ኢትዮጵያን የሚመጥን መሪ ለመፍጠር መስፈርት ላይ ሀሳብ እናዋጣ! በሰው ደም ካልታጠቡ፣ በዜጎች ዕንባ ካልዋኙ አየር የተነፈሱ የማይመስላቸው ድውያነ አእምሮ፣ የክፋት አበጋዞች፣ የሐሰት ምንጮች፣ የሤራ መሀንዲሶች እና የቁማር ሱሰኞች ዳግም እንዳይነዱን ከፈለግን ከጭፍን መንጋነትንወጥተን እናስብ!!! እኔ ለማስጀመር እንዱህ ብያለሁ። እናንተስ? 👉 በነፍሱም በሥጋውም ርኲሰትን የሚጸየፍ፣ ውድቀት ሱያጋጥመው መልሶ በንስሐ የሚታደስብትሁት 👉 ሐቀኛ፦ ለፍትሕ እና ለእውነት የሚኖር፣ ሤራና ቁማርተኝነትን፣ በዜጎች መካከል እድልዎን የሚጸየፍ ደግ አባት/እናት 👉 የህፕገሩቷን የሺ ዘመናት ታሪክ አመዱን ከፍሙንለይቶ ለዛሬ ትውልድ ሙቀትና ከፍታ ወደ ሞተር የሚቀይት፣ የሐሰት ትርክትን፣ ታሪካዊ ጠባሳዎችን አጣምሮ እያጋነነ ለዜጎች ተዋህዶ እንቅፋት የማያኖር፣ የሚከላከል 👉 በሀገሩ ልጆች አእምሮ፣ ጥረትኔ ምክር የሚተማመን፣ የባዕዳን አሻንጉሊትና ተላላኪ ያልሆነ 👉 የቀጠናዊ፣ አህጉራዊና ዓለም ዐቀፋዊ አውዱ ንባብና በሀገሩ ላይ ያለውን አዎንታዊና አሉታዊ ተጽእኖ ተረድቶ ለሀገር ጥቅም በሁሉም ደረጃ አመራር እንዲኖረን ስልት መንደፍና መተግበር የሚችል አቅም ያለው፣ እንደ ስድ አደግ ባለጌ ጎሮምሳ ዘለቄታዊነትንየሌለው ግኑኝነት የማፕፈጥር 👉 በጎረቤት ሀገራት መካከል ሰላም ለምስፈን ክሂሎትና ጥበብ ያለው፣ ያሉትን መልካም አጋጣሚዎች የሚጠቀም ብቻ ሳይሆን የሚፈጥር 👉 በሀገር ውስጥ ያሉትን ብዝኃ እምነቶችና ባህሎች። የስነ ምህዳር ብዝኃነት፣ የትፈጥሮ ህብት ብዝኃነትን ሁሉ ለግጭትና ለሽሚያ ያይደለ ለጉድለት መሞላላትና ሕብረታዊንየሕይወት አንድነት እንደ ተቃራኒ ጾታ ተዋህዶ ለፍሬ መምራት የሚችል 👉 ከሀሉ በላይ ክንረ-ሰብእ፣ ክብረ-ሀገር፣ ክ...
ከ፫ ዓመት በፊት የተለጠፈ ነው። አሁንም እዚያው የውድቀት ደረጃን ላይ ስለምንገኝ እንድናስታውስ ደግሜ አጋራሁት። ========= እንመለስ!!! 💠 #ክርስቲያን መሆን ቢሳነን #ተፈጥሮአዊ ሰው ብቻ ለመሆን እንሞክር እንጂ። መምህራኑም ከማስጨብጨብና ከእልልታው ያለፈ ትምህርት አስተምሩንማ! #ክርስቲያን መሆን ቢሳነን #ተፈጥሮአዊ ሰው ብቻ ለመሆን እንሞክር:- በውርጃ ሕጻናትን ከመፍጀት ንስሐ መግባት፣ ወጣቶች ዝሙትን ማቆም፣ ከሰዶምነት መውጣት፣ ዘረኝነትን መጸየፍ፣ ሐሰትና ጥላቻን መጥላት፣ ትዳርን ከማፍረስና ከማርከስ ራሳችንን በክርስትና መጠበቅ እንዴት ይሰወረናል? አሁን የምንገኝበት በገዛ አገራችን መሰደድና መገድል፣ መዋረድና መሰደብ፣ ለምን ይመስላችኋል? እግዚብሔርን ስለማስቀየማችን የመጣ ቅጣት እይደለምን? 💠እኛ ክርስቲያን ነን ባዮች በዚህች በቅድስት አገር እየኖርን፣ በዚህ ክርስቲያን በተሰኘ ታላቅ ስም እየተጠራን በእግዚአብሔር ፊት ምን እየሰራን እንደሆነ በትክክል አውቀን ንስሐ እንግባ! ከዚያም የአጋንንት ማኅበርና መሣሪያ ሆነው ክርስቲያኖችን በሁለገብ ጥቃት ሥር እያጠፉ ያሉትን ፊትለፊት በአንድነት፣ በአንድ ልብና በእምነት ሆነን እንግጠማቸው!!! በክርስትና እየተጠራ ክፋትን የሚሠራ ሁሉ የአንድ አካለ-ክርስቶስ ብልት ነውና ያልበደለውን ሁሉ ያስቀጣናል!!! ለሀጥአን የመጣ ለጻታድቃን አንዲሉ። ============ በጥፋታችን እንደንቀጣ ሰውን ከሰውነት ባዋረደ፣ ከዜግነትም ውጭ በሚያደርግ፣ ከሁሉም በላይ በጥምቀት የተገኘችዋን የክርስቶስ ልጅነት ሁሉ አርክሶ፣ዘ ንግቶ በሌላ አይነት የማንነት መሥፈርት በመሰብሰብ፤ ሌሎችን ለይቶ ለማዋረድና ብ...