው አትምራ፣ ተመሪዎችን በልክህ ትከረክማቸዋለህ" የሚል ብሂል ላስተዋውቅ መሰለኝ? በሕይወት ከምመለክተው የእኛ ሀገር ዋና የችግር መንጭ (1) ሰውን የማያውቁ የሰው መሪዎች እና (2) ሃይማኖት የሌላቸው የሃይማኖት መሪዎች ድምር ነፍስንም ሥጋንም እየጎዱ ነው። እነዚህን ለመታገል የሚነሳ ማንኛውም ግለሰብእ ታጋይ ወይንም መሪ እራሱ ከእነዚህ መቅሰፍቶች ለመቃረን፦ "ሰው" መሆኑን፣ ፈሪሃ እግዚአብሔር እንዳለው፣ ለራሱ የግል ፍተወት መርኪያነትና የባዕዳን ማኅደርነት የሚያገለግል አለመሆኑን ማረጋገጥ ይኖርበታል። ከአጥፊ እንታደጋችኋለን፣ ለህልውናችሁ እንድትታገሉ እንመራችኋለን እያሉ "ሰውን" የማያውቁ፦ --› ስው ሳይሆን ብሔረ-ስብእ፣ --› አማኝ ሳይሆን ካህንና ጳጳስ፣ --› በእውነት ላይ ቆመው ሐርነት ሳይኖራቸው "ነጻ አውጭ ፣ የህለውና ታዳጊ፣ መሪ ወዘተ" ባዮች የአዳዲስ መከራ ፈልፋዮች እንጂ መፍትሔዎች ሊሆኑ አይችሉም። ----- የሥልጣንና የዝና ጥማት ያደነቆራቸውና "ሥጋ ብቻዎችን" (ክብር-ነፍስን የማያውቁ የሆድ ሎሌዎች) መሪ ከማድርግና ሥጋ ብቻ ከመሆን ራስን መጠበቅ፣ ማሰብ፣ ማሰላሰል፣ በእምነት መጽናትን እንለማመድ። ለበለጠ ዐሳብ --› ይህን ይመልከቱ፣ ይሟገቱ፣ አዳዲስ "ሰውነትን" ያገናዘበ ዐሳብ ያመንጩ። ሰውን የማያውቁቱ የጎጥ ባሮች በሰጡኝ ስሜ "ጃል" ዋቄ. ነኝ ============ ሰው የማይታወቅበት አመራርና አስተዳደር በኢትዮጵያ  ሰውነትን ያላወቁ ሰው ነን ባዮች ከመክራችን ሊገላግሉን አይችሉም! ጭፍን መንጎች እየተከተላችሁ መከራችሁን አታራዝሙት! ለሰው ያለን ትርጉ እንኳ አላግባባ ይበለን?  ለብልጽ...

በግላችሁ ጎልሙቱ! ሕዝብ ይዛችሁ አትሙቱ!!

