ወደ ዋና ይዘት ዘለው ይሂዱ

ልጥፎች

ኢትዮጵያን የሚመጥን መሪ ለመፍጠር መስፈርት ላይ ሀሳብ እናዋጣ!

ኢትዮጵያን የሚመጥን መሪ ለመፍጠር መስፈርት ላይ ሀሳብ እናዋጣ! በሰው ደም ካልታጠቡ፣ በዜጎች ዕንባ ካልዋኙ አየር የተነፈሱ የማይመስላቸው  ድውያነ አእምሮ፣ የክፋት አበጋዞች፣ የሐሰት ምንጮች፣ የሤራ መሀንዲሶች እና የቁማር ሱሰኞች ዳግም እንዳይነዱን ከፈለግን ከጭፍን መንጋነትንወጥተን እናስብ!!! እኔ ለማስጀመር እንዱህ ብያለሁ። እናንተስ? 👉 በነፍሱም በሥጋውም ርኲሰትን የሚጸየፍ፣ ውድቀት ሱያጋጥመው መልሶ በንስሐ የሚታደስብትሁት 👉 ሐቀኛ፦ ለፍትሕ እና ለእውነት የሚኖር፣ ሤራና ቁማርተኝነትን፣ በዜጎች መካከል እድልዎን የሚጸየፍ ደግ አባት/እናት 👉 የህፕገሩቷን የሺ ዘመናት ታሪክ አመዱን ከፍሙንለይቶ ለዛሬ ትውልድ ሙቀትና ከፍታ ወደ ሞተር የሚቀይት፣ የሐሰት ትርክትን፣ ታሪካዊ ጠባሳዎችን አጣምሮ እያጋነነ ለዜጎች ተዋህዶ እንቅፋት የማያኖር፣ የሚከላከል 👉 በሀገሩ ልጆች አእምሮ፣ ጥረትኔ ምክር የሚተማመን፣ የባዕዳን አሻንጉሊትና ተላላኪ ያልሆነ 👉 የቀጠናዊ፣ አህጉራዊና ዓለም ዐቀፋዊ አውዱ ንባብና በሀገሩ ላይ ያለውን  አዎንታዊና አሉታዊ ተጽእኖ ተረድቶ ለሀገር ጥቅም በሁሉም ደረጃ  አመራር እንዲኖረን ስልት መንደፍና መተግበር የሚችል አቅም ያለው፣ እንደ ስድ አደግ ባለጌ ጎሮምሳ ዘለቄታዊነትንየሌለው ግኑኝነት የማፕፈጥር 👉 በጎረቤት ሀገራት መካከል ሰላም ለምስፈን ክሂሎትና ጥበብ ያለው፣ ያሉትን መልካም አጋጣሚዎች የሚጠቀም ብቻ ሳይሆን የሚፈጥር 👉 በሀገር ውስጥ ያሉትን ብዝኃ እምነቶችና ባህሎች። የስነ ምህዳር ብዝኃነት፣ የትፈጥሮ ህብት ብዝኃነትን ሁሉ ለግጭትና ለሽሚያ ያይደለ ለጉድለት መሞላላትና ሕብረታዊንየሕይወት አንድነት እንደ ተቃራኒ ጾታ ተዋህዶ ለፍሬ መምራት የሚችል 👉  ከሀሉ በላይ ክንረ-ሰብእ፣ ክብረ-ሀገር፣ ክ...
የቅርብ ጊዜ ልጥፎች

በድለናል፣ እንመለስ!

