ኢትዮጵያን የሚመጥን መሪ ለመፍጠር መስፈርት ላይ ሀሳብ እናዋጣ! በሰው ደም ካልታጠቡ፣ በዜጎች ዕንባ ካልዋኙ አየር የተነፈሱ የማይመስላቸው ድውያነ አእምሮ፣ የክፋት አበጋዞች፣ የሐሰት ምንጮች፣ የሤራ መሀንዲሶች እና የቁማር ሱሰኞች ዳግም እንዳይነዱን ከፈለግን ከጭፍን መንጋነትንወጥተን እናስብ!!! እኔ ለማስጀመር እንዱህ ብያለሁ። እናንተስ? 👉 በነፍሱም በሥጋውም ርኲሰትን የሚጸየፍ፣ ውድቀት ሱያጋጥመው መልሶ በንስሐ የሚታደስብትሁት 👉 ሐቀኛ፦ ለፍትሕ እና ለእውነት የሚኖር፣ ሤራና ቁማርተኝነትን፣ በዜጎች መካከል እድልዎን የሚጸየፍ ደግ አባት/እናት 👉 የህፕገሩቷን የሺ ዘመናት ታሪክ አመዱን ከፍሙንለይቶ ለዛሬ ትውልድ ሙቀትና ከፍታ ወደ ሞተር የሚቀይት፣ የሐሰት ትርክትን፣ ታሪካዊ ጠባሳዎችን አጣምሮ እያጋነነ ለዜጎች ተዋህዶ እንቅፋት የማያኖር፣ የሚከላከል 👉 በሀገሩ ልጆች አእምሮ፣ ጥረትኔ ምክር የሚተማመን፣ የባዕዳን አሻንጉሊትና ተላላኪ ያልሆነ 👉 የቀጠናዊ፣ አህጉራዊና ዓለም ዐቀፋዊ አውዱ ንባብና በሀገሩ ላይ ያለውን አዎንታዊና አሉታዊ ተጽእኖ ተረድቶ ለሀገር ጥቅም በሁሉም ደረጃ አመራር እንዲኖረን ስልት መንደፍና መተግበር የሚችል አቅም ያለው፣ እንደ ስድ አደግ ባለጌ ጎሮምሳ ዘለቄታዊነትንየሌለው ግኑኝነት የማፕፈጥር 👉 በጎረቤት ሀገራት መካከል ሰላም ለምስፈን ክሂሎትና ጥበብ ያለው፣ ያሉትን መልካም አጋጣሚዎች የሚጠቀም ብቻ ሳይሆን የሚፈጥር 👉 በሀገር ውስጥ ያሉትን ብዝኃ እምነቶችና ባህሎች። የስነ ምህዳር ብዝኃነት፣ የትፈጥሮ ህብት ብዝኃነትን ሁሉ ለግጭትና ለሽሚያ ያይደለ ለጉድለት መሞላላትና ሕብረታዊንየሕይወት አንድነት እንደ ተቃራኒ ጾታ ተዋህዶ ለፍሬ መምራት የሚችል 👉 ከሀሉ በላይ ክንረ-ሰብእ፣ ክብረ-ሀገር፣ ክ...
This is a spot where I post and share part of my daily reality. I would love to hear from others too to learn how differently we interpret daily encounters including our imaginations. ይህ ሥፍራ የየዕለት ገጠመኞቼን፣ እንዴት በዕለቱ እንተረደሁትና የማስበውን ለሌሎች ያማጋራበት ነው፡፡ የሌሎችን በመስማትና ምን ያህል ዓለማችንን በተለያየ መንገድ እንደምንመለከታት ለመማር እጓጓለሁ፡፡