በግላችሁ ጎልሙቱ! ሕዝብ ይዛችሁ አትሙቱ!!  https://ethiopiaorthodoxchristian.blogspot.com/2025/06/blog-post_62.html ነገር ግን  እንደ ሕወሃትና ኦነግ   የየሠፈራችሁን  የዋህ አታልላችሁ ሕዝብ ይዛችሁ አትሙቱ! ብሎ መናገር ሳይረፍድ መነገር አለበት። ከ፶ ዓመቱ የናርሲስቶች እና የዘረኞች የሤራ ፕሮፓጋንዳ ተማሩ! ለተከተላቸው ምን እንዳተረፉላቸሁ አስቡ! ================== እንደ እኔ ---- ግለ-ሰብእን ለማረቅ  የግለሰቡን ሰንእና የጎዳውን መሠረታዊ ዐስተሳሰብን ማቃናት  ለነፍስ ዋጋ ብዙ ያለው ይመስለኛል።  ጥመት ከጠማማ አእምሮ መንጭታ አድጋና ተንሰራፍታ  ትውልድን እንዳትበክል በዐሳብ ላይ መነጋገር   ለሀገር ይተርፋልና ከአንድ ጉልምት ድውይ ግለሰብ ተነስቼ  ትውልዱን እናገራለሁ።  የእኔ የሕይወት መርህ ምንጩ ቤተክርስቲያን ናት። እውነትን በፍቅር ስንናገር ሁላችንም ለታመሙ ወገኖቻችን ሐኪሞች እንሆናለን። ሌሎችም እኛ ስንታመም ያክሙናል። በጎጥና በሌላም የመሰባሰቢያ ምክንያት መነሻነት የቡድን ዕሳቤ ባርነት ተይዘን ጭፍን መንጎች ስንሆን  ግን ሁላችንም እንታመማለን። ሐኪም አይገኝም፣ ከተገኘም ክፉና ደጉን፣ ጤናና በሽታን መለየት እንዳይችል የቡድን አምላክ አይፈቅድለትም። ሞቶም  እያለ እኔን ምደሉ. ተከተሉኝ እያለ ጥፋቱን ያጋባል። የታረማችሁ  ወገኖቼ አርሙኝ።  =========  የጎጥና የድብቅ ዓላማ ወዳጆቹ የምትሆኑ ሁሉ ለመናገርና ሀሳብን ለማካፈል ምክንያት ለሆነኝ ወንድሜን ምስግኑት። እኔ ላነጋግረው ብደውልለት  ለዚህ  የሕፃን ፕሮፓጋንዳ አገል...

ለሁኔታችን የሚመጥን መሪ እንዴት እንወቅ?

ለሁኔታችን የሚመጥን መሪ እንዴት እንወቅ? #በአብይ እና ከርእዮት ወላጆቹ ከአመጡብን መከራ ተነስተን ስለ መሪዎች ሰብእና ምን እንማራለን? ========== #አብይ አህመድ እርሱን ከፈጠሩት ቀዳሚ ዘረኛ መሪዎች በመርከብ በሀገራችን ላይ ያደረሰውና እያደረሰው የሚገኘው ጉዳት ካሣ የማይገኝለት ቢሆንም አንድ ትልቅ ውለታ ለትውልዱ ውሏል። እርሱም የፖለቲካ መሪዎችን በምላሳቸውና በብልጣብልጥ ንግግሮቻቸው እና በአዲስነትና ለውጥ ሽፋን ምን ያህል ሕዝብን አደንዝዘው በማስከተል ወደ አጠቃላይ ውድቀት ሊወስዷቸው እንደሚችሉ ማሳየቱ ---- እንደ እኔ ግምት ከአሁን በኋላ ትውልድ ሁሉ  የፖለቲከኞችን የመጨርሻ ደረጃ ህሊና ቢስነትና የማታለል አቅማቸው ተገንዝቦ መሪዎችን ለመምረጥና ለመታዘዝ ከስሜትና ንግግር ባሻገር በግልጽ መሥፈርት ብቻ እንዲመዝን ትምህርት አግኝቷል እላለሁ። ስለዚህ ----- መሪ ስንመርጥ ስንከተልና ስን ታዘዝ አስቀድመን  በሚከተሉት ነባር ሰብአዊ እናቶች  መመዘኛ መሆን ይኖርበታል ብለን የምንግባባ ይመስለኛል:- ፩) ፈሪሃ እግዚአብሔር እንዳለው በአጠቃላይ ሕይወቱ ያስመሰከረ ፪) ለራሱ ሳይሆን ለሚመራቸው ወገኖቹ ለመሰዋት ዝግጁነቱን በተግባራዊ ሕይወቱ ያረጋገጠ፤ ፫) ተክለ ሰውነቱን መንጋ አጫፋሪዎችን በጎጥ፣ በጥቅም፣ በተስፋ እያጓጓ  በማሰማራት የማይገነባ ትሁትና እውነተኛ፣ በተግባር ብቻ ከፍ የሚል፣# ፬) ወገንተኝነቱን ከጎጥና ከጎሣ ነጻ አውጥቶና እርሱም  ወጥቶ ለክብር-ሰብእ፣ ለፍትህ፣ ለእውነት ፣  ለአሁንና ለመጭው  ትውልድ ሁለንተናዊ ደኅነት ማድረጉን በተግባር ያስመሰከረ፤ ፭) በግል ሕይወቱ ከስግብግብነት፣ ፍቅር ንዋይ፣ ዝሙት፣ ትዳርን ከማርከስ፣ ከሤራ፣ ከከፋፋይነት፣ ከነ...