ከ፫ ዓመት በፊት የተለጠፈ ነው። አሁንም እዚያው የውድቀት ደረጃን ላይ ስለምንገኝ እንድናስታውስ ደግሜ አጋራሁት። ========= እንመለስ!!! 💠 #ክርስቲያን መሆን ቢሳነን #ተፈጥሮአዊ ሰው ብቻ ለመሆን እንሞክር እንጂ። መምህራኑም ከማስጨብጨብና ከእልልታው ያለፈ ትምህርት አስተምሩንማ! #ክርስቲያን መሆን ቢሳነን #ተፈጥሮአዊ ሰው ብቻ ለመሆን እንሞክር:- በውርጃ ሕጻናትን ከመፍጀት ንስሐ መግባት፣ ወጣቶች ዝሙትን ማቆም፣ ከሰዶምነት መውጣት፣ ዘረኝነትን መጸየፍ፣ ሐሰትና ጥላቻን መጥላት፣ ትዳርን ከማፍረስና ከማርከስ ራሳችንን በክርስትና መጠበቅ   እንዴት ይሰወረናል?  አሁን የምንገኝበት በገዛ አገራችን መሰደድና መገድል፣ መዋረድና መሰደብ፣ ለምን ይመስላችኋል? እግዚብሔርን ስለማስቀየማችን የመጣ ቅጣት እይደለምን? 💠እኛ ክርስቲያን ነን ባዮች በዚህች በቅድስት አገር እየኖርን፣ በዚህ ክርስቲያን በተሰኘ ታላቅ ስም እየተጠራን  በእግዚአብሔር ፊት  ምን እየሰራን እንደሆነ በትክክል አውቀን ንስሐ እንግባ! ከዚያም የአጋንንት ማኅበርና መሣሪያ ሆነው ክርስቲያኖችን በሁለገብ ጥቃት ሥር እያጠፉ ያሉትን ፊትለፊት በአንድነት፣ በአንድ ልብና በእምነት ሆነን እንግጠማቸው!!! በክርስትና እየተጠራ ክፋትን የሚሠራ ሁሉ የአንድ አካለ-ክርስቶስ ብልት ነውና ያልበደለውን ሁሉ ያስቀጣናል!!!  ለሀጥአን የመጣ ለጻታድቃን አንዲሉ። ============ በጥፋታችን እንደንቀጣ  ሰውን ከሰውነት  ባዋረደ፣ ከዜግነትም ውጭ በሚያደርግ፣ ከሁሉም በላይ በጥምቀት የተገኘችዋን የክርስቶስ ልጅነት  ሁሉ አርክሶ፣ዘ ንግቶ በሌላ አይነት የማንነት መሥፈርት  በመሰብሰብ፤ ሌሎችን ለይቶ ለማዋረድና ብ...

ክትስቲያን ወደ ጠላቶችህ ለምረትብአታልቅስ?

ኤዲያ! ራስህን ተከላከል!  ምን የማይለቅ ጽኑ አዚም ነው ኦርቶዶክስ ክርስቲያኑን የተፀናወተው? አታልቅስ!  ሰሚ ወገን የለህም! ካለቀስክ ውድ እግዚአብሔር  ብቻ! እንዴት የሚገድልህ መንግሥት ሊታደግህ  ይደርስልሃል?  ነው መንግሥት ይድረስልኝ  እያልክ ፯ ዓመት ሙሉ ምን ሆንክ አላየኸውም?   ራስህን ተከላከል! ነፃ አውጭም መፍትሄ ሰጭም የለም። በቤተመንህሥትም ሆነ ብቤተ ክህነት የተካድክ፣ እረኞች ግድ ይህን እያወደሱና ካባ እያለበሱ "በርታልን፣ እኛን ብቻ ከድሎታችን አታፈናቅለን ብለው አላግጠውብሃል። መፍትሄው አንድ ሆኖ መነሳት ብቻ  ነው። ለነገሩ  የጎሣ ፖለቲካ ጭፍን መንጋ ለ፶ ዓመታት ያጠቃውን የሃይማኖትና የቋንቋ መለያ የለጠለፈለትን ክፍለ-ሕዝብ በግልፅ እና በመደበኛ ሠራዊት እየጨፈጨፈው  እንደተለመደው  "መንግሥት ይድረስልን" የምትል ድምጽ ከወደ ወለጋ ዛሬም ቀጥሏል።   አዚሙ ምንድነው? አጥፉውን ድረስልን የሚል እንደ ኦርቶዶክስ ክርስቲያን የደነዘዘ ዜጋንየለም!!! የባእዳኑ ተላላኪዎች ገብቷቸዋል፣ በጎሣ መንጋነት ከከፋፈልናቸው እንኳን ምእመኑ መነኩሴውና. ጳጳሱም ዳግም ተመልሶ የክርስቶስ አንድ መንጋ መሆን አይችሉም ብለው ሠርተዉበት አሁን የምናየውን ጎጠኛ፣ በደም ውስጥ ቆሞ የግል ፍተወቱን የሚያርካ፣ የአንድ እምነትና ቋንቋ ባለቤትና ተጠቂ የሆነውን አማራን ሕዝብ እንኳ የሚከፋፍል ሆኖ አገኙት። ፈነጩበት። ከዘረኛ ፖለቲካ የበለጠ የአማራ ጠላቱ ጎጠኛና ናርሲሱስት ባህርይ ያላቸው የፋኖና የዲያስፖራ ደጋፊያቸው ነው።  እነዚህ ቅርብ አዳሪ ጎጠኞች  ከህዝብ ሞይ፣ ስደት፣ መራብ፣ የሕፃናት ትምህርት ማጣት፣ የወጣት በጤርነት መጠበስ...

