ጎሰኝነት/ኑዑስ ብሔርተኝነት ባለ ረዥም ታሪኳ ኢትዮጵያ ውስጥ ሳይቀር እንዴት ተፈጠረ፣ እንዴትስ በአፍራሽነቱ ጸና? የሀገራችን ዋና የመከራ ምንጭ፤ የስደት፣ ዘር ማጥፋት ደረጃ መድርስ 1. በማኅበራዊና ተፈጥሮአዊ ሰንሰለታዊ መስተጋብር የሚፈጠሩ ታሪካዊ አሻራዎች፦ በዓለም ውስጥ፣ በተለይ በአፍሪካችን ጎሣዎች የኖራሉ። ለዩ ቋንቋዎች፣ ልዩነት የሚያሳዩ ባህሎች፣ በተወሰነ ደርጃ በአስተዳደርና ፍትሕ ሥርዓት ለዩነታቸው እየተዋሐደ ሳይሆን እየደመቀ መቆየቱ ይታያል። ይህ ንዑስ ማንነት ጤናማ ሆኖ የሚኖረው ፖልቲካዊ መሣሪያ፣ የምጣኔ ሀብት ሽሚያ ምክኒያት ሲሆን ጎጅ፤ በተፈጥሮው ተከብሮና ተመጋጋቢ ህብረት አስገኝቶ ለእድገትና ለአቅም ምንጭ ይሆናል። 2. የቅኝ ገዥዎች ተጸኖ፦ በከፋፍለህና አዳከመህ ግዛ የቅኝ ግዥዎች ስልት በቀጥታ በአካል ተገኝተው ባርያ ያደረጓቸው የአፍሪካ ሀገራት፣ እንደ ኢትዮጵያ በትምህርት ስም አእምሮ አጠበው ባርያ ያደርጉት አገር ውስጥ ያሉ ታሪካዊና በማኅበራዊ መስተጋብራዊ ዝግመተ ለውጥ የተፈጠሩ ኑዑሳን-የጎሣ ማንነቶች ከህብረታዊ አንድነትና ከተዋህዶ በተቃራኒ እንድ ሕወሃትና እንደ ኦነግ ባሉ የባዕዳን የአእምሮ ባሪያ ልሂቃን ጠላትነት አፍርተዋል። ከመዋሀድ በተቃራኒ መራራቅና መጠፋፋትን ሳይቃወሙት ለልሂቃኑ የጥፋት መሣሪያነት ተሰልፈው ቀጥለዋል። 3. የቋንቋና የባህል ብዝኃነት፦ አፍሪካ ውስጥ በአጠቃላይ በአንድ ሀገረ-መንግሥት ውስጥ ብዙ ቋንቋ ተናጋሪዎችና ልዩ ልዩ ባህሎች አሉ። እንዚህ ልዩነቶችን ወደ ሀገራዊ የጥንካሬ ምንጭ ለማሳደግ ከሚደረገው ጥረት የበለጠ በቱሪስት ሸቀጥነት፣ በየጎሣ መሪዎችና የየጎሣው አባ...
This is a spot where I post and share part of my daily reality. I would love to hear from others too to learn how differently we interpret daily encounters including our imaginations. ይህ ሥፍራ የየዕለት ገጠመኞቼን፣ እንዴት በዕለቱ እንተረደሁትና የማስበውን ለሌሎች ያማጋራበት ነው፡፡ የሌሎችን በመስማትና ምን ያህል ዓለማችንን በተለያየ መንገድ እንደምንመለከታት ለመማር እጓጓለሁ፡፡