አባቶችህን አክብር! ወደ መዳን መንገድ ያሳዩሃል።

ክብር ለማን ይገባል? ጌትችን፣ አምላካችን፣ መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዮሐንስ ወንጌል ፲፪፣ ፵፫    "ከእግዚአብሔር ክብር ይልቅ የሰውን ክብር ወደዋልና።" ብሎ ፈሪሳውንን ሲወቅሳቸው  ለተከተሉት እና የዚህን ክፉ ዓለም ቅጣት ሳይሰቀቁ  መኖር ለተገባቸው  ደግሞ  በዚሁ መጽሐፍ ውስጥ ፲፯: ፳፪-፳፫  በተዋሐደው ሥጋ ለሚመለከቱትና ግራ ለተጋቡት ምሥጢር ሱገልጥ ወደ ሲጸልይ  "እኛም አንድ እንደ ሆንን አንድ ይሆኑ ዘንድ፤ እኔም በእነርሱ አንተም በእኔ ስትሆን፥ በአንድ ፍጹማን እንዲሆኑ፥ የሰጠኸኝን ክብር እኔ ሰጥቻቸዋለሁ፤ እንዲሁም ዓለም አንተ እንደ ላክኸኝ በወደድኸኝም መጠን እነርሱን እንደ ወደድሃቸው ያውቃል።" ብሎ ክብር የሚገባቸው  እግዚአብሔር አብ ፣ እግዚአብሔር ወልድን በወደደበት የባህርይ ተዋህዶ አንጻር በጸጋ የፍቅር ተዋህዶን ከእግዚአብሔር ለማግኘት የሚጋደሉትን ወገኖቹን፣ በዚህ ተጋድሎ ፍቅረ እግዚአብሔርን ቀምሰው በፍቅረ ቢፅ የሰጠሙትን፣ እነርሱ የቀመሱትን ደግሞ ሌሎችም አማኞች  ሁሉም እንዲቀምሱላቸው፣ በክርስቶስ ሁሉም የጥምቀት ልጆች እንዲዋሀዱላቸው ሕይወታቸውን የሰጡትን  ሐርያትንና የሚመስሏቸውን  "አባቶች" ልንል፣ ከእግዚአብሔር በነሱት ክብር ልናከብራቸው  ይገባል። ይህን የምናደርገው ስለታዘዝን ብቻ ሳሆን ክርስትናን ለመኖር የምግብ ጀመሪያ መግቢያ በርና ግዴታችን ስለሆነም ነው፤ ከባህርይ መድኀኒት ከክርስቶስ የሚያገናኙ  ሰዎች የጸጋ መድኀኒት ናቸው እና መዳኛውን የማያከብር ኢአማኒ ብቻ ነው።  በዚህ መልክ ለአባቶች ክብር ይገባቸዋል።    ነገር ግን እውነተኛ አባቶች የወሰዱትን የክህነት ደ...

