ወደ ዋና ይዘት ዘለው ይሂዱ

ልጥፎች

ከፌብሩዋሪ, 2026 ልጥፎች በማሳየት ላይ

የፖለቲካ ጠላት የተደረገውና የህልውና አደጋ የተጋረጠበት ኦርቶዶክሳዊነት እና የተከዳው ኢትዮጵያዊነት

የፖለቲካ ጠላት የተደረገውና የህልውና አደጋ የተጋረጠበት ኦርቶዶክሳዊነት እና የተከዳው ኢትዮጵያዊነት 24-10-2015 ዓ/ም ካምፓላ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ። የቤተክርስቲያን የሕልውና አደጋ የአግርም ነው!!!    ዛሬ አደጋው ከውጭ አይደለም።   በእርግጥ መርዛማው የኢትዮጵያዊነትና ኦርቶዶክሳዊነት ጠላት ፖለቲካ የሀሳብ ምንጩ ከውጭ ነው፤    ይህ ፖለቲካዊ አመለካከት የተጣባው ትውልድ ማንኛውንም ነባር ባህልና እምነቶች የማጥፋት ዝንባሌውን ከራሱ ያመነጨው እስኪመስለው የተጋተው ከውጭ ነው። በቅኝ ገዥዎችና ከባዕዳን ከ700 ዓመታት አስቀድሞ የተጀመረ ሂደት ነበር፥    የዛሬ 180 ዓመታት ገደማ አስቀድሞ ሸዋ አንኮበር ቤተመንግሥት የጀርመኑ ጆሃን ሀኒክራፍ ሉድዊግ በቤተክርስቲይን እና በነባሩ የኢትዮጵያ ስነ መንግሥት ላይ እሾኽ ተከለበት፥    ያ እሾኽ ከተተከለ ከ50 ዓመታት በኃላ የዛሬ 130 ዓመታት ገደማ በጣሊያን ተኮትኩቶ አገር በቀል ተከታይ አፈራ፤ ከናዚ ሶሻሊሰት ፓርቲ መሸነፍ በኋላ ከጀርመን ያመለጡትና ወለጋ የተጠጉት “የጀርመን ክርስትና” የተሰኘ ለዘረኝነት የሚስማማ ፕሮቴስታንቲዝም ያነገቡ ሰባኪያን    የዛሬ 72 ዓመት ገደማ ሥር እንዲሰድ በተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤትና በቀ/ኃ/ሥ ዩኒቭረሲቲ መዋቅራዊ የትምህርት አቅም ተሰጠው፤   የዛሬ 60 ዓመታት አካባቢ የመጀመሪያው መርዛማ ፍሬ እሸቱ ታየ፥ በመንበረ ልዑል ቤተ መንግሥት ውስጥ መሪዎችን ሰውቶ የመጠፋፋት ባህልን አስተዋወቀ፥    የዛሬ 50 ዓመት ገደማ በአገራዊነትና ነባርነት ላይ የሚያምፀው ትውልድ እግዚአብሔር የለሽ የፖለቲካ ርእዮተ ዓለምን ታጥ...

ኦርቶዶክሳዊ ካህን ወይንም አባት እንዴት ይታወቃል?

ኦርቶዶክሳዊ ካህን ወይንም አባት እንዴት ይታወቃል? በአባትነት ስም የዘራፊዎች ኔትዎርክ የሚደግፉ ምእመናን ቆም በለው ማሰብ የጠበቅባቸእዋል። የጠበቅብናል። ከጭብጨባና ከእልልታ፣ ከሞንታርቦና ከሁካታ እንውጣ። ክህነት ለገቢ የሚገቡበት ሙያ አይደለም፣ ክህነት ክርስቶስን መስሎ የሰው ልጆችን ወደ እግዚአብሔር አብ እቅፍ የሚመሩበት፣ ከልጁ ከቃለ እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ ጋር በአባት ቀኝ እንዲቀመጥ ለማገልገል በራስ ላይ የሚጭኑት የሰማእትነት ሕይወት ነው። ክህነት የመንግሥተ ሰማያት መግቢያ መክፈቻ ቁልፍ ነው። ይህን መክፈቻ የሆድ መሣሪያ በማድረግ በሰው ፊት መንግሥተ እግዚአብሔርን መዝጋት የበደል ሁሉ በደል ይሆናል። (በስንክሳራችን ሰኔ 17 ቀን የሚነበበውን የአባ ለትጹን ታሪክ በማንበብ በክህነት ስም መቀለድ ምን እንደሚያስከትል መረዳት ይቻላል።0 አባት የሚባለው ቢያንሰ የሚከተለውን ካላሟላ ሊገሰጽ፣ በቆና ተዳኝቶ ከክህነት ጾታ ውጭ ሆኖ ሕዝባዊ ተንሳሒ መሆን አለበት፦ 1) ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ካህን የምትላቸው፦ 👉 ኦርቶዶክሳዊ ካህን በጋብቻ ውስጥ ንጽህ የጠበቀ 👉 ዝግተኛ 👉 ሱሰኛነትና ከጠጭነት የራቀ 👉 አመጽኛነትና ከመጣላት ፈጽሞ የራቀ ሰላማዊ 👉 ታማኝ፣ በሌብነትና በፍቅረ ንዋይ የማይታማ፣ በማጨብርበርና የማይከሰስ፣ 👉 በዘመደ አዝማድ ተክብቦ ሌላውን በማግልል በክርስቲያኖች መካከል ለመለያየት ምክንያት የማይሆን፣ 👉 በሚኖርበት ማኅበረሰብ በክፋት ስሙ የማይነሳ፣ (1 ጢሞ 3፣ ቲቶ 1) 2. የቤተ ሰብእና የትዳር መለኪያ፦ 👉 ቅስና በጋብቻ ወይንም በፍጹም ምንኩስና ውስጥ ብቻ የሚኖሩት የቅድስና ሕይወት በመሆኑ፦ 👉 ጋብቻ የሚፈጸመው ከእጅ መጫን አስቀድሞ ነው፣ የምንኩስና ...