የአማራ ሕዘብ የህልውናና የፍትህ ተጋድሎ የውስጥ እንቅፋቶች፦ በእኔ ምልከታ ፲ ናቸው ። ሌሎችም ሊኖሩና በሌላ እይታ ሊብራራ ይችላል። እኔ ቁንጽልና አጭር ምልከታ ነው የማደርገው። በእርግጥ አሁን ባለው የትግሉ አውድ ሰዎች መወያየት የሚፈልጉት ጀግና እንዲሆንላቸው፥ ፋኖን ጠቅልሎ እንዲገዛላቸውና ከትጥቅ ትግል ማብቃት በኋላ የአገር ገዥዎች አድርጎ እንዲያነግሥሳቸው የሚሹ ወገኖች --- ጉዳይ ላይ መወያየት አይፈልጉም። ስለ ግለ-ሰብእና ስለ ቡድን ልዩነትና መበላለጥ፥ ማን ትክክል እንዳልሆነና እንደሆነ በመወጠር ስሜትን በሚቀሰቅስ፥ ማስበን በሚገድብ፥ ርቀት ከማየትን በሚጋርድ ድምጽ ውስጥ ሕዝቡን በራሳቸው ዙሪያ መሰብሰብ ይሻሉ። እኔ ግን ጠቃሚ የሚመስለኝ ከግለሰቦችና ቡድኖች ጉዳይን አስቀድመን በመነጋገር ግለሰቦችና ቡድኖች ጉዳዮችን አንዳይጠልፉ፥ በተቃራኒው ለትግሉ ዓላማ፥ ፍልስፍና፥ ርእይ፥ ሂደት፥ ውጤት፥ የውጤት ዘለቃዊነትና የመስዋዕትነት መቀነስ አንጻ ብቻ እየተመዘኑ አንዲስተካሉ ማስገደድ/ማስተጋገልና ቀንበር ማስገባት ላይ ማተኮር ይመስለኛል። በዚህ ማኅቀፍ ውስጥ የግል አስተያየት አጥቻለሁ!!! መወገድ ያለባቸው የትግሉ እንቅፋቶች፦ ( ፩ ) በአድዋ በቆሰሉ ቅኝ ገዥዎች፥ በአምላክ-የለሽ ማርክሳዊ ፖለቲካ ውድቀት ላይ የተወለዱት ሕወሃትና ኦነግ በሰፉት የ ዘ ረና የአፓርታይድ ሕገ - መንግሥት ውስጥ የተወለደው ትውለድ ከ1942ቱ የቀኝ ገዥዎች አእምሮ አጣቡ ትምህርት ቤት መከፈት ጀምሮ ብናስበው አሁን 70 ዓመታት የሚላው ነው። ሕወሃትና ኦነግ የ50 ዓመት ጎልማሶችን አፍርተዋል። የአማራ ህልውና አደጋ ጥንስ ከ70 ዓመት አስቀድሞ የተጀመረና ባለፉት 50 ዓመታት ሕወሃት / ኢሕአዴግ ወደ ሕግና ፖ...
This is a spot where I post and share part of my daily reality. I would love to hear from others too to learn how differently we interpret daily encounters including our imaginations. ይህ ሥፍራ የየዕለት ገጠመኞቼን፣ እንዴት በዕለቱ እንተረደሁትና የማስበውን ለሌሎች ያማጋራበት ነው፡፡ የሌሎችን በመስማትና ምን ያህል ዓለማችንን በተለያየ መንገድ እንደምንመለከታት ለመማር እጓጓለሁ፡፡