እሽ አትበሉኝ የሹም ዶሮ!! ጎጠኛ "የህልውና ታጋይ" ሊሆን ከቶም አይችልም! ራሱም አደጋ ነውና።

እሽ አትበሉኝ የሹም ዶሮ!! --- እንትን ያለበት ዝላይ አይችልም እንደሚባለው ትንሿ የእኔ የግል ትችት በጓዳ ሲቦካን የከረመውን  ቡኮ  ወደ አደባባይ አውጥቶ ልብ ያለው ሁሉ የሽታውን መርዛማነት እንዲያውቀው በማድረጉ እግዚአብሔርን አመስግነዋለሁ። ======================  ይህ አገር እንደተቀሰፈ የጅዝቡን መከራ በማየት እናውቃለን። የበለጸ ግን እርግማኑ ጽኑ መሆኑን የሚያሳየው ከመከራ ልታደጋችሁ፣ ከሃውና አደጋ ልከላከላችሁ ዘመትኩ ከሚሉት ወይንም ከፕሮፓጋንዳ ክንፋቸው አንዳንዶች ወደ አደጋ ተለውጠው መከሰታቸው ነው። አማራንና ኦርቶዶክስን አደጋ ላይ የጣለውን ትርክት በብታቸው ይዘው ተገኙ፤ እንዲህም ገለጡት! ፩) አሮጌ ትርክት አንሻም፣ ፪) ሰለሞናዊ ትርክት ጠላታችን ነው፣ ፫) እንደ ደርግ ኢሕአፓ፣ መኢሶን፣ ሕወሃት፣ ኦነግ ወዘተ "አዱሱቷ ኢትዮጵያ" ነባር እምነትም አይሻም፣ ፬) ትግላችን እግዚአብሔርን እንደ አምላክ  ታሳቢ የማያደርግ ሴኩላር፣ በተለይ የመጽሐፍ ቅዱስ ጽጥስን የሚጸየፍ ነው፣  ፭) ትግላችን ለዐስብና እሴት ይበልጥ የደም ጥራት ላይ የተመሠረተ ነው፣ ፮) የኦርቶዶክሳዊ ክርስቱያንን መብት ይሚጠይቅ ንቅናቄንየአማራንትግል ጠላይ ነው፣ ፯) ከጽምቀት የክርስቶስ ልጅነት ፖለቲካዊ አማራነት (ነባር ማነቱን የጣለ በልሂቃን ዕሳቤ ልክ ለተፈለገ ግብ መሳካትንየሚተረጎም፣ ለሕወሃቱንትግራዋይነትና ለኦነጉ ኦሮሞነት አቻ የሆነ አማራነትን ብቻንየሚቀበል)  --- በማለት ተገለጡ። ይህ መገለጥንሳይዘገይ በመሆኑ እግዚአብሔር ይመስገን። ፕህን ልፉ ሤራንያነገቡ ሰዎች ወራት ኪሎ ደርሶ አዲሱ "የአማራው 'አብይ አህመድ' " ተገልጦ ቡሆን ኖሮ የአማራ መስዋእትነት ከንቱ በሆነ መከራችን በቀጠለ ነበር። ...

ሃይማኖት የለሽ ትግል ጸረ ኦርቶዶስ ለመሆኑ በሃምሳ ዓመታት ተምረናል

ይበቃል! ታሞ ከመማቀቅ አስቀድሞ መጠንቀቅ እንዲሉ የበሽታው ምልክት ታይቷልና ሕክምና ያስፈልጋል!!!  አምላክ የለሾች፣ ሀሰትኞች፣ የባእዳን ዕሳቤ ባሮች የድፕቅኑትን የህልውና አደጋ ለመቀልበስ የተሰለፈውን ክቡር የሰው ልጅ ሕይወት እየከፈሉ፣ በተቃራኒው ሕይወቱን የሚሰጠውን ማኅበረ-ሰብእ ሃይማኖት፣ እሤት፣ ነባር ትርክት   ከጀርባ ለማጥቃት መሞከር  ከባድብክህደትም ኃጢአትም ነው።  " ጸረ-ኦርቶዶክስ ካልሆንን ትግል አይሳካም" የሚል  መዝሙር የማነው? መልስ ይፈልጋል። ፶ እና ከዚያም እጥፍ የሆነውን ሕዝብ የእሤትና የማነት ምንጭ የሄነችዋን ኦርቶዶክሳዊት ክርስትና እንደሌለች ቆጥሮ ፖለቲካና ትግል ለማካሄድ ማሤርን ከደርግ፣ ከኦነግ፣ ከወያናና ከድቅል ልጃቸው ከብልጽግና ወንጌሉ ፖለቲካዊ ኦሮሙማ ውጤቱን አጭደናል።  ተምረናል። የአማራንም ተጋድሎ ጠልፎ በጸረ-ኦርቶዶክስ አጀንዳ መበከል ተቀባይነት አይኖረዉም።   ይህንን  በአቃፊነት ስም ያልተጻፈውን፣ በተክባር አግልሎ የማያውቀውን አማራነትና ኢትዮጵያዊነት በጠላት በጠለሸ ትርክት እየተመሩ "ሃይማኖታዊ መብቶችን ካነሳን አንድ መሆን አንችልም" የሚል ውሃ  የማያነሳ ማደናገሪያ ከፊት አስቀድመው በኦርቶዶክስ ክርስትና ላይ መርዛቸውን የሚረጩ አንዳንድ ድብቅ ተልእኮ ይዘው ፋኖ ውስጥ የሰረጉትን ወገኖች በጥንቃቄ መመልከትን ችላ አንልም።   አንድነትህን ያደነቃቀፈው እስልምናና ክርስትና ሳይሆን የሥልጣን ጥምና ጎጠኝነት፣ ሤረኝነትና ራስ ወዳድነት፣ ከዚያንካለፈ ድብቅ የጠላት ተልእኮ፣ ተሸካሚነት ወይንም  ይትግሉን ውስብስብነትና የሚጠይቀውን ጥንቃቄ ያለማወቅ ድንቁርና ሊሆኑ ይችላሉ።  አማራን እንደ ኮድ አድርጎ...