የብሔር ፖለቲካ ነጋዴዎች የሚጠቀሙት ስልት ሁሉ ይመሳሰላል ልበል?

"አሥር ጊዜ ደጋግመህ  ለካ፣ አንድ ጊዜ ቁርጥ" ለአናፂ ከተነገረ ለሕዝብ ሕልውና ተጋድሎ "መቶ ጊዜ ምከር አንዴ ወስንና ፈጽም" የምትል ብሂል ብናቀንቅን ስህተት  አይመስኝም። ========== እንደምታዘበው ከሄነ የብሔር ፖለቲካ ነጋዴዎች የሚጠቀሙት ስልት ሁሉ ይመሳሰላል ልበል?  * በሕዝብ ስም መማል፣ ግን ሕዝቡን እቃቸው ማድረግ  * ደም፣ አጥንት፣ ቋንቋ፣ ትርክትን መሣሪያ አድርጎ ክብረ-      ሰብእን፣ እውነትን ሰብአዊነትን መድፈቅ፣ * ሤራ * የሚመለኩ ጥቂት ሰዎችን ግን በብዙ  መስዋእትነት መፍጠር * ጎጠኝነት * በሕዝብ ጀርባ ከባዕዳን ተወዳጅቶ ለሥልጣን መሥራት * ሐሰተኝነት ወዘተ ህወሃትን ኦነግ፣ ብልጽግና ወዘተ ነውር የሚፈጽሙት የቡድን ጠባብ ፍላጎታቸውን በኦሮሞ በትግራይ ሕዝብ "ጥያቄ" ስም ነው። ሙስናቸውንም በልማትና በሕዝብ ሀብት የማፍራት ስም ራሳቸውን ያበለጽጋሉ። ይህን የመሰለ ክህደት በፋኖ መሪዎች ምልክት ከታየ የህልውናንታጋዮች ሳይሆኑ ጸረ-አማራ ሊባሉ ይገባል።   አማራ ይህ ሁሉ የጠላቶቹ ርኩስ ልማድ አይስማማውም ባይ ነኝ። ምክንያቱም ሤረኞች ትርክትብፈጥረው፣ ማኒፌስቶ ጽፈው፣ የሰውን ጠላት አበጅተው፣ ከባእዳን መክረው ያስጀመሩት የሕወሃትና የኦነግንአምሳል አይደለም። ራስን የማዳን የትቀደሰ የሰብአዊነትና የፍትህ ተጋድሎ ነው። ተፈጥሮአዊ ነው። ይህን ጠልፎ የጥቂት በሽተኞች መገልገያንለማድረግ መሞከር የወንጀሎች ሁሉ ወንጀል ነው። =========== እሁን አሁን መሬት ላይ ከተንሠራፋው የባንዳነት ስነልቦና የተነሳ   በአንድ ወጥ አስተሳሰብም  የእማራን ትግል እንኳ ለመምራት አልተቻለም። ይህን ጉድለት ያመጣው በአብሮነት ከማሰብ ይልቅ  ...