በፋኖ መካከል እንክርዳዱን ማን ዘራው?

#በፋኖነት ውስጥ እንክርዳድ እንዴት በቀለ? ማን ዘራው? #አማራ ንቃ!  ጠላቶችህ በሥጋህ እየገደሉህ ነው፣ ከዚህ ለመዳን በመስዋእትነትህ ምላሽ እየሰጠህ ነው፤  ግና ከጉያህ ተሸጉጠው በነፍስ ሊገድሉህ በክርስትናህና የተቀደሰው ታሪክህ ላይ የሚደራደሩ እጅግ እጅግ ጥቂት የአረሞች ምልክት እየታየ ነው። ======================= #አማራ የሥጋን ሞት እየተዋጋህ የነፍስን ሞት በጓሮ በር የሚያስገቡ ድውያነ አእምሮ  ሰርጎ ገቦች  የጠላት ሰይጣንን ፍላጎት ያስቀደመ፣ የትግሉን መርህና ዕሳቤ የሚከልስ ሂደት ብቅ ብቅ እያለ ነው። ነገር ግን --- እግዚአብሔር ይመስገን።  እንኳንስ ሳይረፍድና አረሙ ፍሬ እፍርቶ ሳይረጭ ተገለጠ።   የማረሙ ኃላፉነት በሁሉም ክርስቲያኖች ጫንቃ ነው። በእርግጥ ከቤተ ክህነቱ ምንደኛ የብልጽግና መንግሥት አውዳሾች ምንም አይጠበቅም። ============ #አማራ ዋጋ የምትከፍልለት ተጋድሎህ ለሥጋዊ ህልውናህ ብቻ ሳይሆን ለዘላለማዊ ሕይወትም ዋጋ ያለው የሙሉ ሰብእና ማሳያ ይሁን! ዛሬን ከሥጋ ሞት ለመዳን ስትል እምነትህን በስልት ሊያስጥሉህ፣ ሊከፋፍሉህ፣ የሥልጣን መወጣጫ እርካብን በደምህና በአጥንትህ ሊያቆሙ ከሚሯሯጡ ግለኞች ራስህን ጠብቅ። የባእዳን ዕሳቤና ፖለቲካዊ ርእዮት ወራሽ የሆኑ ጥቂት የሳቱ   ልጆችህ  በረቀቀ መንገድ በክርስትህና ነባር ታሪክህ ላይ በራስህ መስዋእትነት ጥፋት ለማድረስ ተልእኮ ተቀብለው ከአድዋ እስከ ብልጽግና ወንጌል ያልተሳካውን የጠላት ዓላማ ሊያሳኩ እየሞከሩ ነው!   ንቃ!!! ================ #አማራ! የህለውናህ ታጋዮችህን ደም ከንቱ የሚያደርጉ ጸረ ክረስትና ቡድኖች በታጋዮቹ  መካከል ተመድበዋ...

የሚያድን እና የሚገድል ፍርሃት

ራሳችንን እንጠይቅ⁉️  ምን ነካን⁉️ የማያድን ፍርሃት ለምን እንፈራለን ⁉️ ሃምሳ ዓመት ሙሉ እንዲገድሉን ለምን ፈቀድን?⁉️ የሚያስገድሉንና ከገዳዮቻችን ጋር የሚተባበሩትን ምንደኞች እንዴት እረኛ ባለን ተቀበልን⁉️ እግዚአብሔር ሲፈጥረን ከሰጠን የመዳን ጸጋዎች መካከል አንደኛው ወደ ፍጹም ፍቅር እስክንደርስ ድረስ እርሱን በመፍራት ከጥፋት መጠበቅን ነው። #ቅዱስ #ዳዊትና ሰሎሞን "የጥበብ ሁሉ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው" አሉን፤ ለፍጹማን መነኮሳት የሚመክረው ሶሪያዊው ቅዱስ ይስሃቅ (ማር ይስሃቅ) "የጥበብ ሁሉ መጀምሪያ እግዚአብሔርን ማፍቀር ነው" ሲል "ፍርሃት" ወደ ፍቅር ማድረሻ መሆኗን ይጠቁመናል። ጌታችን "ሥጋን የሚገድሉትን አትፍሩ፣ ይልቁንም ስጋና ነፍስን አዋህዶ በሲዖል ሊቀጣ የሚችለውን እግዚአብሔርን ብቻ ፍሩ" ብሎናል። ከእነዚህ መልእክቶች የሚያድን ፍርሃትና የሚገድል ፍርሃት መኖሩን  እንረዳለን። እኛ በዚህ ዘመን ያለን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ክርስትና ተከታዮች ፍርሃንታችን የሚገድልና የሚያስገድለው አይነት ፍርሃት  ነው። የሚያድነው ፍርሃት እግዚአብሔርን ብቻና ብቻ በመፍራት የእውነት ምስክርነት (ሰማእትነት) ሕይወት መኖር ነበር። ይህ አይነቱ አኗኗር በሥጋም፣ በንፍስም ነጻነት እንድናገኝ አባቶቻችን ኑረዉት ባስረከቡን ነጻ ሀገርና ብርሃን በሆኑ ቅዱሳን ታሪኬቻችን ይታወቃል። ዛሬ ያለነው ሀገር ተነጥቀን፣ ቤተ ክርስቱያናችን የምንደኛ መንጋ ተንሰራፍቶባት፣ ታሪካችን ባእዳን አሠልጥነው ምሁራን ባሰኟቸውና ለሀገራቸው ዕንቁ ምሥጢር በማወቅ ዘርፍ ደንቆሮ የሆኑ፣ መዋስ እንጂ ማሰብን እርም ያደረጉ ሰዎች ጠልሽቶ፣ ፖለቲካችን እኛን በማጥፋት ፕሮጀክት ላይ ተዋቅሮ፣ ...