ሰው የማይታወቅበት አመራርና አስተዳደር በኢትዮጵያ

"ሰው ሳትሆን ሰው አትምራ፣ ተመሪዎችን በልክህ ትከረክማቸዋለህ" የሚል ብሂል ላስተዋውቅ መሰለኝ? በሕይወት ከምመለክተው የእኛ ሀገር ዋና የችግር መንጭ (1) ሰውን የማያውቁ የሰው መሪዎች እና (2) ሃይማኖት የሌላቸው የሃይማኖት መሪዎች ድምር ነፍስንም ሥጋንም እየጎዱ ነው። እነዚህን ለመታገል የሚነሳ ማንኛውም ግለሰብእ ታጋይ ወይንም መሪ እራሱ ከእነዚህ መቅሰፍቶች ለመቃረን፦ "ሰው" መሆኑን፣ ፈሪሃ እግዚአብሔር እንዳለው፣ ለራሱ የግል ፍተወት መርኪያነትና የባዕዳን ማኅደርነት የሚያገለግል አለመሆኑን ማረጋገጥ ይኖርበታል። ከአጥፊ እንታደጋችኋለን፣ ለህልውናችሁ እንድትታገሉ እንመራችኋለን እያሉ "ሰውን" የማያውቁ፦ --› ስው ሳይሆን ብሔረ-ስብእ፣ --› አማኝ ሳይሆን ካህንና ጳጳስ፣ --› በእውነት ላይ ቆመው ሐርነት ሳይኖራቸው "ነጻ አውጭ ፣ የህለውና ታዳጊ፣ መሪ ወዘተ" ባዮች የአዳዲስ መከራ ፈልፋዮች እንጂ መፍትሔዎች ሊሆኑ አይችሉም። ----- የሥልጣንና የዝና ጥማት ያደነቆራቸውና "ሥጋ ብቻዎችን" (ክብር-ነፍስን የማያውቁ የሆድ ሎሌዎች) መሪ ከማድርግና ሥጋ ብቻ ከመሆን ራስን መጠበቅ፣ ማሰብ፣ ማሰላሰል፣ በእምነት መጽናትን እንለማመድ። ለበለጠ ዐሳብ --› ይህን ይመልከቱ፣ ይሟገቱ፣ አዳዲስ "ሰውነትን" ያገናዘበ ዐሳብ ያመንጩ። ሰውን የማያውቁቱ የጎጥ ባሮች በሰጡኝ ስሜ "ጃል" ዋቄ. ነኝ ============ ሰው የማይታወቅበት አመራርና አስተዳደር በኢትዮጵያ  ሰውነትን ያላወቁ ሰው ነን ባዮች ከመክራችን ሊገላግሉን አይችሉም! ጭፍን መንጎች እየተከተላችሁ መከራችሁን አታራዝሙት! ለሰው ያለን ትርጉ እንኳ አላግባባ ይበለን?  ለብልጽ...

በግላችሁ ጎልሙቱ! ሕዝብ ይዛችሁ አትሙቱ!!

በግላችሁ ጎልሙቱ! ሕዝብ ይዛችሁ አትሙቱ!!  https://ethiopiaorthodoxchristian.blogspot.com/2025/06/blog-post_62.html ነገር ግን  እንደ ሕወሃትና ኦነግ   የየሠፈራችሁን  የዋህ አታልላችሁ ሕዝብ ይዛችሁ አትሙቱ! ብሎ መናገር ሳይረፍድ መነገር አለበት። ከ፶ ዓመቱ የናርሲስቶች እና የዘረኞች የሤራ ፕሮፓጋንዳ ተማሩ! ለተከተላቸው ምን እንዳተረፉላቸሁ አስቡ! ================== እንደ እኔ ---- ግለ-ሰብእን ለማረቅ  የግለሰቡን ሰንእና የጎዳውን መሠረታዊ ዐስተሳሰብን ማቃናት  ለነፍስ ዋጋ ብዙ ያለው ይመስለኛል።  ጥመት ከጠማማ አእምሮ መንጭታ አድጋና ተንሰራፍታ  ትውልድን እንዳትበክል በዐሳብ ላይ መነጋገር   ለሀገር ይተርፋልና ከአንድ ጉልምት ድውይ ግለሰብ ተነስቼ  ትውልዱን እናገራለሁ።  የእኔ የሕይወት መርህ ምንጩ ቤተክርስቲያን ናት። እውነትን በፍቅር ስንናገር ሁላችንም ለታመሙ ወገኖቻችን ሐኪሞች እንሆናለን። ሌሎችም እኛ ስንታመም ያክሙናል። በጎጥና በሌላም የመሰባሰቢያ ምክንያት መነሻነት የቡድን ዕሳቤ ባርነት ተይዘን ጭፍን መንጎች ስንሆን  ግን ሁላችንም እንታመማለን። ሐኪም አይገኝም፣ ከተገኘም ክፉና ደጉን፣ ጤናና በሽታን መለየት እንዳይችል የቡድን አምላክ አይፈቅድለትም። ሞቶም  እያለ እኔን ምደሉ. ተከተሉኝ እያለ ጥፋቱን ያጋባል። የታረማችሁ  ወገኖቼ አርሙኝ።  =========  የጎጥና የድብቅ ዓላማ ወዳጆቹ የምትሆኑ ሁሉ ለመናገርና ሀሳብን ለማካፈል ምክንያት ለሆነኝ ወንድሜን ምስግኑት። እኔ ላነጋግረው ብደውልለት  ለዚህ  የሕፃን ፕሮፓጋንዳ አገል...