ኦርቶዶክሳውያን ለምን የጎሣ ፖለቲካ ፓርቲዎችና መንግሥት ዒላማ ተደርጉ

ጎሰኝነት/ኑዑስ ብሔርተኝነት ባለ ረዥም ታሪኳ ኢትዮጵያ ውስጥ ሳይቀር እንዴት ተፈጠረ፣ እንዴትስ በአፍራሽነቱ ጸና? የሀገራችን ዋና የመከራ ምንጭ፤ የስደት፣ ዘር ማጥፋት  ደረጃ  መድርስ 1. በማኅበራዊና ተፈጥሮአዊ ሰንሰለታዊ መስተጋብር የሚፈጠሩ ታሪካዊ አሻራዎች፦   በዓለም ውስጥ፣ በተለይ በአፍሪካችን  ጎሣዎች የኖራሉ። ለዩ ቋንቋዎች፣ ልዩነት የሚያሳዩ ባህሎች፣ በተወሰነ ደርጃ በአስተዳደርና ፍትሕ ሥርዓት ለዩነታቸው እየተዋሐደ ሳይሆን እየደመቀ መቆየቱ ይታያል።  ይህ ንዑስ ማንነት  ጤናማ ሆኖ የሚኖረው ፖልቲካዊ መሣሪያ፣ የምጣኔ ሀብት  ሽሚያ ምክኒያት ሲሆን ጎጅ፤ በተፈጥሮው ተከብሮና ተመጋጋቢ ህብረት አስገኝቶ ለእድገትና ለአቅም ምንጭ ይሆናል። 2. የቅኝ ገዥዎች ተጸኖ፦  በከፋፍለህና አዳከመህ ግዛ የቅኝ ግዥዎች ስልት በቀጥታ በአካል ተገኝተው ባርያ ያደረጓቸው የአፍሪካ ሀገራት፣ እንደ ኢትዮጵያ በትምህርት ስም አእምሮ አጠበው ባርያ ያደርጉት አገር ውስጥ ያሉ ታሪካዊና በማኅበራዊ መስተጋብራዊ ዝግመተ ለውጥ የተፈጠሩ ኑዑሳን-የጎሣ ማንነቶች  ከህብረታዊ አንድነትና ከተዋህዶ በተቃራኒ እንድ ሕወሃትና እንደ ኦነግ ባሉ የባዕዳን የአእምሮ ባሪያ ልሂቃን ጠላትነት አፍርተዋል። ከመዋሀድ በተቃራኒ መራራቅና መጠፋፋትን ሳይቃወሙት ለልሂቃኑ የጥፋት መሣሪያነት ተሰልፈው ቀጥለዋል።  3. የቋንቋና የባህል ብዝኃነት፦  አፍሪካ ውስጥ በአጠቃላይ  በአንድ ሀገረ-መንግሥት ውስጥ ብዙ ቋንቋ ተናጋሪዎችና ልዩ ልዩ  ባህሎች አሉ። እንዚህ ልዩነቶችን ወደ ሀገራዊ የጥንካሬ ምንጭ ለማሳደግ ከሚደረገው ጥረት የበለጠ በቱሪስት ሸቀጥነት፣ በየጎሣ መሪዎችና የየጎሣው አባ...

ፖልቲካ-ሠራሽ ከሰውነት ከሚያሳንስ ኑዑስ-ጎሣዊ-ማንነት መገላገል መከራችንን ይቀንሳል

 የጎሣ ልሂቃንና ጭፍን ተክታዮቻቸውን የምመክርው ነገር አለኝ፦ በቋንቋ፣ በትርክትና ፖልቲካ-ሠራሽ ከሰውነት በሚያሳንስ ኑዑስ-ጎሣዊ-ማንነት የአእምሮ መዛባት ራሳችሁን ማዳን ጥቅሙ ለራሳችሁ ነው! ክርስቶስን በመዘንጋት ጎሣቸውን እንደ ጣዖት የሚያገልግሉ የፓርቲ አገልጋየ አባት መሰል ግለሰቦች ሲገኙና ሲወቀሱ እጅግ የሚያማቸው የኦነግ ኦሮሙማ   የፋሺዝም አእምሮዎች እጅግ ይንጫጫሉ። ስሞኑን አቡነ ገብርኤል በሚያሠራጩት ኑፋቄ ምክንያት መወቀሳቸውን ከሚመለከታቸው ከሊቃውንት ጉባኤ፣ ምሥጢር ካደላድሉ መምህራን፣ ከሲኖዶስ ቀድመው   ተቆጭተው የሚይውለበለቡት ኦነጋውያንና የብልጽግና ወንጌል አራማጆችና  ጸረ-ነባር እሤት እንዳላቸው ላልፉት 50 ዓመታት ሀገር በማመስ የሚታወቁት ናቸው። #OMN የተባለው ቀንደኛ የዘ*ር ማ*ጥ**ፋት  አዋጅን ያለ ድካም የሚለፍፈው ሚዲያ ይህንኑ የተለመደ አሉታዊ ጣልቃ ገብነቱን ቀጥሎበት የሃይማኖትን ጉዳይ ለኦሮሞ ፖለቲካ ማድመቂያ ተጥቅሞበት ታይቷል።  በዚህ ሚዲያ "አማራን ከ30 ሚሊዮነ ውድ 120 ሺ መቀንስ፣ manegable በማድረግ ሰሜን ሸዋ  መንዝ ማስቀመጥ"  የሚል ፕሮፓጋንዳ ጋዚጠኛ ደጀኔ በሚባል ግለሰብ አቅራቢነት የቀረብ ተወያይ ለተከታዮቹ ሲመክር  የሚዲያው ባለቤቶች ስለተስማማቸው እርምት አልወስዱም፣ ይቅርታም አልጠየቁበትም።  በተግባር ድግሞ በአማራ ስም ኦርቶዶክሳውያንን፣ ኦሮሞ ኦረቶዶክስ ክርስቲያኖችን ጨምሮ ማጽዳቱ በአርሲና ወለጋ ቀጥሏል። ይህ ሚዲያ ስለዚህ አይዘግብም። በታሪክ እንደምናውቀው፦- የጎሣ ፖለቲካ ከፋሺዝም አምልጦ አያውቅም።  በሀገራችን ኦነግና ሕወሃት የተከሉት የፋሽዝምና አፓርታይድ  ርእዮት እውር ድንብ...

ኢትዮጵያ የተገዳደሯትን ሁሉ ቅኝ ገዥወች የተከላከለችባቸው፣ የተዋጋችባቸውና ነጽነቷን ያስከበረችባቸው እሴቶች; በቀሲስ አስተርአየ ጽጌ

የጽዋዕ ማህበራትና ሰንበቴ ከቅድስት ድንግል ማርያም ጋራ የተሳሰሩት የጽዋ ማሕበራትና ሰንበቴወች ናቸው፡፡  ኢትዮጵያ የተገዳደሯትን ሁሉ ቅኝ ገዥወች የተከላከለችባቸው፣ የተዋጋችባቸውና ነጽነቷን ያስከበረችባቸው እሴቶች  ቀሲስ አስተርአየ ጽጌ  nigatuasteraye@gmail.com  ሚያዚያ ፳፩ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም.  (April 28, 2025)  መግቢያ  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያናችን ኩለንታዊት ቀዳማዊት ደኀራዊት፡ ዘመናዊት ናት ስትባል እም ኀበ አልቦ አይደለም፡፡ በብዙ እሴቶቿ ነው፡፡ ኩለንታዊት ከምታደርጋት ከብዙ እሴቶቿ መካከል የጽሑፌ መነሻ የሆኑት ከቅድስት ድንግል  ማርያም ጋራ የተሳሰሩት የጽዋ ማሕበራትና ሰንበቴወች ናቸው፡፡ ስንበቴ በቀጥታ ከእግዚአብሔር የታዘዘች ናት፡፡ የጽዋ ማኅበርም እንደ ሰንበቴው ቀጥታ ከግዚአብሔር ባይሆንም፡ በዮቶር በኩል ለሙሴ የደረሰው የግዚአብሔር ምሪት ናት፡፡ የጽዋ ማሕበርና ሰንበቴ የትርጉማቸው መነሻ፡ መድረሻና የመጨረሻ ዋና ዓላማቸው ሰባዊ ክብርና ነጻነት ነው፡፡   ኢትዮጵያ የተፈታተኗትን ሁሉ ቅኝ ገዥወች ከተከላከለችባቸው ከተዋጋችባቸውና ነጽነቷን ካስከበረችባቸው ዋናወቹ እሴቶቿ ውስጥ የጽዋ ማሕበራትና ሰንበቴወች ናቸው፡፡ በቅኝ ገዥወች ሲቀጠቀጡ ከኖሩት ካጎራባች አገሮች ልዩና የነጻነት ምሳሌ ያደርጓትም የጽዋ ማህበርና ሰንበቴ ናቸው፡፡ የጽዋ ማኅበራትና የሰንበቴ ድርጅቶች እንዴት ተመሰረቱ? ለኢትዮጵያ ምን ጠቀሙ? ትሩፋታቸው ምንድነው? የደርግንና የወያኔን ዘመናት እንዴት ተሻገሩ? በብልጽግና ዘመንስ እንዴት ናቸው? እንዴት ይቀጥሉ ? የሚሉትን ጥያቄወች ለመመለስ ከጽዋ ማኅበር እንጀምር፡፡   የጽዋ ማኅበር መነሻ...