ለሁኔታችን የሚመጥን መሪ እንዴት እንወቅ?

ለሁኔታችን የሚመጥን መሪ እንዴት እንወቅ? #በአብይ እና ከርእዮት ወላጆቹ ከአመጡብን መከራ ተነስተን ስለ መሪዎች ሰብእና ምን እንማራለን? ========== #አብይ አህመድ እርሱን ከፈጠሩት ቀዳሚ ዘረኛ መሪዎች በመርከብ በሀገራችን ላይ ያደረሰውና እያደረሰው የሚገኘው ጉዳት ካሣ የማይገኝለት ቢሆንም አንድ ትልቅ ውለታ ለትውልዱ ውሏል። እርሱም የፖለቲካ መሪዎችን በምላሳቸውና በብልጣብልጥ ንግግሮቻቸው እና በአዲስነትና ለውጥ ሽፋን ምን ያህል ሕዝብን አደንዝዘው በማስከተል ወደ አጠቃላይ ውድቀት ሊወስዷቸው እንደሚችሉ ማሳየቱ ---- እንደ እኔ ግምት ከአሁን በኋላ ትውልድ ሁሉ  የፖለቲከኞችን የመጨርሻ ደረጃ ህሊና ቢስነትና የማታለል አቅማቸው ተገንዝቦ መሪዎችን ለመምረጥና ለመታዘዝ ከስሜትና ንግግር ባሻገር በግልጽ መሥፈርት ብቻ እንዲመዝን ትምህርት አግኝቷል እላለሁ። ስለዚህ ----- መሪ ስንመርጥ ስንከተልና ስን ታዘዝ አስቀድመን  በሚከተሉት ነባር ሰብአዊ እናቶች  መመዘኛ መሆን ይኖርበታል ብለን የምንግባባ ይመስለኛል:- ፩) ፈሪሃ እግዚአብሔር እንዳለው በአጠቃላይ ሕይወቱ ያስመሰከረ ፪) ለራሱ ሳይሆን ለሚመራቸው ወገኖቹ ለመሰዋት ዝግጁነቱን በተግባራዊ ሕይወቱ ያረጋገጠ፤ ፫) ተክለ ሰውነቱን መንጋ አጫፋሪዎችን በጎጥ፣ በጥቅም፣ በተስፋ እያጓጓ  በማሰማራት የማይገነባ ትሁትና እውነተኛ፣ በተግባር ብቻ ከፍ የሚል፣# ፬) ወገንተኝነቱን ከጎጥና ከጎሣ ነጻ አውጥቶና እርሱም  ወጥቶ ለክብር-ሰብእ፣ ለፍትህ፣ ለእውነት ፣  ለአሁንና ለመጭው  ትውልድ ሁለንተናዊ ደኅነት ማድረጉን በተግባር ያስመሰከረ፤ ፭) በግል ሕይወቱ ከስግብግብነት፣ ፍቅር ንዋይ፣ ዝሙት፣ ትዳርን ከማርከስ፣ ከሤራ፣ ከከፋፋይነት፣ ከነ...